አድዋ እና “አንድ ወጥ” አከባበር -ሸንቁጤ – ከካናዳ

ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር  የዘንድሮው 127 የአድዋ ድል በአል “አንድ ወጥ ”  በሆነ መልኩ እንዲከበር  በቂ ዝግጅት አድርጎ  እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝ አሳውቋል:: 

“አንድ ወጥ ” የሚለው  የባህልናስፖርት ሚኒስቴር ዝግጅት በትግባር ሲተረጎም-

  1. ለበአሉድምቀት በሚዘጋጀው ፖስተር  ላይ  የዳግማዊ  አፄ ምንሊክን ፎቶ አስቀርቶ  በምትኩ በትግራይ ክልል የወታደርነት ዘመኑ የሚያውቁት ጌቶቹ እንደነገሩን በኢትዮ -ኤርትራ  ጦርነት ወቅት ጏዶቹ  የተጣለባቸውን ወታደራዊ ግዳጅ ሲወጡ እርሱ ግን ከበሻሻ እስከ መቀሌ ድረስ  የዘለቀ የ ከሰል እሳት ማርገብገቢያ ሽያጭ ንግድ  ሲያጧጡፍ የከረመ  በዚህም የተነሳ  የመቀሌ ጌቶቹ”መሽረፈት” እያሉ የሚያላግጡበትን ምኩን  በምትኩ በአድዋ ድል መታሰቢያ ፖስተር ላይ ፎቶው እንዲታተም ማድረግ
  2. የዳግማዊአፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ  ምስሎች የታተሙባቸው አልባሳትን የሚሸጡ ሱቆችንና ማሸግ እና መዝረፍ
  3. የዳግማዊአፄ ምኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱን ምስል የሚያትሙ   ማተሚያ ቤቶችን ማስፈራሪያ እና ማስጠንቀቂያ  መስጠት እና ማሸግ
  4. የዳግማዊአፄ ምኒልክ  እቴጌ ጣይቱ እናየኢትዮጵያ  ባንዲራ  የታተመባቸውን አልባሳትም ሆነ አርማዎች ይዘው የተገኙ  ዜጎችን ማሰር…( እስካሁን ወደ 50 የሚጠጉ ታስረዋል..)
  5. የቴዲ አፍሮ  ” ጥቁር ሰው”  ሙዚቃ በመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንዳይጫወት ክልከላ መጣል
  6. ወደ400 የሚጠጉ  ሆድ አደር  መድረክ እና ወረት( ብር) የተጠሙ አርቲስቶችን ሰብስቦ  ምኒሊክ እና የጣይቱ ስም  እንዳይነሳ አስምለው  ቃለ ተውኔት መቼት  ገፀ ባህሪያት አልቦ ቲያትር ማሰራት  ወ.ዘ.ተ….

ጥያቄ  ለባህልና ስፖርት ሚኒስቴር

ጋሽ  መርዳሳ  እነዚህን መፈፀም ይችሉ ይሆን

  1. የአድዋንጦርነት እና የዳግማዊ አፄ ምኒሊክ/  እቴጌ ጣይቱን ሚና  የዘገቡ  በአለም ዙሪያ የተበተኑ የታሪክ መዛግብትን ሰብስቦ ማቃጠል ይቻል ይሆን
  2. የታሪክምሁራን እና ተመራማሪዎችን አፍ መለጎም ደብዛቸውን ማጥፋትስ
  3. የዳግማዊ አፄ ምንሊክን እና እቴጌ ጣይቱን ታሪክ  ከህዝቡ ልብ መፋቅ እና ማጥፋት ይሞከር ይሆን

ጋሽ መርዳሳ እና አጋሮቻቸው ለ ኢትዮጵያ  እና  ኢትዮጵያውያን ካላቸው “ልዩ ፍቅር”  የተነሳ ይህን ከመሞከር እንደማይታክቱ አምናለሁ::

ይልቅስ ጋሽ መርዳሳን ላመስግን ! እድሜ ለርስዎ እና ለጥረትዎ  የታሪክ መፃህፍቶቻችንን ከየወሸቅንበት እና ከጣልንበት እያወጣን በወጉ አራግፈን እና ጠርዘን  ለልጆቻችን  ውርስ እንድናስቀምጥ ስላነቁን እጅግ እናመሰግናለን! እንዴ ያኛው  ሎሌዎ  እኮ “ስንሞት ኢትዮጵያ…” እያለን ሸማችንን ተከናንበን ተኝተን ነበር:: አሁን እርሶ ባይኖሩ ማን ይቀሰቅሰን ነበር?!

 

ተጨማሪ ያንብቡ:  በኢትዮጵያዊያ የመሳፍንት ዘመን አጭር ታሪክ

3 Comments

  1. Soon Mekelakeya Minstir may also be asked to be the supreme oversee r of the celebration of Meskel and Id Al Fatr festivals. When Ethiopians from all walks of life, not just soldiers, paid the ultimate sacrifice at Adwa for the survival of Ethiopian independence, why would an institution that was not present at the time take oversight of the people’s victory?
    A one-man military dictatorship that stifles all facets of social life is in the making. We should not accept that. People should be free to celebrate this legacy of their ancestors in the best manner they see fit without being humiliated by elites that feel humiliated by the anti-colonial victory (on behalf of their ‘masters’).

  2. በምኒልክ ታሪክ በገድሉ ብትቀና
    እያንገሸገሸህ ትኖራለህ ገና
    ነጭን ድል አድርጎ ነጻነት ያጸና
    ሌላ አፍሪካዊ አልነበረምና

  3. ቀጀላ መርዳሳ፤ሽመልስ አብዲሳ፤መራራ ጉዲና፤ እንዲሁም ሌሎች ባንዳዎችና የባንዳ ልጆች እንኳን ለአድዋ አደረሳችሁ ምንሊክ በአድዋ ያንን ገድል ባይሰሩ ስማችሁ ቀጀላም ሮቤርቶ ዳውድም አንቶኒዎ፤ ሺመልስም ፒኮሎ፤ በያን ሱጳም ኔግሮ ፤ ስብሃት ነጋም ሳልቪኖ እየተባላችሁ በጌቶቻችሁ ስም ትጠሩ ነበር የአባ ጅፋር ልጆች ደግሞ የአረብ ስም ይዛችሁ ማንነታችሁ ይቀየር ነበር ያለመቀየራችሁ አበሳጭቷችኋል ችግራችሁ ይገባናል የባንዳነት ታሪካችሁ እረፍት ስለነሳችሁ አዲስ አገር አዲስ ትርክት በመፍጠር እይተጣደፋችሁ ነው

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share