በወቅታዊ ጉዳዮች ከማኅበረ ቅዱሳን ጽ/ቤት የተላለፈ መልእክት!

May 23, 2023
mahbere Kidusan 1 1

ማኅበረ ቅዱሳን በኢ/አ/ተ/ቤ/ን ቅዱስ ሲኖዶሶ በ1984 ዓ.ም እውቅና አግኝቶ በ1994 ዓ.ም በጸደቀለት ሕገ ደንብ መሠረት አገልግሎቱን ሲያከናውን ቆይቷል። በዚህም የቅድስት ቤተክርስቲያን ዐቢይ ተልዕኮ የሆነውን የእግዚአብሔርን ወንጌለ መንግሥት በስፋት ለሕዝበ ክርስቲያኑ ሁሉ እንዲዳረስ በርካታ ሥራዎችን አከናውኗል። በየጊዜው ያጋጠሙትን ፈተናዎችን እግዚአብሔር ቸርነት በከፍተኛ ትጋትና ጽናት ያለፈ መሆኑን ሕዝበ ክርስቲያኑ ሁሉ የሚያውቀው ሀቅ ነው።

ማኅበሩ ካሉት የአገልግሎት ዘርፎች ውስጥ አንዱ የብሮድካስት አገልግሎቱ ሲሆን፤ በ2012 ዓ/ም የተጀመረው ይህ በተለያዩ ቋንቋዎች የሚያሰራጨው የወንጌል አገልግሎት በመላው ምእመን ዘንድ አማራጭ ሚዲያ ከመሆን አልፎ ለመንፈሳዊ ሕይወታቸው የየዕለት ስንቅ በመሆን በሕዝበ ክርስቲያኑ ዘንድ እንደ ዐይን ብሌን የሚጠብቁት ሚዲያ ለመሆን በቅቷል።

የብሮድካስት አገልግሎት ልዩ ጥንቃቄ የሚሻ ሥራ ከመሆኑም በተጨማሪ ማኅበራችን አገልግሎቱን በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜትና መንፈሳዊ ቅኝት የሚያከናውን በመሆኑ ሁሌም ምስጉንና የተከበረ ጣቢያ መሆኑን ምእመናን ሁሉ የሚመሰክሩት እውነታ ነው።

በዚህ መነሻነት በወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ በቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመው ዐቢይ ኮሜቴ ያዘጋጀውን መግለጫ በማስተላለፋችን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም በጻፈው ደብዳቤ “ጊዜያዊ እገዳ” ማድረጉን ገልጾልናል፡፡

ባለሥልጣን መ/ቤቱ ለጊዜያዊ እገዳ የሰጠው ምክንያት ማኅበሩ ከተቋቋመለት ዓለማ ውጭ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

እንኳን ሊያሳግድ ይቅርና ጥያቄ ሊነሳበት የማይገባ ጉዳይ መሆኑን ማኅበሩ ይረዳል። የእግዱ ሂደትም የመገናኛ ብዙኃን አዋጁን ያልተከተለና የሚዲያውን አገልግሎት በጸሎት፣ በገንዘብና በእውቀታችሁ በመደገፍ ሊዚህ ያበቃችሁትን ካህናት፣ ምእመናንና አባላትን ያሳዘነ መሆኑን ተረድተናል፡፡

በመሆኑም እግዱ የምእመናን ድምጽ የሚያፍን ብሎም ትምህርተ ወንጌልን የመማር መብታቸውን የሚገድብ መሆኑን በማሳወቅ ለሚመለከተው አካል አቤቱታውን በደብዳቤ አቅርቧል።

አቤቱታውም በአግባቡና በሕጉ መሠረት ታይቶ በጎ ምላሽ እንደሚሰጠው ተስፋ እናደርጋለን። እንዲሁም ማኅበራችን ጉዳዩ የሕግ አግባብን ተከትሎ ውሳኔ እስከሚያገኝ አስፈላጊውን ሁሉ የሚያደርግ መሆኑን መላው ሕዝበ ክርስቲያን እንዲገነዘብልንና ይህንኑ በየጊዜው በይፋ የምናሳውቅ ስለሆነ በታላቅ ትዕግሥት አንዲጠብቅ እንጠይቃለን።

በዚህ አጋጣሚ መላው ሕዝበ ክርስቲያን ስለ ጉዳዩ በተፈጠረባችሁ ቁጭትና ከፍተኛ የቁጣ ስሜት የቤተክርስቲያንን መብት ለማስከበር ለምታደርጉት ተነሳሽነት ሁሉ በእግዚአብሔር ስም ከፍተኛ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።

በተጨማሪም ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦቱ ርክበ ካህናት ስብሰባ ግንቦት 14/2015 ዓ.ም ባደረገው ምልአተ ጉባኤ ችግር ባለባቸውና አስፈላጊ በሆኑ አኅጉረ ስብከቶች ፱ አዳዲስ ኤጴስ ቆጶሳትን በጥናት ለመሾም አስመራጭ ኮሜቴ መሰየሙ ተገቢ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ የምርጫ ሄደቱም ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን የተከተለ፣ ግልጽነት ያለው፣ ካህናትና ምእመናንን ያሳተፈ እንደሚሆን እንጠብቃለን፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop