ስለመሬት መሸጥ መለወጥ -ተጨማሪ ማብራሪያ (ፋሲል የኔዓለም)

 

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

ውድ ስርጉትና ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች የጽሁፌን ይዘት በደንብ ባለመረዳት ይመስል “ የምን ጠጋ ጠጋ” ብለውኛል። እኔና ኢህአዴግ ከምንጠጋጋ ጸሃይና መሬት ቢጠጋጉ ይቀላል። ወያኔን የምደግፍበት አንድ ነገር አገኘሁ ማለቴ ስላቅ ነው። ወያኔ መሬት አይሸጥም አይለወጥም ይላል። ይህን ያለው ከ20 በፊት ነው። ዛሬ ግን በሙሉ ልቡ ደፍሮ እንደዛ አይልም። ለምን? ያን ጊዜ የህወሃት ሰዎች ገንዘብ አልነበራቸውም። ዛሬ ግን የአገሪቱን መሬት ጠቅልለው የሚገዙበት ገንዘብ አላቸው። ዛሬ መሬትን በግል አዙር ብንለው መሬቱን እነማን እንደሚገዙት እናውቃለን። በ20 አመት ፖለቲካ ማሰብ የለብንም። ብዙ ህዝብ አገራችን ያለችበትን ሁኔታም የተረዳ አይመስለኝም። ዛሬ ገንዘቡ ኢፈርት በተባለው በህወሃት ድርጅትና በአላሙዲ ስር ነው ያለው። መሬት ወደ ግል ቢዞር እኮ የሚገዙት ሁለቱ ናቸው። እና 90 ሚሊዮኑን ህዝብ ባሪያ እናድርገው። ወያኔን ታግሎ መጣልና አዲስ መንግስት ማቋቋም ተገቢ ነው። አሁን መሬትን ወደ ግል አዙር እያልን ከጨቀጨቅነው ግን በደስታ ያዞርና ሌላው ህዝብ የዝምባብዌ ወይም የደቡብ አፍሪካ እጣ ይገጥመዋል።

 

አንዳንድ ሰው ስለ አዲሱቹ ካፒታሊስቶች የገባው አልመሰለኝም። ኢትዮጵያ እኮ የደቡብ አፍሪካ አይነት የኢኮኖሚ ስርአት እየገነባች ነው። በዘር ላይ የተመሰረተ ስርአት።

ለማንኛውም ለሌሎች አስተያየት ሰጪዎች የሰጠሁትን መልስ እዚህ ላይ እንዳለ አትሜዋለሁ። የአቋም ለውጥ ያደረኩ የሚመስላችሁ ካላችሁ ጽሁፌን እንደገና እንድታነቡት እመክራለሁ።

 

“ዳዊት ሰለሞን የተባለው ሰው በመሬት ዙሪያ ለጻፍኩት መልስ ሰጥቷል። አመሰግናለሁ። እኔ ከ20 አመት የኢህአዴግ የስልጣን ጊዜ በሁዋላ የተገለጠልኝ ሃሳብ እንደሆነ፣ ቀደም ሲል መሬት እንዲሸጥ እንዲለወጥ ስፈልግ እንደነበር የሚያስመሰል ሃሳብ አቅርቧል። ያነሳቸው ሃሳቦች ብዙም ጠናካራ ሆነው ባላገኘኛቸውም፣ ለትምህርት ይሆነን ዘንድ ትንሽ ለማለት ፈለኩ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  መስጠት ብቻ ወይንስ ስጥቶ መቀበል? (ጥሩነህ)

 

ቀደም ብየ እንደገለጽኩት መሬት ወደ ግል እንዲዞር ከሚፈልጉት መካከል ነኝ። ነገር ግን በዚህ መንግስት መሪነት የሚደረግን ክፍፍል አልደግፍም። ዶ/ር ታደሰ ብሩ ኢህአዴግ መሬት ወደ ግል መዞሩ ኢህአዴግን ቢጠቅመው ኖሮ እስካሁን ያደርገው ነበር በማለት መሬትን ወደ ግል ማዞር ለፖለቲካው እንደሚጠቅም ገልጿል። የዳዊትም ሃሳብ ተመሳሳይ ይመስላል። የእኔ ሃሳብ ደግሞ መንግስት መሬትን ወደ ግል እንዲያዞር ከመጠየቅ ፣ ስርአቱን ቶሎ አስወግዶ በዲሞክራሲያዊ መንገድ የሚቋቋመው መንግስት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ያከፋልፍ የሚል ነው።

 

ኢህአዴግ  መሬት ለማከፋፈል ለምን አልፈለገም? ብዙ ሰዎች ህዝቡን ለመቆጣጠር ስለሚመቸው ነው ብለው ምክንያት ይሰጣሉ። ሊሆን ይችላል። ነገር ግን መሬት ወደ ግል ቢዞርም ኢህአዴግ ሌላ የመቆጣጠሪያ ዘዴ መፍጠሩ  እንደማይቀር ማወቅ አለብን።   ለእኔ ዋናው ምክንያት ኢህአዴግ የራሱን ካፒታሊስቶች እስኪፈጥር ጊዜ ለመውሰድ ስለፈለገ ነው። ባለፉት 22 አመታት ወያኔ በአንድ ዘር ላይ የተማከለ ካፒታሊስቶችን ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት አድርጓል። በስልጣን ላይ እስካለ ድረስም ይህንን ስራውን ይቀጥልበታል። ካፒታሊስቶች በቂ ሀብት አጠራቅመው አገሪቱን ሙሉ በሙሉ  የሚቆጣጠሩበት ደረጃ መድረሱን ወያኔ ሲረዳ ፣  ማከፋፈሉ አይቀርም። ምክንያቱም መሬት  ወደ ግል ቢዞር መሬቱን የሚገዙት እነዚህ ካፒታሊስቶች ይሆናሉና። ይህ አካሄድ ደግሞ የአገሪቱ መሬት በጥቂት ካፒታሊስቶች እጅ እንዲወድቅ ያደርጋል። እነዚህ ካፒታሊስቶች ደግሞ በአብዛኛው የአንድ አካባቢ ሰዎች ናቸው። ወደድንም ጠላንም አብዛኛው መሬት በእነሱ እጅ መውደቁ አይቀርም። መሬት በመንግስት ስር ከቆየ ግን አዲሱ መንግስት  ሲመጣ በቀላሉ ይነጥቃቸዋል። አዲስ መንግስት ከመምጣቱ በፊት መሬት ወደ ግል ቢዘር  ፣ የሚመጣው መንግስት ጦርነት የሚገጥመው ከእነዚህ ካፒታሊስቶች ጋር ይሆናል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  (የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ) ከወገብ በላይ ታቦት ከወገብ በታች ጣኦት!!

 

መለስ በአንድ ወቅት  “መሬትን ወደ ግል ብናዞር መሬቱን የሚገዙት እነማን እንደሆኑ እናውቃለን፣ ሌላው ህዝብ መሬት የሚገዛበት ገንዘብ የለውም ፣ ስለዚህ መሬት ወደ ግል ቢዞር በአንድ ብሄር እጅ ተመልሶ እንዲገባ ማድረግ ነው።” ብሎ ነበር። መለስ አንድ ብሄር የሚለው የፈረደበትን አማራ ነው። መለስ ባለፉት 23 አመታት ሲሰራ የነበረውም ካፒታሊስቶች በአብዛኛው ከራሱ ወገኖች ብቻ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው። በአሁኑ ሰአት መሬትን ወደ ግል ማዞር የአገሪቱ ሰፋፊ መሬቶች በእነዚህ ካፒታሊስቶች እጅ እንዲወድቅ ማድረግ ነው። ወያኔ ዘረኛ መንግስት ባይሆን ኖሮ ችግር አይኖርብኝም ነበር። ዘረኛ መንግስት ደግሞ ፍታሃዊ በሆነ መንገድ መሬት ወደ ግል ያዞራል ብሎ ማለት ራስን ማሞኘት ነው።”

 

12 Comments

  1. You are right Fasil.
    I donot think sirgute is also serious when she say tega tega…. We knew that you are not ABA MELA!!!

  2. I am saying what I have said that what we lack is that a forum that could help converge all ideas for establishing a better Ethiopia, Fisil. You and Sirgut are deeply concerned about our beloved country and people, so do I. What I have come to understand is that we desparetly need is a forum that can help converge all ideas from all walks of life for a better future of our people and country. God bless you and all the people who are deeply concerned of our people and country.

  3. Dear Fasil,

    Yes, your idea is realistic. I want to commend you here. But that same fear was there 23 years ago from the side of others. What Meles Zenawi once said (which you mentioned above) about the issue of land privatization was also realistic in fact. Now that new capitalists are emerging from another part of the society and you feel you may loose in the competition, you came to recognize the fact you have denied for 23 years. It is very nice of you at least to finally come to reality in principle.

  4. I agreed with a good detailed account of his opinion on land possession law. He predicted the event to happen behind the curtain and is a temporal strategy he considered for the very time he forwarded his view a day ago. We should make a community diagnosis and situational analysis what ever our upcoming interest is. Family has done this already so that he put his diagnosed and analyzed view. Good.

  5. Dear Fasil,
    your idea is quite clear. Some people just want to twist it or as always the weyanes want to seed a mistrust among the opposition. You did not have to explain it all again. The mischievous weyanes are busy looking for every means how they could creat a gap and insert a wedge among the people or the opposion. They twist words or creat and dissiminate lies or engage in nonsense discussions in the nsme of weyane-haters or true ethiopians so that the useful socialmedias look like useless among ethiopians.

  6. Dear Fasil,
    TPLF metfo neger yemadrege chelotaw ejig keftegna newe.Meratn yegel madreg
    bifelege noro yadergew neber.Balew seritm endelebu eyaderegu newe.Ahun KTPLFgar yalew chegre bemifetabet menged aleagbab yeteyazewm merate gudaye yefetal.TPLF behzb asteyayet mekniate yemiadergew lewtt selelale graatagaban.

  7. yabe tokichawn satire anbibo yemireda sint sew neber. yewoyane jelewoch ena nizu sew Abe’n ye eprdf tsehafi adrigo yemiasib kadrena bizu sew awkalehu. ye Fasil silak(satire) bergit gilts new. le sbzagnaw anbabi gin aygebaw yihonal yemli firhat alegn. Fasil ye ysihufun titel bikeyrew emertalhu. neger gin yakerebew hasab gilts new. tikikilim new.

  8. Dear Fasil,

    Great !!! It is a good assessment. However, I have got one question. When do you believe it will be fair to privatize land in Ethiopia? I expect you will say “After the TPLF falls”. You may feel that it will be fair to privatize land once TPLF is removed from power. But there will be another group (you can say TPLFites) who feel the opposite when TPLF falls. Some 23 years ago when EPRDF and many other groups supported the idea of public ownership of land, they had the same concern that you have today. You did not have that concern that time. You developed the concern as a result of what happened in political economy of the country over the past 20 years. But they (those who 23 years ago supported public ownership) developed the concern as a result of what happened in the country over a century. It looks that you want to begin the game when you are sure you will win it !! Right?

    To conclude, I would like to say it is very good that you at least came not only to understand how it feels to be on the other side, but also to bravely express it.

  9. All you arguments against Eprdf privatization (zare gin ye hiwahat sewoch genzeb alachew, zare gin ye agaritun meret teklilew yemigezubet genzeb alachew etc…) doesn’t hold water. Dr tadesse biru ‘s argument is another politically twisted argument. As if this is not enough now you are equating Zimbabwe and South Africa with Eprdf ie the government and one individual Alamudi, nonsense!

    Eprdf lemin meret lemekefafel alfelegem? –Hizbin lemokotater endiyamechew new meretin yalakefafelew? –What kind of logic is this? Kkkkk eprdf wede siltan some answer possible answers – 1) Eprdf is people’s revolutionary party. 2) Eprdf wants the vote from the gebere, most probably 4. Eprdf uses land privatization to keep the opposition out of the country side etc…. 4.eprdf does not have a clue about land policy or land reform. 5. eprdf wants land to remain state property.

