ከታሪክ ማህደር: ፀሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ (ጠ/ሚኒስቴር)

ለሀገራቸው ከሰሩት ዓበይት ሥራዎች መካከል በጥቂቱ….

▻ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረኮች ተገቢውን ውክልናና ጥቅም እንድታገኝ ያደረጉት ተጋድሎና ጀብድ ቀን በባቡር ፣ ሌሊት በመርከብ እንዲሁም በአውሮፕላን ያለእረፍት ለበርካታ ቀናት እየተጓዙ የኢትዮጵያን ጥቅም ለማስጠበቅ ደክመዋል፡፡

▻ ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረራ ወቅት ባደረሰችው ጉዳት ካሳ ልትከፍል ይገባል ብለው በመከራከር በጊዜው ጥቁሮች እንደሰው በማይታዩበት ጊዜ በአውሮፓ የአለም መሪዎች ስብሰባ ላይ እሳቸው ብቻ ጥቁር በስብሰባው ላይ ተገኝተው ለኢትዮጵያ የሚከፈላት የካሳው ብር 5 ሚሊዮን ዶላር ነው ፤ ተብሎ ቢወሰንም ክቡር አክሊሉ ግን እንደዛ እንደማይሆን በውሳኔው እንደማይስማሙና በመሟገታቸው የክፍያው የብሩ መጠን ወደ 25 ሚሊየን ዶላር ከፍ እንዲል አድርገዋል።

▻ ገና በወጣትነታቸው በዓለም መንግሥታት ማኅበር (League of Nations) የኢትዮጵያ ዋና ጸሐፊ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን ፤ በአፋምቦ ፣ ኦጋዴን፣ ጋምቤላና ኤርትራን ጨምሮ በርካታ የኢትዮጵያ ግዛቶች በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ከነበሩ ቅኝ ገዢ አገራት ግዛትነት ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ አድርገዋል።

▻ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የእንግሊዝ መንግስት ያቀረበው ድርድር ወድቅ አድርገው የራሳችን ብሔራዊ ባንክ ባለቤት እንድንሆን አድርገዋል።

የእንግሊዞች ሀሳብ የነበረው ባንኩ መቀመጫውን በለንደን ይሆናል የባንኩ አስተዳደሮች በእንግሊዝዋ ንግስት ይመረጣል ኢትዮጵያ ወርቁን ትልካለች ከዛ ተመርቶ ይላክላቸዋል ሲሉ ጀግናው አክሊሉ ሀ/ወለድ ግን “እኛ የራሳችን ባንክ እዚሁ አ/አ እንዲሆን ነው ምንፈልገው ንግስቲቷ በኛ ባንክ ሰራተኞች መራጭ ማን አደረጋቸው እኛ የናንተ ቀኝ ተገዢዎች አይደለንም” በማለት ተከራክረው በማሸነፍ ኢትዮጵያ የራሷን ገንዘብ አምራች አድርገዋታል።

▻ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለመፍጠር በተሰሩ ታላላቅ ስራዎችና ተቋማት ምስረታ በብዙው መስኮች የተሳተፉ ሲሆን በግንባር ቀደምትነት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምስረታ ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአቶ ቡልቶ ኤጄርሳ ስኬታማ ቤተሰብ ታሪክ

▻ እኚህ ታላቅ ዲፕሎማት ኢትዮጵያን በአለም አቀፍ መድረኮች ላይ የአገራቸውን ብሄራዊ ጥቅም ከማስጠበቅ ባሻገር ከነ ዶ/ር ምናሴና ክቡር ከተማ ይፍሩ ጋር በነበራቸው ጥምረት የአፍሪቃ አንድነት ድርጅትንም በመመስረት በሀገራችን ውጪ ጉዳይ ታሪክ የምንጊዜም ወርቃማው ዘመን ሆኖ በታሪክ እንዲታወስ ታላቁን ሚና ተወጥተዋል።

ፀሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ (ጠ/ሚ)

መጋቢት 5 ቀን 1904 — ህዳር 13 ቀን 1967 ዓ.ም

ክብርና ዘላለማዊ እረፍት ለፀሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀ/ወልድ

#ታሪክን_ወደኋላ

 

https://youtu.be/E7nnEf2SFzM

ክብርና ዘላለማዊ እረፍት ለፀሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀ/ወልድ በፎቶ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share