ቀዳማይ ወያኔ፤ ዓድዋ እና የካቲት 11 በወያኔ ትግሬዎች ዕይታ – ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያ ሰማይ አዘጋጅ)

ከላይ በግራ በኩል የሚታየው ፎቶግራፍ፤ የቀዳማይ ወያኔ መሪ ብላታ ሃይለማርያም ረዳ ለዳግማይ ወያነ መሪ ለመለስ ዜናዊ በቀዳማይ ወያኔ የተገለገሉበት የጦር ሜዳ መነፅር ሲያስረክቡት ነው።
ብዙዎቹ በዚህ ጽሑፍ የቀረቡ መረጃዎች እና ትንታኔዎች በሂደት ላይ ካለ ከሚቀጥለው አዲስ መጽሐፌ የተገኙ ምንጮች ናቸው።እኛ በታሪክ አጋጣሚ ተገኝተን ጸረ ወያኔ አቋም ይዘን የምንተነትን ጸሐፊዎች የተቻለንንን ያህል የወያኔ ቅጥፈቶች እያጠናን ስናቀርብ ማንበብ ሰልችቶአቸው ግማሽ ገጽ አንብበው ወደ ቀላል ዜና እና ትንታኔ የሚሮጡ ብዙ እንደሆኑ አገምታለሁ።እንዲህ ዓይነት ልምድ ጥልቅ እውቀት እንዳይኖረን ያግደናል።እንድያ ከሆነ የሚሞግቱንን ጠላቶች በማስረጃ ለመመከት ደካሞች እንሆናለን።መረጃ ሲያጥረን ሕዝቡ የጠላት ‘ፕሮፓጋንዳ’ ተማሪ ይሆናል።። ስለዚህም ብርቱ ድካም፤ምርምር ጌዜ እና መስዋእት የተደረገባቸው ጽሑፎች ማንበብ ድርሻችሁ እንደሆነም አትዘንጉ።

ባለፈው በክፍል ፩ “የወያኔ ትግሬዎች በጉንደት፤በጉራዕ፤በዶጋሊ ፤….ጦርነቶች የሚዋሹት ውሽት ሲመረመር” በሚል ለብዙ አመታት ሲነግሩን የነበረውን “የወቅቱ ጦርነቶች” የገጠሙት ትግሬዎች ብቻ ነበሩ፤ እያሉ የሌሎች ኢትዮጵያዊያን ተሳትፎ ዋጋ በማሳጣት ሲዋሹን የነበረው ጀብደኛ ትምክሕት በጐንደር፤በጐጃም፤በወሎ እና በሸዋ ጦር ተዋጊዎች ጭምር እየታገዙ ጦርነቱን ገጥመው ድል የተቀዳጁ አንደነበር አንጂ ትግሬ ብቻውን እንዳልተዋጋ እና ድሉም የብቻችን ነው የሚለው የወያኔ የታሪክ ቅሚያ እንደበፊቱ በቸልተኛነት መታለፍ እንደሌለበት ከሃቅ የራቀ ውሸታቸውን በወቅቱ የተጻፉ መረጃዎች በማስረጃ አጋልጫለሁ። ክፍል ፪ “የዓፋሮች እና አፄ ዮሐንስ ፍትግያ” የሚለው ጽፌ አዘጋጅቼው ልለጥፈው ነበር፤ እሱን ወደ ክፍል ሦስት በማቆየት ይህ ክፍል ሁለት ብለን በመሰየም እናንብበው።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለይም አማራ ሆይ ከዳግም ክህደት ተጠንቀቅ! - አገሬ አዲስ

1 Comment

Comments are closed.

Share