የኤርምያስ ለገሰና የመሳይ መኮንን መንገዶች፤ ቀጣዩ የኤርምያስ እሥሥታዊ እርምጃ

ባቡሩ ወደ መዳረሻው በተቃረበ ቁጥር በየፌርማታው የሚንጠባጠቡት ተሳፋሪወች ቁጥር እየጨመረ ይሄዳል፡፡

ያማራ ሕዝብ የራሱን ሕልውና በማስጠበቅ የኢትዮጵያን ሕልውና ለማስጠበቅ የሚያደርገው የሞት ሽረት ትግል በከፍተኛ ደረጃ እየተቀጣጠለ ነው፡፡  በዚህ ደረጃ መቀጣጠሉን ከቀጠለ ደግሞ ዋናውን የአማራና የኢትዮጵያ ጠላት (ማለትም ጭራቅ አሕመድን) በቅርብ ጊዜ ውስጥ እንደሚያንጨረጭረው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡

በተጨማሪ ደግሞ ያማራ ትግል ይበልጥ በተቀጣጠለ ቁጥር፣ ወላፈኑ ይበልጥ አስመሳይ የነበሩትን ፀራማሮች ይበልጥ ስለሚፈጃቸው ከትግሉ ይሸሻሉ፡፡  ኤርምያስ ለገሰ ያደርገውም ይሄንኑ ነው፡፡  በሌላ በኩል ደግሞ፣ ያማራ ትግል ይበልጥ በተቀጣጠለ ቁጥር፣ ራሱንና ጦቢያን የማዳን እድሉ ይበልጥ እየሰፋ ስለሚሄድ አገር ወዳዶች ትግሉን ይቀላቀላሉ፡፡  መሳይ መኮንን እያደረገ ያለውም ይሄንኑ ነው (በዚሁ እስከቀጠለበት ድረስ)፡፡

ሳይደግስ አይጣላም እንዲሉ፣ ፀረኦሮሙማው ትግል ኤርምያስን አጥቶ መሳይን ካገኘ ደግሞ አትርፏል እንጅ ምንም አልተጎዳም፣ ይበልጥ የሚያተርፈው ሁለቱም የትግሉ አካሎች ቢሆኑ ቢሆንም፡፡

አቶ ኤርምያስ ለገሰ ከኢትዮ360 ራሴን በራሴ አሰናብቻለሁ ብሏል፡፡  እንኳን ተሰናበተ፡፡  በኤርምያስ መሰናበት ደግሞ ኢትዮ360ወች ማለት ያለባቸው ፈረንጆቹ እንደሚሉት እንኳን ተገላገልን (good riddance) ነው፣ የተገላገሉት በመኻላቸው ተሰንቅሮ የነበረው እጅግ አደገኛ ነቀርሳዊ ሰንኮፍ ነውና፡፡

አቶ ኤርምያስ ለገሰ ከኢትዮ360 የለቀቅኩት በማስተላልፈው ዝግጅት ምክኒያት ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ቤተሰቦቸ ስለተቀየሙኝ ነው የሚል፣ ለኢትዮ360 ታዳሚወች ያለውን ከፍተኛ ንቀት በገልፅ የሚያሳይ ተልካሻ ምክኒያት አቅርቧል፡፡  በሌላ በኩል ግን አቶ ኤርምያስ ለገስ በዚህ ተልካሻ ምክኒያቱ የተሳደበው እሱን ራሱን እንዲሁም የገዛ ራሱን ቤተሰቦች ነው፡፡

እንደ ተልካሻ ምክኒያቱ ከሆነ፣ አቶ ኤርምያስ የጭራቅ አሕመድን ወንጀሎች በመዘርዘር የሚያቀርበው ዝግጅት በጭራቅ አሕመድ ደጋፊወች ላይ የሚያሳድረውን ስሜት ቤተሰቦቹ እስኪሚነግሩት ድረስ አያውቅም ነበር ማለት ነው፡፡  ይህ ማለት ደግሞ ኤርምያስ የሚያውቀው መተንተኑን እንጅ፣ ስለ ትንተናውን ውጤት ፍንጭ የለውም ማለት ነው፡፡  ይህ ማለት ደግሞ አቶ ኤርምያስ እውቀቱ ከፊል እውቀት፣ እውነቱ ግማሽ እውነት (half truth) ነው ማለት ነው፡፡  ከፊል እውቀት እና ግማሽ እውነት ያለው ሰው ደግሞ ለሌሎች ብቻ ሳይሆን ለሱ ለራሱም እጅግ አደገኛ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ፍቅራችን የት ገባ? - ከተማ ዋቅጅራ

