April 19, 2023
10 mins read

“እውነቲም ማሞ” ማሞ ምህረቴ ባንዳ ነው ደንቆሮ? (ከ አሁንገና ዓለማየሁ)

ማሞ ምህረቴ 1 1
#image_title
ማሞ ምህረቴ 1 1
#image_title

ይልማ ዴሬሳ ከገንዘብ ሚንስትርነት ተነስተው ማሞ የተባሉ ሰው ተሾሙ ። በኃይለ ሥላሴ ጊዜ ነው። ታዲያ አዲሱ ተሿሚ ኦዲት አድርገው መረከብ እንዳለባቸው በመገንዘብ የቀድሞውና አዲሱ የገንዝብ ሚንስትሮች ስብሰባ ይቀመጣሉ።

ይልማ ዴሬሳ “ሁሉም ስነድ ቀረቦልዎታል። ለእያንዳንዱ ወጪና ገቢ ማስረጃው ሰነድ ተያይዟል። ነገር ግን አንድ ሚሊዮን ተኩል* ብር ንጉሡ በትእዛዝ የወሰኑበት አለ እና እሱን ታሳቢ እንዲያደርጉ” ይሏቸዋል። አቶ ማሞ ኦዲቱን ካስደረጉ በኋላ አቶ ይልማን “አንድ ችግር አለ” ይሏቸዋል።

ይልማ “የምን ችግር?”

ማሞ “የሁሉም ሰነድ ተመሳክሮ ሂሳቡም በትክክል ተወራርዷል። አንድ ተኩል ሚልዮን ብር ግን ሰነድ አልተገኘለትም። ጎድሏል ይሏቸዋል።”

ይልማ “እሱንማ ነገርኩዎት ባለፈው። ንጉሡ ያዘዙበት ነው ብዬ አስቀድሜ የገለጽኩልዎትን ዘነጉት?”

ማሞ “እኔ ማንም ይዘዝበት ብቻ ተፈርሞ የወጣበትን ሰነድ ነው የምፈልገው” ብለው ድርቅ ይላሉ።

ይልማ ዴሬሳም በመገረም እየተመለከቷቸው “እውነቲም ማሞ! ንጉሥ በቃሉ ያዛል እንጂ ከመቼ ወዲህ ነው ገንዘብ እየፈረመ የሚወስደው?” አሏቸው ይባላል።

“7ኛ ንጉሥ** ነኝ” የሚለው 3መቶ ምናምነኛ ንጉሣችንስ በፓርላማ ቀርቦ በቢልዮን የሚቆጠር ዶላር የት እንዳደረስኩት ልትጠይቁኝ አትችሉም ብሎ የለም?

ወደ ዛሬው ነገሬ ልግባና ማሞ ምሕረቴ የተባለ ደንቆሮ አይሉት ባንዳ ኢትዮጵያ የምትፈራርስበትን የመጨረሻ ቁማር ከአይ ኤም ኤፍ ጋር ለመጫወት ቡድን መርቶ አሜሪካ ከርሟል። ለዚሁ ተብሎ በሲአይኤ ማሰልጠኛነት በሚታማው የሃርቫርድ ተቋሙ ‘የኬኔዲ ስኩል ኦፍ ጋቨርመንት’ ተመልምሎ የሰለጠነ እና በWorld Bank ሲሠራ የከረመው ይህ ሰው ማን ነው? ደንቆሮም ሆነ ባንዳ ማሞ ምሕረቴ የጥቃት ዒላማ ያደረጓቸውን ሀገሮች በፖለቲካ ምስቅልቅል ውስጥ አስገብተው በከፍተኛ የኑሮ ቀውስ ጫና ብትንትናቸውን ለማውጣት የብድር ተቋማታቸውን የሚጠቀሙት የምእራባውያንን አጀንዳ ለማስፈጸም ለአሻንጉሊቱ ለአቢይ አህመድ የተሰጠ ታኮ ነው። የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሲሆንም የባንኪንግም ሆነ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ሳይኖረው ነው።

