አስማተኛው የኢኮኖሚ እድገት! (በ ገብርኤሉ ተስፋዬ)

ከየት ጀምሬ ወደየት እንደምሄድ አላውቀውም፣ አሁን አሁን የእድገት መለኪያው ምን እንደሆነ እንኩዋን ግራ ገብቷችዋል:: ወይስ የኢኮኖሚ እድገቱ ለኢትዮጲያውያን ሳይሆን ኢትዮጲያን ለሚያስተዳድሯት ብቻ ነው ወይ? እውነቱ በገሀድ ግልፅ ብሎ እያለ ካለፉት አስር አመታት ጀምሮ ጆሮዋችንን በሁለት ዲጅት ሀገሪቱ አድጋለች እያሉ ሲያደነቁሩን ከረሙ:: ለኔ እድገት የሚለው ቃል በአሁን ሰሀት ስድብ መስሎ እየታየኝ ነው:: የተወሰኑ ሰዎች ብር በብር ላይ አካበቱ፣ሀፍታም ሆኑ፣ ህንፃ ገነቡ፣ከመኪና መኪና ቀያየሩ ወዘተ እየተባለ  በኢትዮጲያ ስም መነገዱ አግባብ አይደለም:: ለመሆኑ የኢትዮጲያ ህዝብ ጠግቦ የሚበላው ሀሁን ነው ወይስ የዛሬ 10 እና 20 አመት በፊት ነው? መልሱን የሁላችንም ልቦና ያውቀዋል! ህዝቡ አንገቱን ደፍቶ ሁሉን ነገር ሰምቶ እንዳልሰማ  አይቶ እንዳላየ ዝም ሲል ጅል የሆነ መሰላችው:: እስቲ የኢትዮጲያ እድገት ተብየው ያመጣውን ለውጥ ለመመልከት ልሞክር::

በመጀመሪያ መመለከት የምፈልገው የምግብ ዋስትናን ነው::የምግብ ዋስትና ማሽቆልቆሉን የማያምኑ ለሆዳችው የሞቱ እነሱ ብቻ ሲበሉ ሌላውም የበላ የሚመስላችው ብዙ አሉ:: ሆኖም ግን እውነት እውነት ነች እና ምንም ምንም ቢሉ እውነትነቷን  አትቀይርም:: ስለምግብ ዋስትና ለመናገር በአዲስ አበባ ስለሚኖረው ህዝብ መናገርን መረጥኩ ምክንያቴም አዲይስ አበባ የኢትዮጲያ ዋና ከተማ እንደ መሆኑዋ መጠን፣የኢህአዴግ አመራሮች ስለእድገት ሲያወሩ የሚጠቅሱዋት ከተማ ስለሆነች እና በጣም ብዙ ህዝብ(ከ 5 እስከ 6 ሚልየን) ስለሚኖርባት ነው:: እዝይጋ ሥራ አልባ የሆኑትን፣ሚበላ የሌላችውን ብዙዎቹን የማሀበረሰባች አካላትን ሳይሆን ማየት የምፈልገው ስራ አገኘው ብሎ በመንግስት መስሪያቤት ተቀጥሮ የሚሰራውን ነው:: አንድ የመንግስት ሰራተኛ የድግሪ ምሩቅ የሆነ በወር 1600 ብር የሚያገኝ ሲሆን ከዚያ ላይ 250 እስከ 300  ግብር ይከፍላል በእጁ ላይ 1300 ይቀረዋል እንበል ፣ የቤት ኪራይን በተመለከት በአሁን ሰሀት በአዲስ አበባ አንድ ክፍል ቤት በትንሹ ከ 700 እስከ 800 ብር የሚያወጣ ሲሆን ከ 1300 ላይ ይሄን ብር ስናነሳ  500 ብር አካባቢ ይቀረዋል፣ በየቀኑ ለትራንስፖርት በትንሹ 3 ብር አወጣ ቢባለ 400 ብር እጁ ላይ ቀረው ማለት ነው:: እስቲ ይሄ ሰውዬ ሙሉ ጤነኛ ነው የህክምና ወጪ አያስፈልገው ቤተሰብ (ልጆችም) የሉትም ብንል እንኳን 400 ብር አያምስት ኪሎ ጤፍ ወይም 4 ኪሎ ሥጋ በወር አይገዛለትም:: በአስማት መኖር ማለት ይሄ ነው!! በየቦታው እንደምንሰማው  ከ100,000 በላይ የጎዳና ተዳዳሪዎች በአዲስ አበባ ብቻ ይገኛሉ:: እነሱም ከእድገቱ ጋር  ነው አብረው የመጡት እያሉን ነው! ብሎ ብሎ ጉርሻ መሸጥ የተጀመረበት አገር እድገት አለ ከሚሉ አስማት አለ ቢሉ ይሻላል::እርግጥ ነው የተወሰኑ ሰዎች በአዲስ አበባ  የምግብ ዋስትናችው የተጠበቀ ነው  ከነርሱም ብዙወቹ የገዝው ፓርቲ አባላት ናችው:: እና ስለ እድገት ሲወራ የኢትዮጲያ ህዝብ በልቶ ጠግቦ አደረ  የሚለው ተረት ባይተረክ መልካም ነው እላለው::

