ይኸ ግድየለሽ ግድያና ጭፍጨፋ፣ ታሪካዊ ቅዱሳት መካናትን ከመድፈርና ከማርከስ ዐልፎ በጦር መሣርያ ማውደም ላንዴና ለመጨረሻ መወገዝና በቃ ማለት ያለበት ጉዳይ ነው

June 2, 2023

genocide 1 1 1

በየማኅበራዊ መገናኛው የምንሰማው እውነት ከሆነ – ሐሰት የሚወራበት ምንም ምክንያት ያለ አይመስለኝም፣ የዐቢይና እሱ የፈጠረው የብልፅግና መንግሥት ከፋሽስቱ ኢጣልያንም የከፋ መሆኑን በተደጋጋሚ አረጋግጧል ማለት ትክክለኛ አገላለጽ መሆኑ የሚካድ አይመስለኝም። ታዲያ እነዚያ “አሁንስ ይብቃ” (No More) እያሉ ይጮኹ የነበሩት አፎች የት ገቡ። “ባዕድ ኀይል በአገራችን ጉዳይ አይግባ” ሲሉ ላንቃቸው እስከሚበጠስ ጮኹ፤ ዓለምንም ከጫፍ እስከጫፍ አነቃነቁ። አሁን ታዲያ ይኸው መንግሥት አገሪቷን በጭፍኑ ሲያጠፋ፣ ሲያወድም፣ ከሩዋንዳ በከፋ እንጂ በማያንስ መልክ ሕዝብን ሲያፈናቅልና ሕፃናትን ለጅብ እራት ሲዳርግ፣ ቅዱሳትንና ታሪካዊ መካናትን አላንዳች ርኅራኄ ሲደመስስ፣ ጆሯቸው ዳባ ለብሶ፣ አፋቸውም ተደፍኖ መቅረቱ ምን ይባላል።

ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው የቤተክርስቲያኒቷ ጳጳሳትስ ለምን ዝምታ መረጡ። በሥልጣናቸው ሲመጣ ብቻ ነው ወይ እሳት ለብሰው፣ እሳት ጐርሰው፣ ምእመናኑን ከጐናቸው አሰልፈው፣ መንግሥትን መግቢያ መውጫ የሚያሳጡት፤ ሰማዕትነትን የሚመኙት። እንዴት አያፍሩም። “ኢትዮጵያዊ እንደመሆኔ የአገሬ ጉዳይ ያገባኛል” ብለው ስለአገራቸውና ስለሃይማኖታቸው በኢጣሊያን ጦር ተኳሽ ቡድን ብርቅ ሕይወታቸውን የሠውት ያ ታላቁ  አቡነ ጴጥሮስ ዛሬ በሕይወት ቢኖሩ እንደነዚህ ዐይነቶቹን አባቶች ምን ይሏቸው ይሁን።
ኢትዮጵያዊ መሆን እጅግ በጣም በሚያሳፍርበት ወቅት ነን ያለነው። የማያፍር ልበደንዳና ካለ፣ ሰው መሆኑ ራሱ አጠራጣሪ ነው ማለት ይቻላል።
ኀይሌ ላሬቦ


Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop