በቁማችሁ እናሞኛችሁ ዓይነት ተራ ብልጠት – ከመሳይ መኮንን

የዘንድሮ ደግሞ ይለያል። ያፈጠጠ፥ ያገጠጠ፥ በቁማችሁ እናሞኛችሁ ዓይነት ተራ ብልጠት የተሞላበት፡ እብደትና እብሪት የተቀላቀሉበት አካሄድ ነው። ጄነራል አበባው ታደሰ ‘አጼ ሚኒሊክና እቴጌ ጣይቱን የማይፈልግ የህብረተሰብ ክፍል አለ’ ብለው ሲናገሩ ጆሮዬን ማመን ነው ያቃተኝ። የማይፈልግ የፖለቲኞችና የልሂቃን ስብስብ መኖሩ ጠፍቶኝ አይደለም። ከእሳቸውና ከቆሙለት ተቋም አንጻር ተገቢ አነጋገር መስሎ ስላልታየኝ ነው

በኦሮሚያ ክልል አስተባባሪነት በተዘጋጀውና ሚኒስትሩ አቶ ቀጄላ መርዳሳ በተገኙበት በተካሄደ የአድዋ በዓል ምክክር ላይ የመከላከያ አባላት የሆኑ ባለማዕረግ መኮንኖች የሚሰጡት አስተያየት አረ!? በህግ አምላክ!’ የሚያሰኝ ነው።

ታዋቂው ጸሀፊ ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ በቲያትር ቤቶች ስለአድዋ አከባበር እየተደረገ ያለውን ዝግጅት አስመልክቶ ያካፈለን መረጃ ደግሞ በድንጋጤ ቅንድብን ከፍ የሚያደርግ ነው። ቴዎድሮስ እንደሚነግረን በቲያትር ቤቶቹ ለአድዋ በሚዘጋጀው ተውኔት ላይ አጼ ሚኒሊክና እቴጌ ጣይቱ እንዳይኖሩ ከበላይ ትዕዛዝ ተሰጥቷል። ይህ ሁሉ መዓት ምንድን ነው? የምን ጥድፊያ ነው? ይህቺ ሀገር ላያችሁ ላይ እንዳትናድ እሰጋለሁ

እውነት ለመናገር የዚህ አገዛዝ መልክ ዘንድሮ ግልጥልጥ ብሎ ወጥቷል። አንድ የኦሮሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ከብልጽግና መንግስት ጋር ተስማምተው ለመስራት ሀገር ቤት እንደገቡ የተናገሯት አሁን እየተፈጸመች ናት ‘We need to deconstruct Ethiopia to reconstruct a new Ethiopia’ በግርድፉ ሲተረጎም አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት አሁን ያለችዋን ማፍረስ ይገባል ነው። የቀድሞ ሚዲያ ኢሳት እያለሁ የኦሮሚያ ብልጽግና ከፍተኛ አመራር የሆኑትና የፓርቲው የፍልስፍና መሀንዲስ ከሚባሉት ውስጥ የሚጠቀሱ ሰው ያሉኝን እዚህ ማስታወስ ይገባል። ‘የእናንተ ኢትዮጵያ እኛ(ብልጽግና) ከምንገነባት ኢትዮጵያ የሰማይና የምድርን ያህል ትራራቃለች’ ነበር ያሉኝ

ተጨማሪ ያንብቡ:  በፊት የበቀለን ጅራት በዃላ የበቀለ ቀንድ በለጠው! - አገሬ አዲስ

የእኛ ኢትዮጵያ የቷ ናት? የእኔ ኢትዮጵያ ማን ናት? ብልጽግና ሊያዋልዳት የሚያምጣት ኢትዮጵያስ ምን ዓይነት ናት? ሌላም ልጥቀስ። ከዚሁ ከኦሮሞ ፖለቲከኞች አንዳቸው ‘ላለፉት 3ሺህ ዓመታት ስልጣን በሰሜኖች እጅ ነበር። አሁን ወደ ደቡብ መጥቷል’ ሲሉ ሰምቼአለሁ። እንግዲህ መጪውን 3ሺህ ዓመት ታግሳችሁ ጠብቁ ማለታቸው ነው

