June 5, 2023
6 mins read

ኢትዮጵያን መክሰስ እና መዉቀስ የት ሊያደርስ ?

ETHIOPIAN INTEL

አበዉ የገበያ ግርግር ለዘራፊ በጀዉ ይላሉ ፡፡

በአንድ ወቅት አምስት በሬዎች ነበሩ ቀለማቸዉም ይለያይ ነበር ይባላል ፡፡ ይሁንና አባ ጅቦ ሊበላቸዉ አስቦ የበሬዎች አንድነት ፈርተ ነበር እና በተናጠል ሊበላቸዉ መላ መታ ፡፡ ይኸዉም ከመካከላቸዉ በቀለም ከሩቅ የሚታይ ወይም የሚረብሽ የትኛዉ በሬ እንደሆነ መጠየቅ እና ማረጋገጥ ነበር ፡፡ ይህን መላ ምት ይዞ ከናንተ መኃል በሩቁ ለጠላት የሚታይ ነጭ በሬ አለ ይህም ብቻ አይደለም የሚረብሽ የቱ ነዉ….እያለ ተራ በተራ ጨረሳቸዉ ይባላል ፡፡

ይህ ለኢትዮጵያዉያን በግላጭ የሚሰራ ዕዉነት ነዉ ፡፡

ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊ ዓማራ ህዝብ በአንድነት እና በህብረት መንቃት እና መደራጀት ተስኖት ለሠላሳ ዓመታት የመከራ እና የሞት ቋጥኝ እንዲሸከም ወዶ እና ፈቅዶ በመቀበል አስከዛሬ ሁለተናዉን ከነሙሉ ባርነት እና ስደት ለበአዴን አስረክቦ በተናጠል ሲገለል እና ሲበደል እዚህ ደርሷል፡፡

አሁንም እንደከዚህ በፊት በእኔ ዕምነት ለኢትዮጵያ መፃኢ ዕድል ወይም ዕጣ ፋንታ በዓማራዉ እና የዓማረዉን እና የኢትዮጵያን የቀደመ እና መጪ ትስስር የሚረዳ እና የሚያሳስበዉ ኢትዮጵያዉያን መዳፍ ስር ነዉ ፡፡

ሁሉም ኢትዮጵያዉያን እና ዓለም ቀርቶ የኢትዮጵያ ጠላቶች የሚስማሙበት አንድ ነገር አለ ኢትዮጵያን የግል ንብረት አድርጎ ለመቀጠል እና በኢትዮጵያ ፍርስራሽ የምኞት አገር ጎጆ ለመመስረት ብቸኛዉ መንገድ ዓማራን ከሌላዉ ኢትዮጵያዊ መነጠል እና ማግለል ነበር ፡፡

ይህም በኢትዮ ጠል ኃይሎች የፈጠራ ትርክት ጨቋኟ ኣማራ ብሎ ከብሄራዊ የፖለቲካ ፣የምጣኔ ሀብታዊ እና ኃይማኖታዊ ሚና ማግለል ነበር ይህን አሳክቷል ፡፡  ይህም በጠላት ጥንካሬ ሳይሆን በዓማራ እና አገራቸዉን በሚወዱ ኢትዮጵያዉያን ህብረት እና የጋራ የዓላማ አንድነት እና ፅናት ማጣት ነበር ፡፡

ሁሉም በየተራ በጂብ አስኪነጠቅ ጠላቱ እንዲታደገዉ ወይም ሌላዉ እንዲሞትለት በመጠበቁ በየጊዜዉ ተራዉን ጠብቆ የተበላ ተበላ ያልተበላ ሊበላ አሁንም በተስፋ አይሉት በወረፋ ሞቱን ይጠብቃል ፡፡