    According to you this impending privatization does not include all Eprdf, allies and supports (now only TPLF and Al amoudi, yigermal!!). So you tell us instead of fighting with one government, Ethiopians will be struggling with many capitalists (where did you get this Maths from? you recited only TPLF/the government/the state and one individual!) Do your Maths again! Nothing will have changed. You are talking about the same government or the state we are in now.
    With a new government, those who have money will take over the land including Eprdf people. Or are you telling us, privatization will exclude certain ethnic groups? – or you don’t know what you are talking about.

    Capitalistoch beki habt aterakmew ageritun mulu bemulu yemikotaterubet derja medresun woyane sireda makefelu aykerim…. Meret bemengist sir kekoye gin adisu mengist simeta bekelalu yinetkachewal. Adis mengist kememtatu befit meret wede gil bizor, yemimetaw mengist torinet yemigetmew enezihin kabitalistoch gar yihonal. How did you come up with this? A new government that can dismantle this government will have difficulty to overthrow few capitalists? Kkkkkkkkkk wedew aysiku!!

    You can support whatever land policy, leave meles and eprdf if you are serious, only then will you be able to analyze land policy objectively, you are too partial!!!

    Privatization will lead to monopoly (concentration of land in the hands of few capitalists). The point is – those who support privatization of land stand against the Ethiopian people. You are anti Ethiopian people to put it very openly::

  10. ወዳጄ ፋሲል

    ይህ የመሬት ነገር ብዙ ያሳሰበህ ትመስላለህ። የአንድ ሃገር የመሬት ይዞታ ፖሊሲ በአንድና ሁለት ነጠላ ምክንያቶች ላይ ብቻ ተመስርቶ አይወጣም። አሁን ባንተ ትንታኔ መሰረት አሁን መሬት ይሸጥ ቢባል 22 ዓመታት ገንዘብ የሰበሰቡት የወያኔ ሰዎች ገዝተው ይጨርሱታል ። ስለዚህ ወያኔ እስኪወርድ መሬት የመንግስት ቢሆን ጥሩ ነው። ለመሆኑ ወያኔ ሲወርድ፤ ምን አይነት አወራረድ ነው የሚወርደው? በግፍ ባከማቹት ገንዘብ ያፈሩት ሃብት ባለመብት ይሆናሉ ብለህ ታስባለህ? እንደኔ እንደኔ ወያኔ ወረደ ማለት … የ20 አመቱ የዘር ፖለቲካ ያወየበው የመንግስት ጓዳ ሁሉ ተፈቅፍቆ አዲስ ቅብ (እውነተኛ ዲሞክራሲያዊ ቀለም) ስለሚቀባ ሃብቱም መሬቱም ባለመሬቱም አይኖርም። ከዚህ በኋላ ያለው ሥራ አዲስ በሚመሰረተው ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ተወዳድረው የህዝብ ይሁኔታን የሚያገኙና ለመንግስትነት የሚበቁት የፖለቲካ ኃይሎች ስራ ይሆናል። የውስጥ ፖሊሲ በመሆኑ ማለቴ ነው። በዓለም አቀፍ ህግ ሊታይ የሚችለው የውጭ ኢንቨስተሮች ጉዳይ ነው። የውጭ ኢንቨስተሮች ፈሰስ ያደረጉትን ካፒታል የማግኘት መብት ይኖራቸዋል። ወያኔ የሰጣቸው የ100 ዓመት ኮንትራት ግን አይጸናም። ስለዚህ ወዳጄ ፋሲል መሬት እንደ ሱፐር ማርኬት ሸቀጥ ተሸጦ ያልቃል ብለህ አትስጋ ?፡፤ መሬቱማ አሁንም የነሱ ነው እንኳን ለራሳቸው ለጎርቤት ሃገርም እየሰጡ አይደል እንዴ? ዋናው እነሱን እንደ አመጣጣቸው መሸኘት ብቻ ነው መፍትሄው። እዚያ ላይ እናውራ ….መሬቱን ተወው…

Comments are closed.

Share