በሌላ በኩል ደግሞ ጭራቅ አሕመድ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጽመውን ጭፍጨፋና ማፈናቀል ሳያሰለስ በሚያጋለጠው በኢትዮ360 ውስጥ በመሥራቱ የኤርምያስ ቤተሰቦች ኤርምያስን ከተቀየሙት፣ ቤተሰቦቹ የጭፍጨፋውና የማፈናቀሉ ተሳታፊወች ወይም ደጋፊወች ወይም አትራፊወች ናቸው ማለት ነው፡፡  ይህ ማለት ደግሞ የኤርምያስ ቤተሰቦች የኦሮሙማ አቀንቃኝ ኦነጋውያን ናቸው ማለት ነው፡፡  የኦነጋውያን ቤተሰቦቹን ወቀሳ ሰምቶ ኢትዮ306ን ከለቀቀ ደግሞ እሱም ራሱ የኦሮሙማ አቀንቃኝ ኦነጋዊ ሁኗል ማለት ነው፡፡

የቆየ ልማድ በዋዛ አይወገድ (old habits die hard) እንዲሉ፣ ኤርምያስ የወያኔ ጉዲፈቻ ስለሆነ፣ ከወያኔ የወረስው አለቅጥ ማጋነን እንዲሁም አለልክ መዋሸት ጨርሶ እንዳልለቀቀው የኢትዮ360 ታዳሚወች በደንብ ያውቃሉ፡፡  ስለዚህም አቶ ኤርምያስ ኢትዮ360ን ለመልቀቁ ተልካሻ ምክኒያት ማቅረቡ እንደለመደበት መዋሸቱ ነው፡፡

አቶ ኤርምያስ ኢትዮ360ን የለቀቀው ኢትዮ360ን አዳክሞ የማጥፋት ልዩ ተልእኮ አንገቦ ነው፡፡  ተልእኮውን ከከፍተኛ ገንዘብ ጋር የሰጠው ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ መለስ ቀለስ የሚለው አቶ ታከለ ኡማ ነው፡፡  አቶ ኤርምያስ ኢትዮ360ን አዳክሞ ለማጥፋት ያሰበው ደግሞ ጭራቅ አሕመድ አማራን አዳከሞ ለማጥፋት እየተጠቀመበት ባለው ዘዴ ነው፡፡  ዘዴው ደግሞ የሚከተለው ነው፡፡

አቶ ኤርምያስ አቶ ታከለ ኡማ የሰጠውን ገንዝብ በመጠቀም በሁሉም ረገዶች የተሟላ፣ ደረጃውን የጠበቀ፣ ቆንጆ እስቱዲዮ በቅርብ ጊዜ ይከፍታል፡፡  የሚዲያውን ሥራ ማስኬጃ ደግሞ የጭራቅ አሕመድ መንግስት በየጊዜው ፈሰስ ያደርግለታል፡፡  ከዚያም የኢትዮጵያዊነት አቀንቃኞች ነን የሚሉትን አማራ ጠሎችን (ልደቱ አያሌው፣ ታምራት ላይኔ፣ ያሬድ ጥበቡቴድሮስ ፀጋየ ወዘተ. ) በተደጋጋሚ እየጋበዘ በማር የተለወሰ መርዝ ላማራ ሕዝብ በየዕለቱ ይመግባል፡፡  ይሄን የሚያደርገው ግን የኢትዮ360 ታዳሚወችን ወደሱ በመሳብ ኢትዮ360ን ለማዳከም ሲል ብቻ ነው፡፡  እንዳሰበው ኢትዮ360ን ካዳከመ ደግሞ ግቡን ስለመታና ተልእኮውን ስለጨረሰ እውነትኛ ማነነቱን ገሃድ አውጥቶ ፀራማራነቱን በግለፅ ያውጃል፡፡  ጭራቅ አሕመድ አማራን አዳክሚያለሁ ብሎ በማሰቡ አሁን ላይ ፀራማራነቱ በግልፅ እንደተናገረ፣ ኤርምያስም ኢትዮ360ን ማዳከም ወይም ጨርሶ ማፍረስ ከቻለ ጊዜው ሲደርስ ኦነጋዊነቱን በግልፅ ይናገራል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የመሐል ሀገር ሰው መልዕክት ለትግራይ ሰው! (በፍቃዱ ኃይሉ)

ስለዚህም ኢትዮ360ን የምትወዱ የኢትዮ360 ታዳሚወች ሆይ፣ ከቀጣዩ የኤርምያስ ለገሰ እሥሥታዊ እርምጃ ተጠንቀቁ፡፡  ያማራና የኢትዮጵያ ሕልውና የሚያስጨንቃችሁ አገር ወዳዶች ደግሞ ታከለ ኡማ ለኤርምያስ የሚከፍትለትን ፀራማራና ፀረጦቢያ ሚዲያ ባንድም በሌላም መንገድ በመደገፍ ያማራንና ያገራችሁን ሞት እንዳታፋጥኑ ትመከራላችሁ፡፡  ባንድ ወቀት አቶ ኤርምያስ በውጭ አገር የባልደራስ ተወካይ ስለነበር፣ በአስክንድር ነጋ ላይ ይህ ሁሉ መከራ የደረሰበት አንዱ ምክኒያት አሁን ላይ ገልፅ ሊሆንላችሁ ይገባል፡፡

ኢትዮ360ወች ደግሞ በበኩላችሁ ሁለት ነገሮችን አድርጉ፡፡  በመጀመርያ ደረጃ የኢትዮ360 የመረጃ ምንጮችን ኤርምያስ እንዳያጋልጣቸውና ለጭራቅ አሕመድ አሳልፎ እንዳይሰጣቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ አድርጉ፡፡  በተለይም ደግሞ ኤርምያስ ከኢትዮ360 ኮምፒተሮች ላይ ማህደሮችን (files) እንዳያወርድ (download) ከኮምፒተሮቹ አጠገብ አታስደረሱት፡፡  በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ የኤርምያስ ለገሰ ግርፎች አሁንም በመካከላችሁ ስላሉና በደንብ ስለሚታወቁ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርሱ ባስቸኳይ ሸኟቸው፡፡

የኢትዮ360ና የመሰሎቹ ሚዲያወች እልህ አስጨራሽ ኢትዮጵያዊ ትግል፣ በኢትዮጵያዊነቱ በማይደራደረው ባማራ ሕዝብ ላይ ፍሬ አፍርቶ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እያቃረበ ነው፡፡  ባቡሩ ወደ መዳረሻው በተቃረበ ቁጥር ደግሞ በየፌርማታው የሚንጠባጠቡት ተሳፋሪወች ቁጥር እየጨመረ ይሄዳል፡፡  ትናንት ኤርምያስ፣ ነገ ደግሞ ….

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.com

 

10 Comments

  1. I didn’t know the time but I was very sure about Ermias from beginning. I never gave him my heart at all. And he is also not knowledgeable guy as many believes. He is like having a political target and a hate to amhara is in his blood. Now everyone is going to where they belong. To their respective camps.

  2. ፕሮፍ ተማሪህ ብሆንም ኤርምያስ ላይ ያለኝ ምልከታ ትንሽ ይለያል፡፡ በእርግጥ አንዳንድ ትንታኔው ላይ የግሉ ሃሳብ ነው ብዬ የዘለልኩዋቸው ነበሩ ለምሳሌ የልዩ ክልል ተብሎ ኦነግ የሚፈነጭበትን የአማራ ክልል እንዳይፈርስ ወጥሮ ሲከራከር ስምቼ ግር ብሎኝ ነበር ዳግም ህዝቅኤል ጋቢሳ በሚመራው ስብሰባ ላይ ልጃችን መጣ አይነት አቀባበልንም ሲያደርጉ ተመልክቻለሁ ለርእዮቱ ቴዎድሮስም ስስ ልብ እንዳለው እገምታለሁ፡፡ ይህን ካልኩ በኋላ ሃብታሙም ጋር ተጠባብቀውና ተናንቀው ነው ያሉት በዚህ ሁኔታ 360 ቤት ጫና በዝቶብኛል ቢል ሊደመጥ ይገባል፡፡
    ትላንት እንዳልኩት ሁሉ ኤርምያስ የወያኔን ጀርባ በመስበር ያደረገው አስተዋጽዎ ጉልህ ነው ያን መካድ አይቻልም፡፡ በእርግጥ እውር ድምበሩ የጠፋውን የኦሮሙማን ፐሮጀክትም እንደዛው ቢያነክትልን መልካም ነበር አብይ አህመድን ወደ ፊት ከሚኖርበት እድሜም ጭምር አስልቶ አበጥሮ ነግሮናል ነገር ግን ካሁን በኋላ አብይ ኬኛ ይላል ብዬ አልገምትም፡፡ አብይ ግን ከጌታቸው በላይ የሰደበው ስለሌለ ነገ ኤርምያስ ፊቱን ቢያዞርለት በደስታ ጁዋር አጠገብ ኮንዶሚኒየም ነገር ሰጥቶ እንደ ዳንኤል ክብረት መሳቂያ ያደርገዋል ኤርምያስ ግን የሚጨበጥለት አይመስለኝም፡፡
    ቀደም ባለው ጊዜ በግምቦት 7 የተመዘዘብትን ሰይፍ በርብርብ ወደ ቦታው መልሰነዋል አሁንም ኤርምያስ ኢትዮ 360 ውስጥ ያደረገውን እሰጥ አገባ እንደ አማራ ሳይሆን እንደግለሰቦች ወስዶ በቀሉንም ሆነ እንካ ስላንትያውን ወደ ሌላ ሳያዞረው እውቀቱና ልምዱን ኢትዮጵያ ውስጠ የሚታረደውን ዜጋ ቢታደገው መልካም ነው እላለሁ፡፡ ለነገሩ ትርፉ ትዝብት ይሆናል እንጅ አንድ ሰው በኛ ፖለቲካ ብዙም ፋይዳ ሊያመጣም አይችልም፡፡ በተለይም እንደ ኤርምያስ በህይወት አጋጣሚ ችግር የበዛበት ካሁን በኋላ እንቅስቃሴው ላይ ልዩ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባዋል፡፡ እሱም ካምፑን ከለወጠ ድሮም አመሉ ነው ከማለት ውጭ መንገዶቹ ሁሉ የተመቻቹ አይሆኑለትም፡፡
    ስለዚህ ኤርምያስ የብሽሽቅ ፖለቲካ ሳይሆን ያለፈውን ረስቶ የእውቀት ጋዜጠኝነትና የእውነት ፖለቲካ ቢያደርገው ክብሩ ይጨምራል የሚል ግምት አለኝ፡፡ ነገር ግን ላሳርራቸው ብሎ ተስቦ ወይ ወደ ወያኔ፡ ወደ ቴዎድሮስ ወይ ወደነ ጁዋር ቢሄድ የተሰጠውን እድል እንዳበላሸ ፖለቲከኛ ተቆጥሮ ሚዛኑ የሚቀል ይመስለኛል፡፡ በዛም አለ በዚህ ኤርምያስ ከጅምሩ ጀምሮ ባገለገለበት ቤት እዚህ እርምጃ ላይ ከመድረሱ በፊት አዋቂ ሰዎች በመሃከላቸው ስላሉ በውይይት ቢፈቱት መልካም ነበር ኤርምያስም ወገን በመሆኑ እንዲጎዳ አንፈልግም ኢትዮጵያን እስካልጎዳ ድረስ፡፡ እንግዲህ ከውጭ እውቀታችን ውስን ስለሆነ ከዚህ በላይ ማለት አንችልም እንደገና ተመልሶ በትብብር አብረው እንደሚሰሩ ግን እምነታችን ጽኑ ነው በአንድ የሳይበር የጦር ሜዳ ወድቀዋልና፡፡

  3. አማራነትህን የተጠራጠርኩበት ጊዜም ነበር ይህን ውሸታም ጠሚ አምኜ ስለእሱ በመከራከሬ ይቅርታ እጠይቃለሁ:: ሁሉም ጊዜውን ጠብቆ ይባንናል:: ጠሚ ና የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት አማራጠልነት ከህውሀት ተግተው ነው ያደጉት ይህ ባይለቃቸው አስገራሚ አይሆንም:: አሁን አብዛኛው ህዝብ ነቅቷል:: የቀረው የተበተነውን ድምፅ ማሰባሰብና ማደራጀት ነው:: አማራው ለጥቃት የተጋለጠው ባለመድራጀቱ ነው:: አንድነት ሀይል ነው

    • እውነቱ ጸጸት ገብቶህ ተመልሻለሁ ካልከን ደህና አንዴ ፕሮፌሰሩን አንዴም እኔን እንዳልነበርን አድርገህ ጭቃ ለውሰህን ነበር እኛም ወይ ትንሽ አበል ቆርጠውለት ነው አልያም በእውቀት የተጎዳ ቢሆን ነው ብለን ቂም አልያዝንም ነበር ።እንግዲህ ልቦናህን ከፍቶት ባንዱም ይሆን በሌላ ወደ ተጎጅው ህዝብ ከመጣህ ባጠፋኸው ልክ መካስ ይጠበቅብሀል።

      • ወንድሜ ተፅፅቻለሁ እኔ እንኳ አበል ለመቀበል አልመችም:: ከኢትዮጵያ የምፈልገው ህዝቡ ተቻችሎ እንዲኖር ነው::ይህን ከሀዲ ሰውዬው ባለማወቄ ከራሴ ወንድም ጋር ተጣልቼ አሁን ይቅር ተባብለናል:: ለአማራ ትግልም አዲስ አይደለሁም ለዶክተር አስራት መአህድ ትንሽም ቢሆን ሞክሬ ነበር ሆኖም ኢትዮጵያዊው በአማራነት መደራጀት አልፈለገም እነሆ የዚያን ውጤት አየነው ያሁኑ ትውልድ ያኔ ቢደርስ ኖሮ ታሪክ ይለወጥ ነበር አሁንም አልረፈደም:: የተበተነው አማራ ተገዶም ቢሆን ይደራጃል ይመክታል ያሸንፋልም:: በርቱ አማራ እውነትን ስለያዘ ህልውናውን ያስጠብቃል

  4. ኤርምያስ ለገሰ ዋቅጅራ ልክ አብይ አህመድ ከታወቀበት ቀዳዳነቱ በመነጨ ብልግና መቀሌን “በሻሻ አድርጌታለሁ” ብሎ እንደተቀደደና አሁን መልሶ እንደ ዉሻ “ወደ ትፋቱ” እንደተመለሰ ሁሉ አጭቤውና የበረከት ስሞኦን ግርፍ የሆነውም ኤርምያስ ለገሰ ወያኔንና ኦሮሙማን እንደ አንድ ክፍለ ጦር ሆኖ ስለኢትዮጵያዊነት ሽንጡን ገትሮ የሚታገለውን ኢትዮ 360 ሜድያን”በሻሻ አድርጌዋለሁ” ብሎ ሊፎክር ይችል ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ግለሰቡ በአንድ መልኩ የተጠላውና የተተፋው በብዙ መቶ ሽህወች በሚቆጠሩ ኢትዮ 360ን በየእለቱ በሚከታተሉ የሜድያው ደጋፊወችና ታዳሚወች ስለሆነና በሌላ መልኩ ደግሞ የኦሮሙማው ታከለ ኡማ ወያኔ ለኤርምያስ ይወረውርለት ከነበረው ልቅቃሚ ሳንቲሞች በተሻለ መጠን ዳጎስ ያለ ገንዘብ ስለሰጠው ነው፡፡
    ኤርምያስ አንድም የኢትዮ 360 ዝግጅት ላይ የተጣራና በቂ የሆነ በተለይም በመረጃና በማስረጃ የተጠናከረ ዘገባና ትንተና ሲሰጥ አይታወቅም፡፡ኤርምያስ የሚታወቀው “አጠቃቀስኩ” ሲል ነው፡፤ ወያኔንና ኦሮሙማን በሾርኔ ደግፎ ሲቆም ነው፡፡ምሁር ለመምሰል ሲጣጣር አንዳንዴ ማኖ እስከመንካትም ይደርሳል፡፡ ፣ “..ያ ደራሲ…” …ወዘተ “”ይህ ቻፕተር”” ምናምን እያለ ያደናግራል፡፡
    እውነትን እውነት ሀሰትን ደግሞ ሀሰት ማለት አግባብ ነው፡፤ ሀብታሙ አያሌውን የሚጠሉትም አሉ፡፤ እነርሱም እነዚያው የወያኔ ርዝራዦችና የኦሮሙማ መንጋወች ናቸው፡፡ በቁጥር ግን ትንሽ ናቸው፡፡ ደጋግመው ደጋግመው ስድቦቻቸውን post ስለሚያደርጉ ብዙ ሊመስሉ ይችላሉ፡፡ ስራዬ ብለው ስድብ ላይ የተጠመዱ ናቸው፡፤ በእውነትም ስራቸውም ነው፡፤ ይከፈላቸዋልኮ፡፡ ሀሳብን ሳይሆን የሚተቹት ስበእናን ማንነትን ነው፡፡
    ከሜድያው ኢትዮጵያ የሚልን ቃል ሲሰሙ የሚያማቸው የወያኒ ርዝራዦችና የኦሮሙማ መንጋወች ሳይሆን የኢትዮጵያዊያን ነው፡፡
    ስለዚህ ኤርምያስ ኢትዮ 360ን በመልቀቁ የብዙወቻችን ፍላጎት ስለነበረ እሰየው ነው፡፡ ኢትዮ360 እየጠነከረና ብረት ለበስ እየሆነ አንዱ በቃኝ ሜድያ እንዲሆን እኛ ሚሊዮኖች ከጎኑ ቆመናል፡፡ በኢትዮጵያ ነጻ ፣ ጠንካራና አንዲነቷ የተጠበቀ አገር መሆን የምናምንና እንዲትሆንልንም የምንታገል ሚሊዮኖች ኢትዮጵያዊያን ከሜድያው ጎን እንቆማለን፡፤

  5. በመጀመሪያ ሰዎች የራሳቸውን ሃሳብ ማቅረብ መብታቸው ነው በማስቀጠል ማንም ሰው አታድምጠው አትከተለው ሊለኝ አይችልም ሃሳቡ ጥሩ ከሆነ እወስደዋለሁ ካልሆነም እተወዋለሁ :: በተረፈ የራሱን መክፈት አይደለም የትም ቢገባ ምንም አያገባኝም ጥሩ ሃሳብ ካለው አሰማለሁ::

  6. ኢትዮ 360 የምገባው ከእየሩሳሌምና ሃብታሙ በተጨማሪ ከኤርሚያስ ውጭ ያሉት ሁሉም በሚባል ደረጃ አቀነባብረው ሲያቀርቡት ፍሬ ነገሩን ለመሥማት ነው፡፡ንግግራቸውም ቁም ነገር አለው፡፡
    ኤርምያስ ሲናገር ግን ሌላ ሥራ ነው የምሠራው፡፡አንድም ቀን ንግግሩ ጥሞኝ አያውቅም፡፡”ቢቸግር”እያልኩ የምጠራው ሰው ነው፡፡
    ኢትዮ 360!ኤርምያስን ከተገላገለ ይበልጥ ይጠናከራል እንጅ አይዳከምም፡፡ለምን ቢባል የኤርምያስ ጮርቃ ትንተናና ከልቡ ያልመነጨ የለብለብ ንግግሩና አካሄዱ እንዲሁም እንደአቢይ አህመድ ሁሉን አዋቂ መሥሎ ለመታዬት የሚያደርገው አሥመሳይነት ብዙ ሰዎችን ያሸሻል፡፡
    እኔ ኢትዮ 360ዎችን ብሆን ፣ይህ ወደኋላ ጎታች ሰው በገዛ ፈቃዱ ሲሄድ “እንኳን ተገላገልን” ብላችሁ በውሥጣችሁ ደሥታን መሰነቅ ነው የሚገባችሁ፡፡ “ባቄላ አለቀ ቢሉት ክ. አረፍኩ” እንዳለው ነው፡፡አሁን ደግሞ ጀግናውንና ደፋሩን ምናላቸው ሥማቸውን አግኝታችኋል፡፡ወደፊት መግፋት ነው፡፡ በርቱ!

  7. አያሌው ፈንቴ ወንድማችን ሰላምህ ይብዛ ያላችሁን እናንተ ናችሁ እዚህማ መላ ጠፍቶናል፡፡ የመጨረሻው አማራ እስኪጠፋ እነ አብይ እረፍት የላቸውም፡፡ እንደው ወደ ግብጽ ድምበር ስምሪት ቢሰጡህ ባረቀበኝ ብለህ አስዋንን ብታናግረው ያው ያንተው ወንዝ ነው የሞላው ተጠያቂም አትሆንም እነሱ ናቸው አንዱ ሰላም የነሱን፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share