April 19, 2023
10 mins read

“እውነቲም ማሞ” ማሞ ምህረቴ ባንዳ ነው ደንቆሮ? (ከ አሁንገና ዓለማየሁ)

ማሞ ምህረቴ 1 1
#image_title

ይልማ ዴሬሳ ከገንዘብ ሚንስትርነት ተነስተው ማሞ የተባሉ ሰው ተሾሙ ። በኃይለ ሥላሴ ጊዜ ነው። ታዲያ አዲሱ ተሿሚ ኦዲት አድርገው መረከብ እንዳለባቸው በመገንዘብ የቀድሞውና አዲሱ የገንዝብ ሚንስትሮች ስብሰባ ይቀመጣሉ።

ይልማ ዴሬሳ “ሁሉም ስነድ ቀረቦልዎታል። ለእያንዳንዱ ወጪና ገቢ ማስረጃው ሰነድ ተያይዟል። ነገር ግን አንድ ሚሊዮን ተኩል* ብር ንጉሡ በትእዛዝ የወሰኑበት አለ እና እሱን ታሳቢ እንዲያደርጉ” ይሏቸዋል። አቶ ማሞ ኦዲቱን ካስደረጉ በኋላ አቶ ይልማን “አንድ ችግር አለ” ይሏቸዋል።

ይልማ “የምን ችግር?”

ማሞ “የሁሉም ሰነድ ተመሳክሮ ሂሳቡም በትክክል ተወራርዷል። አንድ ተኩል ሚልዮን ብር ግን ሰነድ አልተገኘለትም። ጎድሏል ይሏቸዋል።”

ይልማ “እሱንማ ነገርኩዎት ባለፈው። ንጉሡ ያዘዙበት ነው ብዬ አስቀድሜ የገለጽኩልዎትን ዘነጉት?”

ማሞ “እኔ ማንም ይዘዝበት ብቻ ተፈርሞ የወጣበትን ሰነድ ነው የምፈልገው” ብለው ድርቅ ይላሉ።

ይልማ ዴሬሳም በመገረም እየተመለከቷቸው “እውነቲም ማሞ! ንጉሥ በቃሉ ያዛል እንጂ ከመቼ ወዲህ ነው ገንዘብ እየፈረመ የሚወስደው?” አሏቸው ይባላል።

“7ኛ ንጉሥ** ነኝ” የሚለው 3መቶ ምናምነኛ ንጉሣችንስ በፓርላማ ቀርቦ በቢልዮን የሚቆጠር ዶላር የት እንዳደረስኩት ልትጠይቁኝ አትችሉም ብሎ የለም?

ወደ ዛሬው ነገሬ ልግባና ማሞ ምሕረቴ የተባለ ደንቆሮ አይሉት ባንዳ ኢትዮጵያ የምትፈራርስበትን የመጨረሻ ቁማር ከአይ ኤም ኤፍ ጋር ለመጫወት ቡድን መርቶ አሜሪካ ከርሟል። ለዚሁ ተብሎ በሲአይኤ ማሰልጠኛነት በሚታማው የሃርቫርድ ተቋሙ ‘የኬኔዲ ስኩል ኦፍ ጋቨርመንት’ ተመልምሎ የሰለጠነ እና በWorld Bank ሲሠራ የከረመው ይህ ሰው ማን ነው? ደንቆሮም ሆነ ባንዳ ማሞ ምሕረቴ የጥቃት ዒላማ ያደረጓቸውን ሀገሮች በፖለቲካ ምስቅልቅል ውስጥ አስገብተው በከፍተኛ የኑሮ ቀውስ ጫና ብትንትናቸውን ለማውጣት የብድር ተቋማታቸውን የሚጠቀሙት የምእራባውያንን አጀንዳ ለማስፈጸም ለአሻንጉሊቱ ለአቢይ አህመድ የተሰጠ ታኮ ነው። የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሲሆንም የባንኪንግም ሆነ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ሳይኖረው ነው።

ይኸው ምእራባውያን አቢይና ሕወሃትን በጦርነት አሻኩተው ካንበረከኳቸው በኋላ እጃቸውን በወንጀልና በውድመት ጫና ጠምዝዘው በአዲስ አበባ እጣ አዲሳባንም ኦሮሚያንም  ወክሎ ኦህዴድ እንደተፈራረመው፣ ማሞን ይዘው በኢትዮጵያም በአይ ኤም ኤፍ በኩልም አይ ኤም ኤፍ ተዋዋይ የሆነበት ሁኔታ ተከስቷል

