ፋሲል የኔዓለምን የምተችበት ምክንያት አገኘሁ! • ‹‹መሬት ተሸጠ አልተሸጠ›› ኢህአዴግ መደገፍን ምን አመጣው?

ከጌታቸው ሽፈራው

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ሰሞኑን ‹‹ኢህአዴግን የምደግፍበት አንድ ምክንያት አገኘሁ፡፡ መሬት አይሸጥም፤ አይለወጥም›› የሚል ጽሁፍ አስነብቦናል፡፡ በአሁኑ ወቅት ስርዓቱን የሚተቹ ወይንም የሚቃወሙ ኢትዮጵያውያን ‹‹ኢህአዴግን የምደግፍበት ምክንያት አገኘሁ›› ማለት ይቅርና ትችታቸው የሰላ ሆኖ ካልተገኘ ‹‹ወያኔ›› መባላቸው የተለመደ ሆኗል፡፡ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን ፋሲል ይህንን የፖለቲካ ባህላችን እያወቀና ደፍሮ ‹‹ኢህአዴግን የምደግፍበት አንድ ምክንያት አገኘሁ!›› ማለቱ በራሱ ይበል የሚያሰኝ አዲስ ባህል ነው፡፡
በእርግጥ ፋሲል ኢህአዴግን እደግፈዋለሁ ሲል በጭፍን አይደለም፡፡ ከግራ ፖለቲካው የተቀነጨበ ‹‹ካፒታሊስቶች መሬቱን ተቆጣጥረው አርሶ አደሩን መሬት አልባ ያደርጉታል፡፡›› የሚል መከራከሪያ አንስቷል፡፡ ይህ መከራከሪያ በዚህ ዘመን ደግሞም ፋሲል እደግፈዋለሁ ያለው ኢህአደግ ራሱም ሆነ በቅርቡ የሚገኙት ባለሃብቶች መሬትን በተቆጣጠሩበት በአሁኑ ወቅት ባይሆን ኖሮ ‹‹ለአቅመ መከራከሪያነት›› ብቁ በሆነ ነበር፡፡