ተጨማሪ ያንብቡ:  እናንተ ለአገልግሎት ነበር። እነሱ ዘበኛ ነው የሚፈልጉት። - ዳዊት ዳባ

በመቀጠል ማየት የምፈልገው ማንኛው የምራባውያን ሀገር የኢኮኖሚ እድገት መጣ ብለው ሲያወሩ ለማሀበረሰባችው የተሻለ የስራ እድልን ፈጥረው ሲገኙ ነው:: በአሁን ሰሀት አብዛኛው የኢትዮጲያ ወጣት የት ነው የሚገኘው ጫት ቤት፣ መጠጥ ቤት፣ሺሻ ቤት፣ ወይስ ኑሮውን ለማሸነፍ ከሀገር ወቶ ተሰዶ በረሀ በልቶት ቀርቷል:: ማንም በአገሩ መኖርን የሚጠላ የለም! ወጣቱ ከሀገር ተሰዶ ሲወጣ ነጮቹ ናፍቀውት አይመስለኝም:: ከሀገር ተሰዶ በረሀ ላይ መሞት እንዳለ፣ በሀር ውስጥ የሻርክ እራት መሆን፣መደፈር፣ ከህንፃ ላይ ተወርውሮ መሞት አልፎ ተርፎም የሰውነት አካላችው እስከመሸጥ እንደሚደርስ እያወቁ ሀገራችውን ጥለው የሚሄዱት ቁጥር መጨመሩ ምንን ያሳያል? ምን ያህል ወጣቱ በኢህአዴግ አመራር እንደተማረረና  ተስፋ እንደቆረጠ ነው የሚያሳየን:: ሌላው የሴት እህቶቻችን ቁጥር በወሲብ ንግድ ላይ እየጨመረ መሄዱ በካንፓስ ደረጃ መርጠው  የተማሩት ፊልድ ነው ብዬ አላምንም ለኔ ይሄ የሚያሳየው ወጣቱ ከስራ ማጣት የተነሳ ኑሮን ለማሸነፍ የማይፈልገው አዝቀጥውስጥ እየገባ እንዳለ ነው:: ከሰሞኑ ደግሞ  ይባስ ብሎ እድሜያችው ከ18 አመት በታች የሆኑ ልጅ አገረዶችን በየድረ ገጹ ለወሲብ ሽያጫ አቅርበዋል፣ የሚገርም ነው እዚም ዘመን ላይ ደረስናል ያስብላል!

በሶስተኛ ደረጃ ማየት የምፈልገው ከምግብ ውጪ ለሰው ልጅ መሰረታዊ ነገሮች ብዬ የምላችውን የውሀና የመብራት አቅርቦትን ነው:: በአዲስ አበባ ከተማ የመብራትና የውሀ ነገር አነጋገሪ ከሆነ ሰንብቷል:: አብዛኛው የከተማው ክፍሎች ውሀና  መብራት በፈረቃ ነው የሚያገኙት:: ጥቁር አንበሳን የሚያህል ሆስፒታል በየህለቱ በጣም ብዙ በሽተኞችን የሚያስተናግድ ሆኖ ሳለ ለዚህ አይነቱ ችግር መጋለጡ በጣም አሳዛኝ ነው:: የእድገት አንዱ መሰረቱ የህዝብን የ መጠጥ ውሀ እና የመብራት አቅርቦት ማሟላት ወይም ስርጭቱን መጨመር ሲሆን በአዲስ አበባ የምናየው ነገር ግን የተገላቢጦሽ ነው::

ተጨማሪ ያንብቡ:  አንድነት፤ አንድነት ስንል አምሳ ዓመት ሊሆን ነው---ለመተባበር ዘውጋዊ ፖለቲካን የማስወገድ ቆራጠኛነት ያስፈልጋል - አክሎግ ቢራራ (ዶር)