ማሞ ምሕረቴ ባንዳ ካልሆነ ፊደል ቆጠር ደንቆሮ ነው። አይ ኤም ኤፍና ወርልድ ባንክ ምእራባውያን በፖለቲካ ያመስቀሏቸውን ብዙ ሀገሮችን በብድር በተለይም በዲቫልዌሽን ጫና እንዳፈረሷቸው ያላነበበ፣ ያላወቀና ያልተረዳ ፊደል ቆጣሪ መሐይም ነው ማለት ነው። ቼኮስሎቫኪያ፣ ዩጎዝላቪያ፣ ሶቪየት ዮኒየን፣ ሱዳን እና ሌሎችም ብዙ ሀገራት በነዚህ የብድር ተቋማት መሣሪያነት ነው ብትንትናቸው የወጣው ወይም ኢኮኖሚያቸው ድምጥማጡ የጠፋው።

አቢይ በሬው ሆይ ሣሩን አይተህ ገደሉን ሳታይ የሚል ጨዋታ ይጫወታል። እሱን አቢይን ራሱን ግን ጌቶቹ ሣሩን አይተህ ገደሉን ሳታይ ብለው ተጫውተውበት ገደል ጨምረውታል። በኖቤል ሽልማት አሞካሽተው፣ ወያኔን እንዲወጋት አበረታተው፣ ብርድ ብርድ እንዳይለው ኢሳያስን ደርበውለት በጦርና በጄኖሳይድ ወንጀል ካጨማለቁት በኋላ በወዲያ በኩል አይዞሽ ብለው ካዘመቷትና ካስወቀጧት ከሕወሃት ጋር አቆራኝተው ኤርትራን በማፍረስ ሙሉ ቀጠናውን የፈረሱ ሀገራት ክምር ለማድረጉ ዘመቻ ፊታውራሪ እያደረጉት ነው። እምቢ ቢል ደሙን ሲያጎርፈው የከረመው ሕዝብ ካልዋጠው እነሱ ራሳቸው የጦርና የጄኖሳይድ ወንጀሉን አጋልጠው ስቅላት ይፈርዱበታል። አሁን ወጥመዳቸው ውስጥ ገብቷልና እንደ ተያዘች አይጥ ቁልጭ ቁልጭ ከማለት በስተቀር ምርጫ የለውም። የሚታዘዘውን ይፈጽማል።

ተላላኪው አቢይ አህመድ ምእራባውያኑ “ሾክ ቴራፒ”*** የሚባለው የዘረፋ ኢኮኖሚክሳቸው እስኪሳካ ድረስ እለት እለት ጆሮ ጭው የሚያደርግ ቀውስ እየጠመቀ፣ ለዘረፋቸው ከለላ ይሰጣል። ሕዝብ በዚህ የማያባራ ቀውስ ተጠምዶ በሀገር ላይ የሚሠራውን የኢኮኖሚ ደባ፣ የአንጡራ ሃብት ዘረፋ፣ የሀገር ሃብት ባለቤትነት ለባእዳን መተላለፍ የሚያስተውልበት እረፍት እንዳይኖረው አበክሮ ይሠራል። ሁሉም የሕልውና አደጋ ተደቅኖበት በሞት ሽረት መካከል የሚንጠራወዝ ዐይነት ስሜት እየተሰማው ከሄደ ለጋራና ለሀገራዊ ጉዳይ ቁብ ሊሰጥ አይችልም። ቁማሩ ይሄ ነው። አዲስ የሚሞከርብን ኤክስፐሪመንት ሳይሆን ፍቱን መግደያ መሆኑ ታውቆ እንድንውጥ የተፈረደብን መርዝ ነው።

 

*አንድ ሚሊዮን ተኩል በምሳሌነት የተጠቀሰ አሓዝ እንጂ ትክክለኛው ሃምሳ ሚሊዮን ይሁን መቶ ሃምሳ ሚልዮን ጸሐፊው ዘንግቶታል።

**አቢይ አህመድ 7ኛ ንጉሥ ነኝ የሚለው በኦነጋዊው የታሪክ እና የሥነ ፍጥረት እሳቤ ስለሚመራ ነው። “መጀመሪያ እግዚአብሔር ዳግማዊ ምኒልክን ፈጠረ። ከቀኝ ጎኑም እቴጌ ጣይቱን ፈጠረለት። “ የሚለው አይነት። ከዚያ በመቁጠር ነው ከሦስት መቶ በላይ ነገሥታት ተመዝግበው በሚገኙባት ሀገር “7 ኛ ንጉሥ ነኝ” ብሎ የደነቆረው፣ የሚያደነቁረው።

***ሾክ ቴራፒ የዘረፋ ኢኮኖሚክስ ቋንቋ ነው። ሾክ ቴራፒ በሕክምና እና ሲአይኤ በሚያካሂዳቸው የወንጀል ምርመራ ሥራዎች ላይ ይውል የነበረ፣  በኤሌክትሪክ ሾክ የሰውን አእምሮ ክውታና ድንጋጤ ውስጥ በማስገባት አዲስ ትእዛዞችን እና አጠባዎችን እንዲቀበል የሚደረግበት ልማድ ነው። ከዚህ በመነሳት ሚልተን ፊሪድማን የተባለ የዘረፋ ኢኮኖሚክስ ባለሙያ ሀገራትን በመብረቃዊ የሽብርና የደንጋጤ ማእበል በመዝፈቅ ተዘራፊዎቹ በጤናማ ሁኔታ ሊቀበሉት የማይችሉትን ለዘራፊዎቹ ብቻ የሚጠቅም የኢኮኖሚ ውልና ስምምነት መጫን እና ተፈጻሚ የማድረግ ስልት ቀርጿል። ለዚህም የኢኮኖሚክስ ኖቤል ሽልማት ተሸላሚ ተደርጓል።  በዚህ ስልትም ብዙ ሀገሮች ተመዝብረዋል፣ ወድመዋል፣ ብትንትናቸው ወጥቷል።  አምስቱ አመት የአቢይ አህመድ የሽብር፣ የጦርነት፣ የተከታታይ ቀውስ ጠመቃ መርሐ ግብር በግልጽ የሚያመለክተው ያንን የሾክ ቴራፒ ኢኮኖሚክስ ትግብራ በኢትዮጵያ ላይ ተፈጻሚ የማድረግ ጉዞን ነው።

 

https://www.independent.org/news/article.asp?id=46

https://www.peoplesworld.org/article/world-bank-and-international-monetary-fu

https://www.jstor.org/stable/160829

https://tesfanews.net/how-the-world-bank-and-the-imf-destroy-africa/

http://erepository.uonbi.ac.ke/bitstream/handle/11295/60212/Githua_Th

e%20impact%20%20of%20Internat%20(IMF)%20and%20the%20World%20Bank%

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

                                                         ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)                                                       ጥር 12፣ 2017(January 20, 2025) ጆ ባይደን ስልጣናቸውን ለማስረከብ ጥቂት ቀናት ሲቀራቸው በአሜሪካን ምድር በጣም አደገኛ የሆነ የኦሊጋርኪ መደብ እንደተፈጠረና፣ የአሜሪካንንም ዲሞክራሲ አደጋ ውስጥ ሊጥለው እንደሚችል ተናግረዋል።  ጆ ባይደን እንዳሉት በተለይም በሃይ ቴክ

አሜሪካ ወደ ኦሊጋርኪ አገዛዝ እያመራ ነው! ጆ ባይደን ስልጣን ለመልቀቅ ጥቂታ ቀናት ሲቀራቸው የተናዘዙት!!

ከነፃነት ዘገዬ የአራት ኪሎው ኦነግ ሸኔ ከቁጥር ጋር እንደተጣላ ዕድሜውን አገባደደ፡፡ ኦነግ/ኦህዲድ ዛሬም ሆነ ዱሮ፣ በቤተ መንግሥትም ይሁን በጫካ ቁጥር ላይ ያለው አቋም ምን ጊዜም ያስደንቀኛል፡፡ ደግሞም እየባሰባቸው እንጂ ሲቀንሱ አይታዩም፡፡ ጥቂት

80 ቢሊዮን ብር ስንት ብር ነው?

በላይነህ አባተ ([email protected]) መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ ምዕራባውያን የኢትዮጵያን ልጆች እያታለሉና እየደለሉ ከእምነታቸው ለመንጠቅ ሲቃጡ በ1951 ዓ ም ባሳተሙት ‘መድሎተ አሚን ወይም የሃማኖት ሚዛን ጥልቅ መጽሐፍ ሽፋን ላይ ሕዝብ ልቡናውን፣ ዓይኑን፣ ጀሮውንና

ሰው ሆይ!

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

Go toTop