በአዴን የተሰፋለትን ካባ ማዉለቅ ወይም መቀየር የማይችል በግዑዝነት ወደ ምንም “በድንነት ” የተሸጋገረዉ ገና በኢህአዴግ ምስረታ የኢትዮጵያን እና የዓማራን ህዝብ መራራ የትግል ዉጤት እና ድል አሳልፎ ለትህነግ በ1982 ዓ.ም ኣሳልፎ ሲሰጥ በልኩ ከተሰጠዉ ካባ ዉጭ ምንም ማድረግ የማይችል መሆኑን አሜን ብሎ በመቀበል አንኴንስ  የኢትዮጵያን እና ዓማራን ህዝብ ጥቅም እና ስም ሊያስጠብቅ ቀርቶ የራሱን ድርጂት እና የሞቱለትን ጓዶች መዘከር የማይችል መሆኑን ድሮ ነዉ ያስመሰከረዉ ፡፡

ይባስ ብሎ በወረራ እና በዕብሪት የወደመዉ የሠዉ እና የብሄራዊ ሀብት ሳይበቃ ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር በጎጃም ፣ ጎንደር ፤ ወሎ እና ሸዋ ላይ በህዝብ እና በኃይማኖት ተቋማት ላይ ዕልቂት እንዲሆን የሚፈቅድ ወይም ሲሆን የሚያይ ድርጂት ከጅምሩ አገር እና ህዝብ ለመጉዳት እንጂ ለመታደግ የማይችል መሆኑን ከዚህ በላይ ማሳያ አይኖርም ፡፡

ቢመሽም ሁሉም ኢትዮጵያዉያን እና በተለይም የዓማራ ህዝብ የዘመናት መከራ ቀንበር በጋራ እንዲጫንበት የፈቀደ ነገር ግን በተናጠል እየሞተ ያለዉ ከራሱ መሞት ባሻገር የትዉልድ እናየአገር ሞት መዳረሻ ምዕራፍ ላይ መሆኑን አዉቆ ለአገሩ እና ለራሱ ህልዉና መቀጠል አንድነቱን እንደብረት ማጠንከር ይኖርበታል ፡፡

ይህ ባይሆን የአምስቱ በሬዎች እጣ እና መጨረሻም በመቃብሩ የጂቦች ዋሻ ይመሰረታል ፡፡

በጦርነት ጊዜ አንተን ያሉ ሁሉ፣

ዓማን ቢሆን ነዉ ወይ  ጥለዉህ የበሉ ፡፡

ይህ ስነ ቃል ፡ ለመላ ኢትዮጵያዉያን የቁርጥ ቀን ልጆች ዋኖች /ጀግኖች ይሁን ፡፡

አንድነት ኃይል ነዉ !

 

አለን -ፀ. ሥላሴ

3 Comments

  1. ለምዕራባዊያን ራስ ምታት የነበረው ኢትዮጵያዊያን በባዶ እግራቸው ፋሽስት ጣልያን ያሽነፉበት ለአፍሪካ ክብር ለምዕራባዊያን ውርደትን ነበር የድሉም ምክንያት የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ና ፍቅር ነበር አሜሪካ ይህንን አንድነት ለመሥበር የፋሺሽት ባንዳ የልጅ ልጅ መለስ ዜናዊ በወያኔ ፓርቲ የመጀመሪያው እርምጃ ኤርትራን ማስገንጠል (በአሥገንጣይ ና ተገንጣይ ኦፒሬሽን) እንዲሁም የኢትዮጲያን ህዝብ በዘር የተመሠረተ ፌዴራልዝም መመሥረት ና ህዝቡ በጥላቻ እንድኖር ነበር ።
    ዛሬም የብልጽግና ፓርቲም የአሜሪካን ፍላጎት ከግቡ ለማድረስ በመሳሪያ ሃይል ና በአሜረካ ድጋፍ
    1 _ በከፋ ኑሮ ውድነት ህዝቡን ማደንዘዝ ማዳከም ህዝቡም ተስፋ ቆርጦ እንዲስደድ ።
    2- ኢትዮጲውያንን በዘር ለይቶ በገጠር የጅምላ ጭፍጨፋ ና ከእርሻቸው ማፈናቀል እንዲሁም በከተማ የመኖሪያ ቤቶች አፍሪሶ ማፈናቀል ።
    3- ቤተእምነቶችን ማፍረሥ ና ምዕመናንን መግደል ።
    ይህን አደገኛ ሴራን ለማክሽፍ ይህ ትውልድ በቂ እውቀት ፍላጎት ሞራል ና አንድነት ባለመኖሩ የኢትዮጵያ የወደፊት እድል እንደ ሶማሊያ ና አረብ ሀገሮች ለመበተን የተቃረበች ይመስላል ።

  2. የዛሬዎቹን ዘልዛላና ወገንተኛ ፓለቲከኞችና የብሄር ሰካራሞች ተወት አድርገን ያለፈውን ስናይ ብዙ ትምህርት እናገኛለን። ለምሳሌ የደርጉ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት ኮሎኔል ደበላ “ዲንሳ ዳአኒ ጃራቹ ወይም ሞቶ መኖር” በተሰኘው መጽሃፋቸው ላይ እንዲህ ይሉናል። የተወለድኩት በአንዲት ገጠራማ የወለጋ ክፍለሃገር ውስጥ ነው። ማንም በምርጫ ከአማራ ከኦሮሞ ብሎ የተወለደ የለም። ከኦሮሞ ብሄረሰብ መወለዴ የእኔ ምርጫ አይደለም። ግን ደስ ይለኛል። የበለጠ ደግሞ በኢትዮጵያዊነቴ እኮራሉ በማለት ግለ ህይወታቸውን አባታቸው ከወለጋ ወደ ጎጃም እየተመላለሱ ይነግድ እንደነበርና የጎጃም ህዝብን ፍቅርና እንግዳ አቀባበል ይተርካሉ። ዛሬ በወለጋ የሚፈጸመውን በደልና ደም መፋሰሰ በብዙ መቶ የሚቆጠሩ የወለጋ ልጆች በህይወት ኑረው ቢመለከቱት ምን ይሉ ይሆን? ወለጋ የኢትዪጵያ ምሁራን፤ ፓይለቶች፤ ሃኪሞች ወዘተ የፈለቁባት ምድር ነበረች። እውቁ ገጣሚና ሃያሲ ሰለሞን ዴሬሳ፤ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን ኸረ ስንቱ ዛሬም በቁም ያሉና ሥራ ጥለውልን ያለፉት የወለጋ ክፍለ ሃገር ተወላጆች ለቁጥር ብዙ ናቸው። በወለጋ ስንት ኢትዮጵያዊ ጀግና ተፈጥሯል። ቤቱ ይቁጠረው!
    በመሰረቱ ኢትዮጵያን መክሰስና ማጥላላትን ለአለም በተለይም ለዓረቡ ስብስብ ያስተዋወቀው ጀበሃ በህዋላም ሻቢያ ነው። ይህን የክፋትና የከፋፍለህ ግዛው ሂሳብ ተቀብሎ የመነዘረው ደግሞ ወያኔ ባርነት ትግራይ ሲሆን ከዚሁ አብራክ የወጣው የድህነቱ መንግስት ደግሞ በሰላም ስም ከኤርትራ በረሃ ያስገባቸው የኦነግና መሰል ታጣቂዎቹ የዘር ፓለቲካውን ጣራ ላይ በመስቀል ባንዲራ አድርገውታል። ሙት ይዞ ይሞታል። የድቤ ጠጥቶ የሰከረና ከፍሎ የሰከረ አንድ ነው። ችግሩ ባለ እዳው በቀኑ ሳይከፍል ሲቀር የሚደርስበት ገመና ነው። ዛሬ የኢትዮጵያን ህዝብ ከውስጥ ሆነው የሚያምሱት በብድር የሚጋቱት ሳይሆኑ ቀን ወቶላቸው በዘራቸው ዙሪያ ሃገሪቱን በማተራመስና በመዝረፍ ላይ ያሉት የክልል ሰካራሞች ናቸው። ጊዜ ግን ሁሉን ይፈርዳል። በታሪክ ያየነው ይህኑ ሃቅ ነው።
    አንድ የወያኔ የዜሮ ስድስት እስር ቤት ጠባቂ የነበረ ያየውን ግፍ ሲመሰክር እንዲህ ብሎአል። አይኔ ብዙ አይቷል። ሰው ግን በሰው ላይ እንዲህ ይጨክናል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር። አሁን በስውር እሥርቤቶችና የማሰቃያ ቦታዎች እውነትን በመናገራቸው ብቻ ታጉረው በቀጠሮ የሚንገላቱትን ሳስብ ይህች ሃገር መዳኛ የላትም እንዲል እገደዳለሁ። እርምጃዋ ከክፋት ወደ ክፋት እንጂ ነገርን የሚያለዝብ ምንም ነገር አይታይም በማለት ተስፋ እቆርጣለሁ። ነገር ግን ተስፋ መቁረጥ ዋጋ ይብሉን። እውቁ ጸሃፊ አቤ ጉበኛ “አልወለድም” በተሰኘው መጽሃፉ ላይ እንደሚነግረን መወለድ በምርጫ አይደለም። “አንዴ ኢትዮጵያዊ/ት ሆነን ተወልደናልና እንበርታ” ኢትዮጵያን የሚያጠለሹ ሃይሎች ሁሉ በወረፋ የእጃቸውን ያገኛሉ። በቃኝ!

  3. ለምዕራባዊያን ራስ ምታት የነበረው ኢትዮጵያዊያን በባዶ እግራቸው ፋሽስት ጣልያን ያሽነፉበት ለአፍሪካ ክብር ለምዕራባዊያን ውርደትን ነበር የድሉም ምክንያት የኢትዮጵያ ህዝብ አንድነት ና ፍቅር ነበር አሜሪካ ይህንን አንድነት ለመሥበር የፋሺሽት ባንዳ የልጅ ልጅ መለስ ዜናዊ በወያኔ ፓርቲ የመጀመሪያው እርምጃ ኤርትራን ማስገንጠል (በአሥገንጣይ ና ተገንጣይ ኦፒሬሽን) እንዲሁም የኢትዮጲያን ህዝብ በዘር የተመሠረተ ፌዴራልዝም መመሥረት ና ህዝቡ በጥላቻ እንድኖር ነበር ።
    ዛሬም የብልጽግና ፓርቲም የአሜሪካን ፍላጎት ከግቡ ለማድረስ በመሳሪያ ሃይል ና በአሜረካ ድጋፍ
    1 _ በከፋ ኑሮ ውድነት ህዝቡን ማደንዘዝ ማዳከም ህዝቡም ተስፋ ቆርጦ እንዲስደድ ።
    2- ኢትዮጲውያንን በዘር ለይቶ በገጠር የጅምላ ጭፍጨፋ ና ከእርሻቸው ማፈናቀል እንዲሁም በከተማ የመኖሪያ ቤቶች አፍሪሶ ማፈናቀል ።
    3- ቤተእምነቶችን ማፍረሥ ና ምዕመናንን መግደል ።
    ይህን አደገኛ ሴራን ለማክሽፍ ይህ ትውልድ በቂ እውቀት ፍላጎት ሞራል ና አንድነት ባለመኖሩ የኢትዮጵያ የወደፊት እድል እንደ ሶማሊያ ና አረብ ሀገሮች ለመበተን የተቃረበች ይመስላል ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

religion 1
Previous Story

በአስከፊ የፖለቲካ ሥርዓት አዙሪት ውስጥ እየጓጎጡ የሃይማኖት ነፃነት ብሎ ነገር የለም!

Ethiopia
Next Story

 የባለአደራ ግዚያዊ የአገር ጉባኤ ይቋቋም!

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop