ይኸ ግድየለሽ ግድያና ጭፍጨፋ፣ ታሪካዊ ቅዱሳት መካናትን ከመድፈርና ከማርከስ ዐልፎ በጦር መሣርያ ማውደም ላንዴና ለመጨረሻ መወገዝና በቃ ማለት ያለበት ጉዳይ ነው

በየማኅበራዊ መገናኛው የምንሰማው እውነት ከሆነ – ሐሰት የሚወራበት ምንም ምክንያት ያለ አይመስለኝም፣ የዐቢይና እሱ የፈጠረው የብልፅግና መንግሥት ከፋሽስቱ ኢጣልያንም የከፋ መሆኑን በተደጋጋሚ አረጋግጧል ማለት ትክክለኛ አገላለጽ መሆኑ የሚካድ አይመስለኝም። ታዲያ እነዚያ “አሁንስ ይብቃ” (No More) እያሉ ይጮኹ የነበሩት አፎች የት ገቡ። “ባዕድ ኀይል በአገራችን ጉዳይ አይግባ” ሲሉ ላንቃቸው እስከሚበጠስ ጮኹ፤ ዓለምንም ከጫፍ እስከጫፍ አነቃነቁ። አሁን ታዲያ ይኸው መንግሥት አገሪቷን በጭፍኑ ሲያጠፋ፣ ሲያወድም፣ ከሩዋንዳ በከፋ እንጂ በማያንስ መልክ ሕዝብን ሲያፈናቅልና ሕፃናትን ለጅብ እራት ሲዳርግ፣ ቅዱሳትንና ታሪካዊ መካናትን አላንዳች ርኅራኄ ሲደመስስ፣ ጆሯቸው ዳባ ለብሶ፣ አፋቸውም ተደፍኖ መቅረቱ ምን ይባላል።

ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው የቤተክርስቲያኒቷ ጳጳሳትስ ለምን ዝምታ መረጡ። በሥልጣናቸው ሲመጣ ብቻ ነው ወይ እሳት ለብሰው፣ እሳት ጐርሰው፣ ምእመናኑን ከጐናቸው አሰልፈው፣ መንግሥትን መግቢያ መውጫ የሚያሳጡት፤ ሰማዕትነትን የሚመኙት። እንዴት አያፍሩም። “ኢትዮጵያዊ እንደመሆኔ የአገሬ ጉዳይ ያገባኛል” ብለው ስለአገራቸውና ስለሃይማኖታቸው በኢጣሊያን ጦር ተኳሽ ቡድን ብርቅ ሕይወታቸውን የሠውት ያ ታላቁ  አቡነ ጴጥሮስ ዛሬ በሕይወት ቢኖሩ እንደነዚህ ዐይነቶቹን አባቶች ምን ይሏቸው ይሁን።
ኢትዮጵያዊ መሆን እጅግ በጣም በሚያሳፍርበት ወቅት ነን ያለነው። የማያፍር ልበደንዳና ካለ፣ ሰው መሆኑ ራሱ አጠራጣሪ ነው ማለት ይቻላል።
ኀይሌ ላሬቦ


ተጨማሪ ያንብቡ:  ቆሜ ነው እምሞተው ( አሥራደው ከካናዳ )

1 Comment

  1. እናመሰግናለን ፕሮፌሰር ህዝባዊ ምሁር የምንለው እንድ እናንተ ያለውን ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share