ይኸው ምእራባውያን አቢይና ሕወሃትን በጦርነት አሻኩተው ካንበረከኳቸው በኋላ እጃቸውን በወንጀልና በውድመት ጫና ጠምዝዘው በአዲስ አበባ እጣ አዲሳባንም ኦሮሚያንም  ወክሎ ኦህዴድ እንደተፈራረመው፣ ማሞን ይዘው በኢትዮጵያም በአይ ኤም ኤፍ በኩልም አይ ኤም ኤፍ ተዋዋይ የሆነበት ሁኔታ ተከስቷል

ማሞ ምሕረቴ ባንዳ ካልሆነ ፊደል ቆጠር ደንቆሮ ነው። አይ ኤም ኤፍና ወርልድ ባንክ ምእራባውያን በፖለቲካ ያመስቀሏቸውን ብዙ ሀገሮችን በብድር በተለይም በዲቫልዌሽን ጫና እንዳፈረሷቸው ያላነበበ፣ ያላወቀና ያልተረዳ ፊደል ቆጣሪ መሐይም ነው ማለት ነው። ቼኮስሎቫኪያ፣ ዩጎዝላቪያ፣ ሶቪየት ዮኒየን፣ ሱዳን እና ሌሎችም ብዙ ሀገራት በነዚህ የብድር ተቋማት መሣሪያነት ነው ብትንትናቸው የወጣው ወይም ኢኮኖሚያቸው ድምጥማጡ የጠፋው።

አቢይ በሬው ሆይ ሣሩን አይተህ ገደሉን ሳታይ የሚል ጨዋታ ይጫወታል። እሱን አቢይን ራሱን ግን ጌቶቹ ሣሩን አይተህ ገደሉን ሳታይ ብለው ተጫውተውበት ገደል ጨምረውታል። በኖቤል ሽልማት አሞካሽተው፣ ወያኔን እንዲወጋት አበረታተው፣ ብርድ ብርድ እንዳይለው ኢሳያስን ደርበውለት በጦርና በጄኖሳይድ ወንጀል ካጨማለቁት በኋላ በወዲያ በኩል አይዞሽ ብለው ካዘመቷትና ካስወቀጧት ከሕወሃት ጋር አቆራኝተው ኤርትራን በማፍረስ ሙሉ ቀጠናውን የፈረሱ ሀገራት ክምር ለማድረጉ ዘመቻ ፊታውራሪ እያደረጉት ነው። እምቢ ቢል ደሙን ሲያጎርፈው የከረመው ሕዝብ ካልዋጠው እነሱ ራሳቸው የጦርና የጄኖሳይድ ወንጀሉን አጋልጠው ስቅላት ይፈርዱበታል። አሁን ወጥመዳቸው ውስጥ ገብቷልና እንደ ተያዘች አይጥ ቁልጭ ቁልጭ ከማለት በስተቀር ምርጫ የለውም። የሚታዘዘውን ይፈጽማል።

ተላላኪው አቢይ አህመድ ምእራባውያኑ “ሾክ ቴራፒ”*** የሚባለው የዘረፋ ኢኮኖሚክሳቸው እስኪሳካ ድረስ እለት እለት ጆሮ ጭው የሚያደርግ ቀውስ እየጠመቀ፣ ለዘረፋቸው ከለላ ይሰጣል። ሕዝብ በዚህ የማያባራ ቀውስ ተጠምዶ በሀገር ላይ የሚሠራውን የኢኮኖሚ ደባ፣ የአንጡራ ሃብት ዘረፋ፣ የሀገር ሃብት ባለቤትነት ለባእዳን መተላለፍ የሚያስተውልበት እረፍት እንዳይኖረው አበክሮ ይሠራል። ሁሉም የሕልውና አደጋ ተደቅኖበት በሞት ሽረት መካከል የሚንጠራወዝ ዐይነት ስሜት እየተሰማው ከሄደ ለጋራና ለሀገራዊ ጉዳይ ቁብ ሊሰጥ አይችልም። ቁማሩ ይሄ ነው። አዲስ የሚሞከርብን ኤክስፐሪመንት ሳይሆን ፍቱን መግደያ መሆኑ ታውቆ እንድንውጥ የተፈረደብን መርዝ ነው።

 

*አንድ ሚሊዮን ተኩል በምሳሌነት የተጠቀሰ አሓዝ እንጂ ትክክለኛው ሃምሳ ሚሊዮን ይሁን መቶ ሃምሳ ሚልዮን ጸሐፊው ዘንግቶታል።

**አቢይ አህመድ 7ኛ ንጉሥ ነኝ የሚለው በኦነጋዊው የታሪክ እና የሥነ ፍጥረት እሳቤ ስለሚመራ ነው። “መጀመሪያ እግዚአብሔር ዳግማዊ ምኒልክን ፈጠረ። ከቀኝ ጎኑም እቴጌ ጣይቱን ፈጠረለት። “ የሚለው አይነት። ከዚያ በመቁጠር ነው ከሦስት መቶ በላይ ነገሥታት ተመዝግበው በሚገኙባት ሀገር “7 ኛ ንጉሥ ነኝ” ብሎ የደነቆረው፣ የሚያደነቁረው።

***ሾክ ቴራፒ የዘረፋ ኢኮኖሚክስ ቋንቋ ነው። ሾክ ቴራፒ በሕክምና እና ሲአይኤ በሚያካሂዳቸው የወንጀል ምርመራ ሥራዎች ላይ ይውል የነበረ፣  በኤሌክትሪክ ሾክ የሰውን አእምሮ ክውታና ድንጋጤ ውስጥ በማስገባት አዲስ ትእዛዞችን እና አጠባዎችን እንዲቀበል የሚደረግበት ልማድ ነው። ከዚህ በመነሳት ሚልተን ፊሪድማን የተባለ የዘረፋ ኢኮኖሚክስ ባለሙያ ሀገራትን በመብረቃዊ የሽብርና የደንጋጤ ማእበል በመዝፈቅ ተዘራፊዎቹ በጤናማ ሁኔታ ሊቀበሉት የማይችሉትን ለዘራፊዎቹ ብቻ የሚጠቅም የኢኮኖሚ ውልና ስምምነት መጫን እና ተፈጻሚ የማድረግ ስልት ቀርጿል። ለዚህም የኢኮኖሚክስ ኖቤል ሽልማት ተሸላሚ ተደርጓል።  በዚህ ስልትም ብዙ ሀገሮች ተመዝብረዋል፣ ወድመዋል፣ ብትንትናቸው ወጥቷል።  አምስቱ አመት የአቢይ አህመድ የሽብር፣ የጦርነት፣ የተከታታይ ቀውስ ጠመቃ መርሐ ግብር በግልጽ የሚያመለክተው ያንን የሾክ ቴራፒ ኢኮኖሚክስ ትግብራ በኢትዮጵያ ላይ ተፈጻሚ የማድረግ ጉዞን ነው።

 

https://www.independent.org/news/article.asp?id=46

https://www.peoplesworld.org/article/world-bank-and-international-monetary-fu

https://www.jstor.org/stable/160829

https://tesfanews.net/how-the-world-bank-and-the-imf-destroy-africa/

http://erepository.uonbi.ac.ke/bitstream/handle/11295/60212/Githua_Th

e%20impact%20%20of%20Internat%20(IMF)%20and%20the%20World%20Bank%

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Tplf and Oromo
Previous Story

የብልፅግና እና የህውሃት የእባብ ለእባብ ጉዞ

181963
Next Story

መስታወት-ቀውሱ እንዴት ይቀልበስ?-የዶ/ር ዮናስ ብሩ ማኒፌስቶ Mengizem media

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop