February 28, 2023
4 mins read

ታሪክን ለባለታሪኩ፤ በተደረገበት ቦታ፤ በተፈጠመበት ቀን!! (አሥራደው ከፈረንሳይ)

adwa 2በዚች አጭር ጽሁፌ ፤ የቀደምት የግሪክ ታሪኮች ( Classical mytology) ስለ ሔርኩል (Hercule)  በተጠቀሰች አጭርና ውስጠ ወይራ በሆነች ጥቅስ መንደርደር መረጥኩ :: 

« On ne se baigne jamais deux fois dans le même fleuve »

« በአንድ ወንዝ አንድ ጊዜ እንጂ፤ ሁለት ጊዜ አንጠመቅም  » ይላል

ይህን ጥቅስ እንድዋስ ያስገደደኝ፤ በኢትዮጵያ የዘንድሮውን የ127ኛ የአድዋ ድል በዓል አከባበር፤ በተመለከተ፤ የሚደረገውን የታሪክ ሸፍጥ፤ « ተረኞች ነን » ባዮቹን፤ ህዝብ አደብ ግዙ እንዲላቸው ለማሳሰብ ነው ::

ታሪክ፤ በአድራጊውና በተደራጊው መሃል፤ በአንድ ወቅት፤ በተወሰነ ቦታና : በተወሰነ ጊዜ፤ በበጎ ወይም በጎጂ መልኩ፤ በአሸናፊና በተሸናፊ መሃል የሚደረግ ግብ ግብ ሲሆን፤ በመጨረሻም በመኖር ወይም ባለመኖር መሃል ይቋጫል::

የአድዋ ድል፤ በእምዬ ምኒልክና እተጌ ጣይቱ  አዝማችነት፤ በኢትዮጵያ ህዝብ ጀግንነት፤ በወራሪው የጣሊያን ፋሽስት ላይ፤ የተገኘ የአብሮነታችን ድል ከመሆኑም በላይ፤ የመላው አፍሪካ የጥቁር ህዝቦች ድል እንደሆነ ሊታወቅ ይገባል ::

የዘመኑ የዘርና የጎሣ ፖለቲከኞች፤ የአድዋን ድል ከኢትዮጵያዊነት ማማው ለማውረድ፤ ከመሬት ስበት በከፋ መልኩ ቁልቁል ወደታች በመጎተት፤

 

ያለ ድሉ ባለቤቶች፤ እምዬ ምንሊክ፤ እተጌ ጣይቱና ጀግኖቻችን፤

ያለ ቦታው፤ የአድዋ ድል አደባባይ  ፊት ለፊት፤

ያለ አብሮ ዘማች ታቦቱ፤ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን

ያለ ሰንደቅ ዓላማችን፤ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለሙ፤  እንዲከበር ወስነዋል ::

አይምሯቸው፤ በዘርና በጎሣ ከታጠረ ግለሰቦች፤ ማህበረሰ’ባዊም ሆነ አገራዊ ዕሳቤ ስለማይመነጭ፤  አብሮነትን በሚያቀጭጭ፤ ክብርን በሚያጎድፍ፤ ታሪክን በሚከልስ ሁኔታ፤ እንዲከበር የወሰኑትን አጠፊዎች፤ ህዝብ በአንድነት እንዲጠየፋቸው አደራ እላለሁ ::

እግረ መንገዴንም፤ በእስር ለሚጉላሉት :

– ጋዜጠኛና የታሪክ ምሁር፤ ጋሼ ታዲዎስ ታንቱ፤

– በአዲስ አበባ አካባቢና በአማራ ክልል፣ ለሚፈናቀሉ ወገኖቻችን፤

– የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ተከታይ ለሆኑት ወገኖቻችን፤

– ለአርበኛ ዘመነ ካሴና፤ ለመላው የፋኖ አባላት ፍትህን እጠይቃለሁ ::

 

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

ነፃነት፤ እኩልነትና ወንድማማችነት ይለምልም !!

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ህዝቧን ይባርክ !!

የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ.ም  (28/02/2023) እኤአ

 

ባቡሩም ሰገረ ስልኩም ተናገረ
ምኒልክ መልዐክ ነው ልቤ ጠረጠረ
ምኒሊክ የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ፈር ቀዳጅ
332336598 3629627227271315 6505558082944763049 n

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop