April 2, 2023
3 mins read

በኦሮሚያ ክልል የተደረገው ሰልፍ እንደውም የዘገየ ነው

በተያዙት መፈክሮች እንደተገለፀው ጠቅላይ ሚኒስትሩን ወይም የብልፅግና ስርሃትን አሻግሮናል፤ እንደግፋለን ነው።
ይሄ ስርዓት እኮ!

339104097 524369569848574 3581751921323049074 n 1 1 1

  •   ኢሬቻውን በደብረዘይት ማክብር የተቸገረ ከነበረ አልፎ አዲስ አበባ ድረስ አርቴፊሻል ሀይቅ ሰርቶ እንዲያከብር የካሰ ስርዓት ነው፣
  •   ለውጥ ስለጠየቀ ይታሰር ከነበር ወደ አሳሪነት የቀየረ ስርዓት ነው፤
  •    በወያኔ ተዘቅዝቆ ይገርፈው የነበረ ኦሮሞ ዘቅዝቆ እንዲሰቅል የፈቀደ ስርዓት ነው፤
  •   ኦሮሞ ያልሆኑትን ገድሎ ንብረት ሲያቃጥል በጠሚር ገና ጥቅሙን መቼ አስከበረ ተብሎ ያሞገሰ ስርዓት ነው፤
  •   ኦነግ ጥይት ጠሽ አድርጎ ጫካ መሮጥ ከነበረበት ዘመን እንደጫጩት እንዲጨፈጭፍ የፈቀደ ስርዓት ነው፣
  •   ከባንክ ጠባቂነት ወደ ባንክ ዘራፊነት የቀየረ ስርዓት ነው፣
  •   በቋንቋው መናገር ይሸማቀቅ ከነበረ ወደ እፃናት በግዳጅ ቋንቋውን እንዲማሩ ያደረገ ስርዓት ነው፤
  •    ከኦሮሞ ውጪ የሆነ ጋዜጠኛ እና አክቲቪስት እስከ ዶክተር እና ጀነራል እያፈነ አስሮ በድብደባ እያሰቃየ የካሰ ስርዓት ነው።
  •   ኦሮሞ አይደሉም ያሏቸውን መኖሪያ ቤት በስካቫተር እየናደ ቤት አልባ ያደረገ ስርዓት ነው፤
  •   ይሄ ስርዓት እኮ ለህክምና ከሀገር ለመውጣት ቋንቋ መናገርን መስፈርት ያደረገ ነው፤
  •   ይሄ ስርዓት እኮ ከተፈናቃይነት ወደ አፈናቃይነት የቀየረ ስርዓት ነው።
  •   መታወቂያ በማደል ሲቭል ሰርቪሱን የአንድ ብሄር ከለር የቀየረ ስርዓት ድጋፍ ማድረግ ቢያንሰው እንጂ አይበዛበትም።
❓❗ ችግር የሚሆነው የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ ሌላው ሲረገጥለት ለመደሰት ነበር ወይ የሚል ጠያቂ ሲመጣ ነው።
❓❗ ችግር የሚሆነው በዚህ መልኩ የአንድ ሀገር ህዝቦች መሆን እንችላለን ወይ የሚል ጠያቂ ኦሮሞ ሲመጣ ነው።
❓❗ ችግር የሚሆነው ተበቃይ ትውልድ እየተፈጠረ መሆኑን ማሰቢያ ሲያሰፋልን ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

የኦህዴድ መራሹ ብልፅግና  መንግስት  በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል በንጹሀን  ዜጎች ላይ እየወሰዳቸው ያሉ የነፃ እርምጃ  ግድያዎች  መንግስት ያሰበውን የፖለቲካ ግብ ያሳካለታል  ወይ ? በኔ አመለካከት እነዚህ የንፁሃን ዜጎች  የጅምላ ግድያዎች  በሁለት በኩል እንደተሳለ ቢላዎ (double edge sword) ናቸው:: ፩- መንግስት እያሰላው

 የኦህዴድ መራሹ ጅምላ ግድያዎች ስሌት (ሸንቁጥ- ከምዕራብ ካናዳ)

January 24, 2025
እነዶ/ር ደብረፅዮን እና በጠ/ሚ ዐብይ አህመድ በተሾሙት የትግራይ ጊዜያዊ መንግሥት መሪዎች እነጌታቸው ረዳ መካከል የነበረው አለመግባባት ተካርሮ ሰራዊቱን ወደውግንና አስገብቷል። የትግራይ ሐይል አዛዦች ትላንት ባወጡት መግለጫ ውግንናቸው ከእነዶ/ር ደብረፅዮን ጋር መኾኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ የተፈጠረው ምንድነው?

January 23, 2025
የድሮ መሪዎች ያላደረጉትን ምሁር ጳጳሳቱ ያላስተዋሉትን ከፈረሰች ጎጆ ከባልቴት ቤት ገብቶ ክብሩን ዝቅ አድርጎ ውሀዋን ጠጥቶ ምግቧንም ተጋርቶ ያላለቀሰ ሰው ያንን ትይንት አይቶ ማን ይኖራል ከቶ? በዉሸት ፈገግታ ፊቱን አስመስሎ ፀሀይ የበራበት

ሰው በሰውነቱ – ከ ይቆየኝ ስሜ

Go toTop