‹‹መደገፍን ምን አመጣው?››

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

ፋሲል በአሁኑ ወቅት መሬት ቢሸጥ ቢለወጥ በተወሰኑ የስርዓቱ ደጋፊ ካፒታሊስቶች እንደሚያዝ ሲፈራ ስርዓቱ በመሬት ጉዳይም ብልሹ መሆኑን እየገለጸልን ነው፡፡ ታዲያ የዚህ ብልሹ ስርዓት ተግባራዊ የማትሆን አንዲት ዘለላ ‹‹መርሁ›› እንዴት ትደገፋለች? ኢህአዴግ መሬትን አይሸጥም አይለወጥም የሚለው አርሶ አደሩን ጨምድዶ ለመያዝ እንደሆነ ፋሲልን መምከር የሚቻል አይደለም፡፡ በዚህ መንገድ ኢህአዴግ ዘመናዊ ጭሰኛ መፍጠሩ መቼም ቢሆን ድጋፍ ሊያስገኝለት አይችልም፡፡
በሌላ መልኩ የፋሲል መደገፊያ ምክንያትም ቢሆን በአሁኑ እርስ በእርሱ የሚጋጭ ነው፡፡ ፋሲል መሬት ቢሸጥ ቢለወጥ ካፒታሊስቶች መሬት ስለሚያካብቱ የአርሶ አደሩ መሬት በጥቂት ግለሰቦች እጅ ይወድቃል ይለናል፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ህወሓት/ኢህአዴግ የጥቂቶች መንግስት መሆኑን ይነግረናል፡፡ መሬት የ‹‹መንግስት ነው!›› ሲባል ህወሓት/ኢህአዴግ ባለስልጣናትን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅምን ከማስጠበቅ ውጭ ‹‹መንግስት›› በሚባለው መዋቅር እያገለገለ ነው ሊለን አይችልም፡፡ ስለሆነም ወረቀት ላይ ‹‹መሬት አይሸጥም አይለወጥም›› ተብሎም ቢሆን መላው የአገሪቱ መሬት ጥቂቶቹ ገዥዎች እንደፈገሉ የሚጠቀሙበት ከመሆን አልዳነም፡፡
ለኢህአዴግ ምቹ እስከሆነ ድረስ የትኛውም ካፒታሊስት የቻለውን ያህል መሬት የማካበት መብት ተሰጥቶታል፡፡ እነ አላሙዲን መሬት እስከፈለጉ ድረስ የተፈናቀለው አርሶ አደር ተፈናቅሎ አርሰው የማይጨርሱት መሬት ለ99 አመት በነጻ በሚባል ዋጋ እየተሰጣቸው ነው፡፡ በእርግጥ በየ ክፍለ ሀገሩ ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባም ውስጥ ድሃዎች ተፈናቅለው ሰፋፊ መሬቶች ምንም ሳይሰራባቸው ፋሲል ‹‹መሬቱን ይቆጣጠሩታል!›› ብሎ በሚፈራቸው ካፒታሊስቶች ያለምንም ተግባር ታጥሮ ይገኛል፡፡ ምን አልባት ይህ ነገር የተባባሰው ፋሲል ከአገር ከወጣ ከሆነ አላውቅም፡፡
በአንድ ወቅት ጋምቤላ ውስጥ የተሰራ ጥናት የክልሉን ሰፋፊ መሬት የተቆጣጠሩት 75 በመቶ የሚሆኑት የህወሓት ሰዎች መሆናቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ይህን ጉዳይ ኢሳትም ሰፊ ዘገባ ሰጥቶት እንደነበር ይታወቃልና ለእነ ፋሲል አዲስ ሊሆን አይችልም፡፡ ስለ ሰብዓዊ መብት፣ ዴሞክራሲና ሌሎች ጉዳዮች የማያነሱ ካፒታሊስቶች መሬት ከጠየቁ የፈለጉት ቦታ ላይ ይሰጣቸዋል፡፡ አላሙዲን ሳውዲዎችን ይዞ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቷል፡፡ የቱርክ፣ የህንድ፣ የኳታር…… ካፒታሊስቶች ኢትዮጵያውያንን እምብዛም ለማይጠቅም አበባ፣ ሩዝና ሌሎቹንም ምርቶች ለማምረት አርሶ አደሮችን እያፈናቀሉ ቀጥለዋል፡፡ አርሶ አደሩ እየተፈናቀለ ለ99 አመት በሲጋራ ዋጋ እየተሸጠላቸው ነው፡፡ ታዲያ መሬት በይፋ ‹‹ይሸጥ›› ቢባልስ ከዚህ በላይ ምን ያህል አርሶ አደር እንዳልተፈናቀለ ነው? ከዚህ የባሰ ምን ያህል ወረራስ እንዳልተደረገብን ነበር?

ተጨማሪ ያንብቡ:  መውጫ አብጅቶ መግቢያ የከለከለን አሳዳጁ ማን ነው? - ከግርማ ሠይፉ ማሩ

ከምንም በላይ ፋሲል ‹‹መሬት አይሸጥም አይለወጥም!›› የሚለውን የኢህአዴግን አቋም ለኢትዮጵያ አስቦ ያስቀመጠው ያህል አስቦት ‹‹እደግፈዋለሁ!›› ማለቱ ነው የሚገርመው፡፡ ኢህአዴግ ወረቀት ላይ ‹‹መሬት አይሸጥም አይለወጥም!›› ማለቱን እንደ እውነት ቆጥሮም አንድ መደገፊያ ነጥብ ማስቀመጡ ግራ የሚያጋባ ነው፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ አርሶ አደሩን የስልጣን ምንጭ አድርጎ ስለሚመለከት መሬትን በመያዢያነት መጠቀሙ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ መሬትን በይፋ መሸጡ ኢህአዴግን ተጨማሪ አንድ ቀን የሚያቆየው መስሎ ከታየው ዛሬውኑ እንደሚሸጠው ጥርጥር የለውም፡፡ ኢህአዴግ ፋሲል ከሚፈራው ‹‹ካፒታሊስቶች››ና ከአርሶ አደሩ የትኛው እንደሚጠቅመው ያውቃል፡፡ በእርግጥ ሁለቱንም አብሮ ማስኬድ ችሏል፡፡ ፋሲል መሬት ‹‹ካልተሸጠ›› መሬት አያክብቱም ያላቸው ካፒታሊስቶች ‹‹እድሜ ለኢህአዴን!›› እንጅ አርሰው የማይጨርሱት መሬት ከአርሶ አደሩ ነጥቀው አጥረዋል፡፡ ቀሪውን የአርሶ አደሩን መሬት ደግሞ ‹‹አይሸጥም አይለወጥም!›› ብሎ የሚገዛና ምቹ ካፒታሊስት እስኪመጣ ድረስ ጨምድዶ ይዞታል፡፡ በሁለቱ መካከል ግን ፋሲል የሚለው ኢህአዴግና ‹‹መርሁ›› የለም፡፡ አንደኛ ነገር እሱ ለእራሱ እስጠቀመ ድረስ እንጅ ለአገር ብሎ አይደለም‹‹አልሸጥም!›› የሚለው፡፡ ደግሞም ፋሲል ለፈራቸው ካፒታሊስቶች እንደፈለጉ እየቸበቸበላቸው ነው፡፡
እንዲያው ለካፒታሊስቱ ባይሸጥ ኖሮስ ከነ ሌሎቹ ድክመቶቹ መሬትን አልሸጠም ተብሎ እንዴት ይደገፋል? በኢትዮጵያ ፖለቲካ መሬት ብቸኛው የልዩነት መስመር አይደለም፡፡ መሬት ከሚዲያ ነጻነት፣ ከዴሞክራሲያዊና ነጻ ምርጫ፣ ከፍትህ…..ብቻ ከበርካታ ጥያቄዎች መካከል አንዱ እንጅ ብቸኛው ሆኖ አያውቅም፡፡

አንድ ምሳሌ ላንሳ!

ኢህአዴግ ኢትዮጵያውያንን ያስራል፣ ያፈናቅላል፣ ከመብቶቻቸው ይገድባል፡፡ ለአብነት ያህል እነ እስክንድር ጠያቂ ከልክሏቸዋል፡፡ እስር ቤት ውስጥ ችግር ይደርስባቸዋል፡፡ የታሳሪዎች ቤተሰቦች ይጉላላሉ፡፡ በህገ ወጥ መንገድ ከመታሰራቸውም በላይ እስር ቤት ውስጥ በርካታ ችግሮች ይገጥማቸዋል፡፡ ኢህአዴግ የእነ እስክንድር የፍርድ ጉዳይ ባለው ህገ ወጥነት እንደቀጠለ ከበርካታ ችግሮቻቸውና ጥያቄዎቻቸው መካከል አንዱን ቢፈቅድ ልንደግፍው ነው ማለት ነው፡፡ እኔ የፋሲልን መርህ ከዚህ በተመሳሳይ ነው የማየው፡፡ ምን አልባት የመሬት ጥያቄ ቢመለስ እንኳ በኢህአዴግ ላይ የምናደርገውን መማረር (ተቃውሞ) ወደ ሌሎቹ ጉዳዮች ይቀይረዋል አሊያም ምሬታችን ይቀንሰዋል እንጅ ሊደገፍ አይገባውም፡፡ የሚገባህን የቀማህን አካል ጮኸህም ሆነ እንዲሁ ሲመልስልህ በዛ ቅጽበት ‹‹አንድ፣ ሁለት፣ ሶስት፣….›› እያልክ ‹‹በምክንያት›› ልትደግፈው አትችልም፡፡ ምክንያቱም ያችን አንዲት ነገር መልሶም (ፋሲል ላልተመለሰው ነው የደገፈው) ጥፋተኛ ስለሆነ ማማረርክን፣ መቃወምክን ልታቆም አትችልም፡፡ ኢህአዴግ በመሬት ጉዳይ ከብልሹነት አልወጣም፡፡
በዚህ ብልሹ ዘመን መሬት በግልጽ ቢከፋፈል ጉዳት ያመጣ ነበር ተብሎ ‹‹በምክንያት›› መደገፍ መንግስት ያለ ህግ መነሻ አስሮ ጠያቂ ለከለከለው እስረኛ ጠያቂ ሲፈቅድ ‹‹አንድ ምክንያት›› ጠቅሶ እንደመደገፍ ነው፡፡ አሊያም ሁለት ሶስት እቃ መስረቅ ይችል ነበር ተብሎ የተገመተን ሌባ አንድ እቃ ሰርቆ ስለወጣ ይህን ሌባ የመመረቅ ያህል ነው፡፡ ሌባ ሌብነቱን፣ ብልሹ መንግስት ብልሹነቱን ጨርሶ እስካላቆመ ድረስ ከብልሹነቶቹ መካከል ሳይመቼው ስለቀረ አሊያም ስላላሰበው ብቻ አንዱን ወይንም ሁለቱን ስለተወ አሊያም ስላልፈጸመ ሊያስደግፈው የሚገባ አይመስለኝም፡፡ በመርህ የምናምን ከሆነ ማለቴ ነው!

ተጨማሪ ያንብቡ:  “የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ጥያቄ ፍትሐዊና ሕጋዊ ነው”

4 Comments

  1. For TPLF to give free land for those who have greedy apatite, some hard working innocence farmer has to die, evicted tortured or being homeless.
    Humanity is out of the window and TPLF is practicing the NAZI principles for the last twenty three yrs and we have difficulties what is wrong with this until it come to our individual life,
    Our proud farmers has been the worst stage of their life and no one said a word to stop this, a specific group at times become a vitamin of these dehumanisation denies the humanity of the other group. Nation lack constitutional protection for countervailing speech, our hero journalist are a good example for this, hundreds of journalist were fled the country if they are lucky otherwise tortured on the street and man raped by man to ensure they will never survive from the trauma they wre put in. Hate propaganda become the usual and normal routine and people still put the TV or radio to listen and act based on false information. We lost our mothers, children’s, sisters and brothers from more than one region, nothing said about those millions disappear from our eyes.

    People suffer immensely with luck of basic needs and send they youngsters to the worst side of the region (Arabs country, Greek, Turkey, Italy )the list is non stop in the same time western poured billions of dollars for the government who does not care a bit to its nation and make them richer than ever as individual, and they knew exact lye where the money is and does nothing.

    Our young sisters and brothers fall into criminals become a victim, or draund in the ocean otherwise being slave for those inhumane Arabs. Human right watcher said or does very little to bring the issue to international level, back home the Government gave an order to close the embassy door on it is own people and watch them stoned and die.

    Our young sisters was injected poison not to have a child, or infectious vires to I limitation the race basedon hatrad or feel threatened by theses particular ethnic.

    So why are we talking about one hopeless person who has no ground stand for his own belive ruther than the worst thing it happend before and now at this time they go around and massacre with group or individual. We need to pay attention on that and do something about it before it is too late.

  2. የፍሲል አድናቂ ነበርኩ .አሁን ግን ተቀየምኩት በእውነት !ወያኔን እሥከ መቃብር
    ቦታው ካላደረሥኩት አላምነውም

  3. What is the ethiopian peasant/farmer hoping for in Ethiopia today? – redistribution of land. They want land and liberty (political)!

    Opposition parties and some well-known Ethiopian economists say they want to be free (politically to choose whoever they like) and freedom to sell their land.

    They will have freedom when they are able to free themselves from their land, the only way is therefore sell the land and be free. Kkkkkkkkk ! wedew aysiku

Comments are closed.

Share