ዘንድሮ የሚታየው አይን ያወጣ የታሪክ ግድፈት የዚሁ ‘deconstruct’ ኢትዮጵያ ሂደት አካል መሆኑ ነው። እዚህ አሜሪካ ከአገዛዙ ጋር ውርውር የሚሉ አንድ ምሁር አግኝቼአቸው ”አሁን ኢትዮጵያ የምትባለው ‘ፕሮጀክት’ ላይ መነጋገርና ስምምነት ላይ መድረስ አለብን” ሲሉኝ የእኔ አባት ”ኢትዮጵያ ፕሮጀክት አይደለችም። የደም ዋጋ የተከፈለባት ናት” የሚል ወኔ የተሞላባት ምላሽ ሰጥቼአቸው በቶሎ ተለየኋቸው

እናም የኦሮሞ ፖለቲከኞችና ምሁራን በስልጣን ላይ ካለው አገዛዝ ውጭ እስከተበተነው ድረስ ተናበው በአንድ ነገር ላይ ተስማምተው እየሰሩ ለመሆናቸው ብዙ አስረጂ አብነቶችን መጥቀስ ይቻላል። ያለችውን ኢትዮጵያ አፍርሶ፡ እነሱን የምትመስል ‘ኢትዮጵያ’ ን ለመገንባት የሚመስል ጥድፊያ ላይ ናቸው። ኢትዮጵያን በነጠላ ትምህርተ ጥቅስ ውስጥ ያስገባኋት ስያሜዋ ላይ በራሱ ድርድር እናደርጋለን የሚሉ የኦሮሞ ልሂቃን ስለገጠሙኝም ነው

እንግዲሁ ብልጽግና ይህን አደጋ ከፊታችን ደቅኗል። የኦሮሞ ብልጽግና ታንኩንና ባንኩን ተቆጣጥሬአለሁ ዓይነት መታበይ ውስጥ ዘው ብሎ ገብቶ ሀገር የሚያፈርሱ ትርክቶችን ወደ አደባባይ አውጥቷል። እንደጥድፊያቸው ሳይዘጋጁ ኢትዮጵያ ላያቸው ላይ እንዳትናድ እሰጋለሁ

አጼ ሚኒሊክና እቴጌ ጣይቱ ላይ የተጀመረው ዘመቻ የሚነግረን ሌላ ምንም አይደለም። ሸገር በሚል ተመሰረተ የተባለው ከተማ ምን ፈንጂ እንደተቀበረበት ያልተገለጠለት ካለ በጊዜ ሀኪሙ ጋር ይሂድና ጤናውን ይፈትሸው። በየቦታው የሚታየው ማፈናቀል ምን ድግስ ከፊታችን እንደተደገሰልን ያልተገለጠለት ካለም በአቅራቢያው ያለ ጸበል ሄዶ ሁለት ሰባት ይጠመቅ። እናም ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጥልቅ የሆነ ችግር ውስጥ ገብታለች”

ተጨማሪ ያንብቡ:  እያመመን መጣ! - በቦቆቅሳ ሉባክ

4 Comments

  1. አይ መሳይ “በየቦታው የሚታየው ማፈናቀል ምን ድግስ ከፊታችን እንደተደገሰልን ያልተገለጠለት ካለም በአቅራቢያው ያለ ጸበል ሄዶ ሁለት ሰባት ይጠመቅ።” አልክና አረፍከው፡፡ እግዚኦ ህሊና ጨርሶ ገደል ገባ!

    አንተና ጓደኞችህ ላለፉት 5 ኣመታት በአማራ ሕዝብ ላይ የሰራችሁን ግፍ አንኳን ሁለት ሰባት 700 ጊዜ ብትጠመቁም አያፀዳችሁም፡፡ ሙሴ መጣ እያላችህ ቅጠል እንደ ፈጀ ፍየል ልፍልፋችሁ ለዚህ ሁሉ ግፍ አበቃችሁ፡፡ ግድ የለም አማራ ይነሳል፡፡ ይፋረዳችሁል፡፡

  2. አይ ወታደር ይሄ ነው ወታደር ፡፡አብይንስ ሁሉ ሰው የሚፈልገው ይመስልሃል? ወያኔ መለመላችሁ ወያኔ ቀረጻችሁ ብሄራዊ አንድነት የሚባል ውስጣችሁ የለም፡፡ ስትናገሩም ትግሉ ውስጥ በነበርንበት ጊዜ ትላላችሁ የናንተ ትግል የነበረው ኢትዮጵያዉያንን እየገደላችሁ በወያኔ መሪነት ስልጣን ላይ ወጥታችሁ አገር ማጥፋት ነው፡፡ እናንተ እንዲህ ከወታደር ተግባር ዝቅ ስትሉ እኛም በዛው ልክ የማይታወስውን እናስታውሳችኋለን፡፡ ይህንን ካልን በኋላ የወታደር ተግባር ስሩ እንላለን ወታደር መሪው በስልጣን ያለው ሳይሆን ሃገሩ ነው መሪ ይሸሻል፤ይከዳል፤ይሞታል፤ይገደላል ሃገር ግን ጥሩ ወታደሮች ካሏት ሃገር ሁና ትቀጥላለች፡፡ ወታደር ለባለጌ መሪዎች አሽከር ከሆነ ግን ክብር የሌለው ወታደር ተብሎ በታሪክ ሲላገጥበት ይኖራል መሪው ሲሄድም የመጀመሪያው ተጠያቂ ይሆናል፡፡ ሲጀመር በአብረሃም በላይ የሚመራ የመከላከያ ድርጅት ባልኖረ ነበር አብረሃም በላይ ከህወአት ከፍታ ዝቅ አላለም አርከብ እቁባይም ህወአት ሁኖ ነው የኖረው እናንትን ግን ምን እንደነካችሁ አናውቅም ወታደር ወታደር አልሸት ብላችሁናል፡፡ ተዋርዶ ከመኖር አሳምነውን ሁኖ መሞት ክብር ነው፡፡ አሳምነው በህዝቡ በሳር በቅጠሉ ልብ ውስጥ ነው ያለው፡፡ ዘረኞች ምንሊክን ስለጠሉ፤የአድዋ ቂመኞች ምንሊክን ስለጠሉ፤ባንዳና የባንዳ ልጆች ምንሊክን ስለጠሉ ምንሊክ ከታሪክ ይፋቁ? ያሳዝናል ከአንድ ከኢትዮጵያ ወታደር እንዲህ ያለ አስተያየት ሲሰነዘር እኔ ግን ጄነራሉ ደፍሮ ይህን የሚናገር አይመስለኝም፡፡አረ ጄነራል አበበ ጨመዳ በህይወት አሉ ግር ካላችሁ አነጋግሯቸው፡፡

  3. መሳያችን፦
    መጀመሪያ እንኳን ከአብይ አህመድና በርሀኑ ነጋ ወጥመድ ራስህን ነጻ አውጥተህ ወድህዝብህ ተመልልሰህ ተቀላቀልክ፡፡ ደፋር ነህ፡፡ አሁን በትክክል ለአገርህና ለህዝብህ ቆመሀል፡፡ ፈጣሪ አምላክ መንገድህን ያቅናልህ፡፡
    አገራችን ከመጥፎወቹ የወያኔና የኦሮሙማ ፖለቲከኞች የተጣመረ ሴራ ወጥታ ያ ገራምና ያ የዋህ ህዝብ ራሱ በመረጣቸው ሰወች ሲተዳደር ላማየት ያብቃን፡፡ እንወድሀለን!!!

    • ብርሀኑን አንዳርጋቸው ዳግም ካልጠለፉት አሁን ደህና ይዟል ሲሳይ አጌና ነው አገኘሁ እሱ ነው መላ ቅጡን ያጣው

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Share