February 28, 2023
5 mins read

አድዋ እና “አንድ ወጥ” አከባበር -ሸንቁጤ – ከካናዳ

Adwa 11ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር  የዘንድሮው 127 የአድዋ ድል በአል “አንድ ወጥ ”  በሆነ መልኩ እንዲከበር  በቂ ዝግጅት አድርጎ  እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ አሳውቋል:: 

“አንድ ወጥ ” የሚለው  የባህልናስፖርት ሚኒስቴር ዝግጅት በትግባር ሲተረጎም-

  1. ለበአሉድምቀት በሚዘጋጀው ፖስተር  ላይ  የዳግማዊ  አፄ ምንሊክን ፎቶ አስቀርቶ  በምትኩ በትግራይ ክልል የወታደርነት ዘመኑ የሚያውቁት ጌቶቹ እንደነገሩን በኢትዮ -ኤርትራ  ጦርነት ወቅት ጏዶቹ  የተጣለባቸውን ወታደራዊ ግዳጅ ሲወጡ እርሱ ግን ከበሻሻ እስከ መቀሌ ድረስ  የዘለቀ የ ከሰል እሳት ማርገብገቢያ ሽያጭ ንግድ  ሲያጧጡፍ የከረመ  በዚህም የተነሳ  የመቀሌ ጌቶቹ”መሽረፈት” እያሉ የሚያላግጡበትን ምኩን  በምትኩ በአድዋ ድል መታሰቢያ ፖስተር ላይ ፎቶው እንዲታተም ማድረግ
  2. የዳግማዊአፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ  ምስሎች የታተሙባቸው አልባሳትን የሚሸጡ ሱቆችንና ማሸግ እና መዝረፍ
  3. የዳግማዊአፄ ምኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱን ምስል የሚያትሙ   ማተሚያ ቤቶችን ማስፈራሪያ እና ማስጠንቀቂያ  መስጠት እና ማሸግ
  4. የዳግማዊአፄ ምኒልክ  እቴጌ ጣይቱ እናየኢትዮጵያ  ባንዲራ  የታተመባቸውን አልባሳትም ሆነ አርማዎች ይዘው የተገኙ  ዜጎችን ማሰር…( እስካሁን ወደ 50 የሚጠጉ ታስረዋል..)
  5. የቴዲ አፍሮ  ” ጥቁር ሰው”  ሙዚቃ በመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንዳይጫወት ክልከላ መጣል
  6. ወደ400 የሚጠጉ  ሆድ አደር  መድረክ እና ወረት( ብር) የተጠሙ አርቲስቶችን ሰብስቦ  ምኒሊክ እና የጣይቱ ስም  እንዳይነሳ አስምለው  ቃለ ተውኔት መቼት  ገፀ ባህሪያት አልቦ ቲያትር ማሰራት  ወ.ዘ.ተ….

ጥያቄ  ለባህልና ስፖርት ሚኒስቴር

ጋሽ  መርዳሳ  እነዚህን መፈፀም ይችሉ ይሆን

  1. የአድዋንጦርነት እና የዳግማዊ አፄ ምኒሊክ/  እቴጌ ጣይቱን ሚና  የዘገቡ  በአለም ዙሪያ የተበተኑ የታሪክ መዛግብትን ሰብስቦ ማቃጠል ይቻል ይሆን
  2. የታሪክምሁራን እና ተመራማሪዎችን አፍ መለጎም ደብዛቸውን ማጥፋትስ
  3. የዳግማዊ አፄ ምንሊክን እና እቴጌ ጣይቱን ታሪክ  ከህዝቡ ልብ መፋቅ እና ማጥፋት ይሞከር ይሆን

ጋሽ መርዳሳ እና አጋሮቻቸው ለ ኢትዮጵያ  እና  ኢትዮጵያውያን ካላቸው “ልዩ ፍቅር”  የተነሳ ይህን ከመሞከር እንደማይታክቱ አምናለሁ::

ይልቅስ ጋሽ መርዳሳን ላመስግን ! እድሜ ለርስዎ እና ለጥረትዎ  የታሪክ መፃህፍቶቻችንን ከየወሸቅንበት እና ከጣልንበት እያወጣን በወጉ አራግፈን እና ጠርዘን  ለልጆቻችን  ውርስ እንድናስቀምጥ ስላነቁን እጅግ እናመሰግናለን! እንዴ ያኛው  ሎሌዎ  እኮ “ስንሞት ኢትዮጵያ…” እያለን ሸማችንን ተከናንበን ተኝተን ነበር:: አሁን እርሶ ባይኖሩ ማን ይቀሰቅሰን ነበር?!

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

ጥር 2 ቀን 2017 ዓ/ም   January 10, 2025  በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡ ቤተ ሰብ፡ ወዳጅ ዘመዶቻችሁን ያጣችሁ: ልጆቻችሁን የቀበራችሁ፡ አካልችሁን ያጣችሁ፡ የተሰነዘረውን ብትር በመከላከል ላይ ያላችሁ፡ያለፈቃዳችሁ በመንግሥት ተጽእኖ ወደመግደልና

በኢትዮጵያዊነታችሁ፡ በኦርቶዶክሳዊ እምነታችሁ፡ በአማራነታችሁ፡ በአማረኛ ተናጋሪነታችሁ፡ በተሰነዘረባችሁ ብትር፡

January 10, 2025
Go toTop