የህዝቡን የምግብ ዋስትና ካልጠበቁ ወይም ካላሻሉ፣ ለወጣቱ የስራ እድል ማመቻችት ካልቻሉ፣ በቂ ወይም ተመጣጣኝ የውሀ እና የመብራት አቅርቦት መስጠት ካልቻሉ ታዲያ  የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከህዝቡ ህየዘረፉ በሚወስዱት  ብር የሚገነቡት እንፃን በማየት ነው እድገት መጣ የሚባለው:: ኢትዮጲያ በየአመቱ በቢልየን ዶላሮች የሚቆጠር ገንዘብ በእርዳታ መልክ ታገኛለች ከዚህ ውስጥ ብዙው ገንዘብ የሚጠፋው በ ጥቁር ፕሮጀክት(Black project) ነው:: የ ጥቁር ፕሮጀክት ማለት መንግስት በህዝብ ስላልተመረጠ ስልጣኑን ለማቆየት ሲል  ለማሀበረሰቡ ብልፅግና የሚውለውን ገንዘብ ቀይሶ ለካድሬወችና  ለሰላዮች(ለሆድ አደሮች) እድሜውን ለማራዘም እንዲሁ የሚበትነው ብር ነው:: ከሰሞኑም እንደሰማነው መንግስት የተቃዋሚ ፓርቲን እና አባላታችውን ለመሰለል በሚልዮን ዶላር የሚቆጠር  የህዝቡን  ንብረት እንደሚጠቀም(እንደሚበትን) ተገልጿል::ሌላው በሀገሪቷ ውስጥ መጣ እየተባለ የሚያወሩለት የኢኮኖሚ እድገት መሰረት አልባ ስለሆነ መሰረታዊ ለውጦችን ሊያመጣ አልቻለም ይህን ልል   የቻልኩበት ምክንያት

1.  ስለኢኮኖሚ እድገት ሲወራ ብዙም ጊዜ ትኩረት  የማይሰጠው ግን ለኢህአዴግ ዋንኛው የገንዘብ ምንጭ የሆነው የስራአጥ እህትና ወንድሞቻችን በየሀገሩ የሚሰደድ ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመሩ መሄዱ ነው::ይሄን ስል በአሁን ሰአት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጲያን በየአገሩ ተበትነው የሚገኙ ሲሆን በየ ወሩ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ለቤተሰቦቻችው ይልካሉ:: በተዘዎዎሪ ይሄን ብር ኢህአዴግ የኢኮኖሚ እድገት ነው ይላለ:: ዕህት እና ወንድሞቻችንን በተለያዩ ሀገሮች በትኖ በነሱ ጀርባ ላይ ቁጭ ብሎ መሰረታዊ እድገት ሊመጣ አይችልም::

2. በመቶ ሺዎች  የሚቆጠሩ ህዝቦችን ለብዙ ሺ አመታት ከኖሩበት ቦታ አፈናቅሎ ለተለያዩ የእንድ እና የውጭ ሀገር ባለሀፍቶች መሬታችውን በመሸጥ የኢኮኖሚ እድገት አመጣን ማለት አይቻልም::እነዚ ሰዎች መሬታችው ሲወሰድ በመንግስት ብዙ ነገር ቃል የተገባላችው ቢሆንም አንዳችውም ግን እውን አልሆኑም:: በአሁን ሰሀት ከተወሰኑት በስተቀር በሙሉ በኬንያና በተለያዩ ቦታወች ተሰደው ሲገኙ በተቃራኒው ደግሞ የኢህአዴግ ካድሬዎች የከበሩበትን መንገድ እናያለን:: ማንኛውም አይነት እድገት በመጀመሪያ ደረጃ አላማ ሊያደርግ የሚገባው የመሀበረሰቡን ጥቅም ማስከበር ነው::

ተጨማሪ ያንብቡ:  የአብይ አህመድ የመደመር ትውልድ የመጽሐፍ ምረቃ እና ያደረጋቸው አፍራሽ ንግግሮች -  በሽፈራው ዘውዴ

3. ምህራባዊያን(mainly US,UK and ISREAL) ኢትዮጲያ ያላት የጆክራፊ አቀማመጥ ቴሬሪስትን ለመዋጋት ያመቻል ብለው ስለሚያምኑና የኢትዮጲያ መንግስትም ጥቅሙን ለማስከበር አሽከር እንደሆነ ስላዩ  በየአመቱ የሚሰጡት እርዳታ እየጨመረ መሄዱ ይህን እና የመሳሰሉትን አጋጣሚወች በመጠቀም በኢትዮጲያ  እድገት አመጣው እያሉ ያወራሉ:: መሰረታዊ ችግሮች እየተባባሱ ህዝቡም ኑሮ እያሰቃየው፣ ወጣቱም ሥራ አልባ ሆኖ በየአረብ አገሩ እየተንከራተተ እድገት መጣ ማለት አይቻልም!! በሀገሪቷ ውስጥ የሚገባውን ገንዘብ በሙሉ ኢህአዴግ እና ካድሬዎቻችው አፍኖ በመብላት መሰረታዊ ለውጦች ሊመጡ አይችልም::  ስለዚህ ሁሉም ኢትዮጲያዊ የተሻለ አመራር  ያለው መንግስት ለማምጣት የበኩላችንን አስተዋጾ ማድረግ አለብን!!!!!!!!!

ፍቅር ለኢትዮጲያ ህዝብ!!!

አስተያየት ያላቹ በዚ ኢሜል ልታገኙኝ ትችላላቹ ( allforethiopia@gmail.com).

1 Comment

Comments are closed.

Share