February 11, 2023
3 mins read

የተመለሰው ሰይፈ ተዋሕዶ እና የተመዘዘው ሰይፈ ዳንኤል ክብረት

daniele 1

ሳያስቡበት በቅጡ፣ ሰይፍ ካፎቱ አያውጡ

ካውጡ ደግሞ ካቃጡ፣ እንዳይመልሱት ሳይቆርጡ፡፡

ተዋሕዶ በሕልውናዋ ላይ የመጣባትን ኦነጋዊ ሳጥናኤል ለመቆራርጥ ሰይፏን ካፎቱ አውጥታ በሳጥናኤሉ ላይ አቃጣችበት፡፡  ሳጥናኤሉም በተዋሕዶ ሰይፍ ሊቆራርጥ መሆኑን አውቆ እጁን ወደላይ በማንሳት በፍርሀት መቅለብለብና መወራጨት ጀምረ፡፡  ባለመታደል ግን የሳጥናኤሉን ቃላባይነት በመዘንጋት፣ ሳጥናኤሉ የሰጣትን ባዶ ቃል አምና ሰይፏን ወዳፎቱ በመመለስ፣ ምናልባትም ለሞት የሚያበቃትን ትልቅ ስሕተት (fatal mistake) ፈጸመች፡፡  የተዋሕዶ ሰይፍ ወዳፎቱ በተመለሰበት ቅጽበት ደግሞ ሳጥናኤሉ ተዋሕዶን ቆራርጦ ድምጥማጧን ለማጥፋት ስሎ ያስቀመጠው የዳንኤል ክብረት ሰይፍ ካፎቱ ተመዘዘ

ተዋሕዶ ወደ አፎቱ የመለሰችውን ሰይፍ እንደገና ለመምዘዝ አትችልም ባይባልም እንኳን በጣም ከባድ ይሆንባታል፣ ረዥም ጊዜም ይወስድባታል፡፡  በዚህ ጊዜ ውስጥ ደግሞ የዳንኤል ክብረት ሰይፍ ተዋሕዶን ሙሉ በሙሉ ቆራርጦ ግብአተ መሬቷን ሊፈጽም ይችላል፡፡

ስለዚህም ትልቁ ጥያቄ ተዋሕዶን በጭራቅ አሕመድ ከሚታዘዘው ከዳንኤል ክብረት ሰይፍ ማን ይታደጋት የሚለው ነው፡፡  ይህ ትልቅ ጥያቄ ደግሞ ተዋሕዶ የማን ናት የሚለውን ትልቅ ጥያቄ ያስነሳል፡፡

የኢትዮጵያ ታሪክ ባብዛኛው የተዋሕዶ ታሪክ ስለሆነ፣ ተዋሕዶ የተዋሕዶወች ብቻ ሳትሆን፣ ባገሩ ታሪክ የሚኮራ የሁሉም አገርወዳድ ጦቢያዊ ናት፡፡  በመሆኗም የተዋሕዶ ጉዳይ የሚመለከተው ተዋሕዶወችን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም አገርወዳድ ጦቢያውያን ነው፡፡  ተዋሕዶ የተዋሕዶ እምነት ተከታዮች የሆነችውን ያህል፣ የሙስሊሙም፣ የካቶሊኩም፣ የእግዜርቢሱም (atheist)፣ የፖለቲከኛውም፣ የምሁሩም ናት፡፡

ስለዚህም፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ተዋሕዶን ከኦነጋውያን ለመታደግ አመራር መስጠት እማይችልበት ደረጃ ላይ ከሆነ፣ ይልቁንም ደግሞ ራሱ በኦነጋውያን ተበልቶ ተዋሕዶንም ጦቢያንም በኦነጋውያን የሚያስበላ ከሆነ፣ ተዋሕዶን የማዳኑን አመራር አነግን የሚፋለሙ አምራሮች ሊይዙት የግድ ነው፡፡  የኦነጉን መሪ ጭራቅ አሕመድን ጨርቅ ማድረግ፣ በተዋሕዶና በጦቢያ ላይ ያንዣበበውን አደጋ በማስወግድ ባንድ ዲንጋ ሁለት ወፍ ያስመታል፡፡

 

መስፍን አረጋ

mesfin.arega@gmail.comeeewwee

 

1 Comment

  1. ያሳዝናል ዳንኤል ክብረት የሚበላውን አላጣ ዝና አልጎደለው እንዲህ እየተነሸራተተ እራሱን ለውርደት የዳረገው? አንድ የእስላሞች ስብሰባ ላይ ተጠርቶ የጻፈውንም ሆነ የተናገረውን አስተባብሎ ተዋርዶ ሳየው አዘንኩ ፡፡እንደ አንድ ኦርቶዶክስ ዉርደቱ ውርደቴ ነበርና፡፡ በዚህን ሰአት እምነቱ ምን እንደሆነ የጠየቀው ሰው ይኖራል? ወይንስ ኦርቶዶክስ በመሆኔ ተጸጽቻለው እያለ ነው ወይስ አምላኩን አብይን አድርጓል?

Leave a Reply

Your email address will not be published.

328867899 6629652190397534 91884092340704247 n 1
Previous Story

የ”ብልጽግና” ጠቅላይ ገዥነት (totalitarian state) ከበላቸው ጌ

Nero and abiy ahmed 1
Next Story

የአሁኑ ይባስ!! ጨቅላዎቹ የኢትዮጵያ መሪዎችና የህፃኑ የሮማው ንጉስ ኔሮ (Nero) ገቢራዊ ተመሳሳይነት!!

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop