February 27, 2023
6 mins read

በቁማችሁ እናሞኛችሁ ዓይነት ተራ ብልጠት – ከመሳይ መኮንን

General Abebaw Ethiopia 2የዘንድሮ ደግሞ ይለያል። ያፈጠጠ፥ ያገጠጠ፥ በቁማችሁ እናሞኛችሁ ዓይነት ተራ ብልጠት የተሞላበት፡ እብደትና እብሪት የተቀላቀሉበት አካሄድ ነው። ጄነራል አበባው ታደሰ ‘አጼ ሚኒሊክና እቴጌ ጣይቱን የማይፈልግ የህብረተሰብ ክፍል አለ’ ብለው ሲናገሩ ጆሮዬን ማመን ነው ያቃተኝ። የማይፈልግ የፖለቲኞችና የልሂቃን ስብስብ መኖሩ ጠፍቶኝ አይደለም። ከእሳቸውና ከቆሙለት ተቋም አንጻር ተገቢ አነጋገር መስሎ ስላልታየኝ ነው

በኦሮሚያ ክልል አስተባባሪነት በተዘጋጀውና ሚኒስትሩ አቶ ቀጄላ መርዳሳ በተገኙበት በተካሄደ የአድዋ በዓል ምክክር ላይ የመከላከያ አባላት የሆኑ ባለማዕረግ መኮንኖች የሚሰጡት አስተያየት አረ!? በህግ አምላክ!’ የሚያሰኝ ነው።

ታዋቂው ጸሀፊ ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ በቲያትር ቤቶች ስለአድዋ አከባበር እየተደረገ ያለውን ዝግጅት አስመልክቶ ያካፈለን መረጃ ደግሞ በድንጋጤ ቅንድብን ከፍ የሚያደርግ ነው። ቴዎድሮስ እንደሚነግረን በቲያትር ቤቶቹ ለአድዋ በሚዘጋጀው ተውኔት ላይ አጼ ሚኒሊክና እቴጌ ጣይቱ እንዳይኖሩ ከበላይ ትዕዛዝ ተሰጥቷል። ይህ ሁሉ መዓት ምንድን ነው? የምን ጥድፊያ ነው? ይህቺ ሀገር ላያችሁ ላይ እንዳትናድ እሰጋለሁ

እውነት ለመናገር የዚህ አገዛዝ መልክ ዘንድሮ ግልጥልጥ ብሎ ወጥቷል። አንድ የኦሮሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ከብልጽግና መንግስት ጋር ተስማምተው ለመስራት ሀገር ቤት እንደገቡ የተናገሯት አሁን እየተፈጸመች ናት ‘We need to deconstruct Ethiopia to reconstruct a new Ethiopia’ በግርድፉ ሲተረጎም አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት አሁን ያለችዋን ማፍረስ ይገባል ነው። የቀድሞ ሚዲያ ኢሳት እያለሁ የኦሮሚያ ብልጽግና ከፍተኛ አመራር የሆኑትና የፓርቲው የፍልስፍና መሀንዲስ ከሚባሉት ውስጥ የሚጠቀሱ ሰው ያሉኝን እዚህ ማስታወስ ይገባል። ‘የእናንተ ኢትዮጵያ እኛ(ብልጽግና) ከምንገነባት ኢትዮጵያ የሰማይና የምድርን ያህል ትራራቃለች’ ነበር ያሉኝ

የእኛ ኢትዮጵያ የቷ ናት? የእኔ ኢትዮጵያ ማን ናት? ብልጽግና ሊያዋልዳት የሚያምጣት ኢትዮጵያስ ምን ዓይነት ናት? ሌላም ልጥቀስ። ከዚሁ ከኦሮሞ ፖለቲከኞች አንዳቸው ‘ላለፉት 3ሺህ ዓመታት ስልጣን በሰሜኖች እጅ ነበር። አሁን ወደ ደቡብ መጥቷል’ ሲሉ ሰምቼአለሁ። እንግዲህ መጪውን 3ሺህ ዓመት ታግሳችሁ ጠብቁ ማለታቸው ነው

ዘንድሮ የሚታየው አይን ያወጣ የታሪክ ግድፈት የዚሁ ‘deconstruct’ ኢትዮጵያ ሂደት አካል መሆኑ ነው። እዚህ አሜሪካ ከአገዛዙ ጋር ውርውር የሚሉ አንድ ምሁር አግኝቼአቸው ”አሁን ኢትዮጵያ የምትባለው ‘ፕሮጀክት’ ላይ መነጋገርና ስምምነት ላይ መድረስ አለብን” ሲሉኝ የእኔ አባት ”ኢትዮጵያ ፕሮጀክት አይደለችም። የደም ዋጋ የተከፈለባት ናት” የሚል ወኔ የተሞላባት ምላሽ ሰጥቼአቸው በቶሎ ተለየኋቸው

እናም የኦሮሞ ፖለቲከኞችና ምሁራን በስልጣን ላይ ካለው አገዛዝ ውጭ እስከተበተነው ድረስ ተናበው በአንድ ነገር ላይ ተስማምተው እየሰሩ ለመሆናቸው ብዙ አስረጂ አብነቶችን መጥቀስ ይቻላል። ያለችውን ኢትዮጵያ አፍርሶ፡ እነሱን የምትመስል ‘ኢትዮጵያ’ ን ለመገንባት የሚመስል ጥድፊያ ላይ ናቸው። ኢትዮጵያን በነጠላ ትምህርተ ጥቅስ ውስጥ ያስገባኋት ስያሜዋ ላይ በራሱ ድርድር እናደርጋለን የሚሉ የኦሮሞ ልሂቃን ስለገጠሙኝም ነው

እንግዲሁ ብልጽግና ይህን አደጋ ከፊታችን ደቅኗል። የኦሮሞ ብልጽግና ታንኩንና ባንኩን ተቆጣጥሬአለሁ ዓይነት መታበይ ውስጥ ዘው ብሎ ገብቶ ሀገር የሚያፈርሱ ትርክቶችን ወደ አደባባይ አውጥቷል። እንደጥድፊያቸው ሳይዘጋጁ ኢትዮጵያ ላያቸው ላይ እንዳትናድ እሰጋለሁ

አጼ ሚኒሊክና እቴጌ ጣይቱ ላይ የተጀመረው ዘመቻ የሚነግረን ሌላ ምንም አይደለም። ሸገር በሚል ተመሰረተ የተባለው ከተማ ምን ፈንጂ እንደተቀበረበት ያልተገለጠለት ካለ በጊዜ ሀኪሙ ጋር ይሂድና ጤናውን ይፈትሸው። በየቦታው የሚታየው ማፈናቀል ምን ድግስ ከፊታችን እንደተደገሰልን ያልተገለጠለት ካለም በአቅራቢያው ያለ ጸበል ሄዶ ሁለት ሰባት ይጠመቅ። እናም ኢትዮጵያ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጥልቅ የሆነ ችግር ውስጥ ገብታለች”

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Latest from Blog

“በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢአተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ።”  መዝሙረ ዳዊት 39:1 ወንድሙ መኰንን፣ ኢንግላንድ 15 January 2025 መግቢያ የአገር መሪ፣ በስሜታዊነት እንዳመጣለት አይዘረግፍም። እያንዳንዷ ንግግሩ እየተሰነጠቀች ትታይበታለች። ንግግሩ ቁጥብ መሆን

ከተዘራ ያልታረመ አንደበት የጠቅላይ ሚኒስትር አነጋጋሪ ንግግሮች

አስቻለው ፈጠነ የኢትዮጵያን ባህላዊ ሙዚቃ ከዘመናዊ ተፅዕኖዎች ጋር በማዋሃድ ባሳየው ልዩ ችሎታ የተቸረው አርቲስት ነው ። ጥበባዊ ጥረቱ ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህላዊ ትሩፋት እና የሙዚቃ ልምምዶች በልዩ ሚዛን፣ ዜማ እና ዜማ

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

January 15, 2025
ፈራ ተባ እያልን እንጂ ስለፋኖ ትግልና አደረጃጀት ብዙ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዳጀማመሩ ቢሆን ኖሮ እስካሁን ፋኖ ኢትዮጵያን በአጠቃላይና አማራን በተለይ ከታወጀባቸው የመፈራረስና የዕልቂት ኦነግ-ኦህዲዊ ዐዋጅ ነጻ ባወጣቸው ነበር፡፡ ይሁንና በምናውቀውም በማናውቀውም በምንገምተውም

ይድረስ ለፋኖ አደረጃጀቶች በያሉበት – ነፃነት ዘገዬ

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል፦ ዘርፈ ብዙ የጥቃት ሰለባ የሆነ መንግሥት መር፣ ማንነት ተኮር እልቂት ለታዎጀበት ሕዝብ በጥብአትና በጀግንነት የሚከናወን የዘመናችን ሐቀኛ አብዮት ነው። አማራው በዋለበት እንዳያድር፣ ባደረበት እንዳይውል ተወልዶ ያደገበት ቀዬ ድረስ

ከአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

January 14, 2025
ኤፍሬም ማዴቦ ([email protected]) ባለፉት ሁለት ወራት አገር ውስጥና በውጭ አገሮች ያሉትን የኢትዮጵያ ሚዲያዎች ካጨናነቁ ዜናዎች ውስጥ አንዱ ፓርላማው ይህንን ወይም ያንን የህግ ረቂቅ አጸደቀ የሚሉ ዜናዎች ናቸው። የኢትዮጵያ ፓርላማ ምንም ይሁን ምን

የኢትዮጵያ ፓርላማ ሲመረመር

 ፈቃዱ በቀለ(ዶ/ር)   ጥር 2፣ 2017(January 10, 2025) መግቢያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታ በአገራችን ምድር ሲያወዛግበንና በብዙ መቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ህይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበት ዋናው ምክንያት በፖለቲካ ስም የተደረገው ትግል ነው። ይህ ብቻ

ፖለቲከኛ ማለት ምን ማለት ነው? ፖለቲከኛ ራሱን የቻለ ሙያ ነው ወይ? በምንስ ይገለጻል? ለአንድ ህብረተሰብ የሚሰጠው በተጨባጭ የሚታይና የሚመዘን ነገር አለ ወይ? ፖለቲካ ሲባልስ ምን ማለት ነው? አገርን መገንቢያ ወይስ ማፈራረሺያ መሳሪያ?

ከሃይለገብርኤል   አያሌው የኦቦ ሲራጅና የወይዘሮ ፉንታዬ ልጅ ጃዋር መሃመድ ትላንትን ዛሬንና ነጋችንን ሊያሳይ የሚችል መጽሃፍ አዘጋጅቶልናል:: በእውነቱ መጽሃፉ ሊነበብ በሚችል የሃሳብ ፍሰት ተቀንብቦ በአነጋጋሪነቱ ቀጥሏል:: ጃዋርን እና የቄሮን ትውልድ በቅጡ ለመረዳት መጽሃፉ ማንበብ

የጃዋር የፖለቲካ ጅዋጅዌ! “ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ’’

Go toTop