[ዴሞክራሲያ ቅጽ 39 ቁ. 4 የካቲት 2006 ዓ.ም] – ለዳግማዊ የካቲት ሕዝባዊ አመፅ እንነሳ

የየካቲት 66 አብዮታዊ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ጉልህና ደማቅ ሚና ያለው ክስተት ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዝንተ ዓለም የሚያስበው የሚዘክረው ኹነት ነው። የአገዛዞች ጭቆናና ብዝበዛ መጠን እጅግ አድጎ ዜጎች መኖር የማይችሉበት ሁኔታ ሲከሰት የሕዝብን ቁጣና ብሶት ያዘለ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ሊፈነዳ እንደሚችል የሕብረተሰብ ሕግ ይደነግጋል። በዓለም ላይ አስከፊ አገዛዞችን ያርበደበዱና ከሥልጣን ያስወገዱ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች በጣም በርካታ በመሆናቸው ዝርዝሩን ማቅርብ አስቸጋሪ ቢሆንም በ19ኛውና በሃያኛው ክፍለ ዘመን የተከሰቱትን የፈረንሳዩንና የሩሲያ አብዮቶች፤ በ1989-90 ዓም በምስራቅ አውሮፓ አምባገነን አገዛዞች ያስወገዱትን ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንዲሁም በ2010-12 የአረብ የጸደይ እንቃስቃሴ የሚል ስያሜ የተሰጣቸውና በተለያዩ የአረብ አገሮች ተቀጣጥለው አምባገነን አገዛዞችን ያስወገዱትን ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች ለአብነት መጥቀስ ይቻላል። በአገራችን በየካቲት 66 የተከሰተው አብዮታዊ እንቅስቃሴ በዓለም ውስጥ ከነበሩት አብዮቶች የተለየ ባይሆንም በወቅቱ ለ50 ዓመታት ያህል ስር ሰዶ የነበረውንና ማንም ሊያነቃንቀው የማይችልና መለኮታዊ ኃይል ነው ተብሎ ሲፈራ የነበረውን የአጼውን ሥርዓት ገዝግዞና አዳክሞ ከሥልጣን እንዲወገድ በማድረጉ በኢትዮጵያ
ታሪክ ውስጥ አቢይ ምዕራፍ ይዞ ይኖራል።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ተጨማሪ ያንብቡ:  በኢትዮጵያ “የብሄር ፖለቲካ” ምንጩ፤ ያስከተለው ጉዳትና መፍትሄዉ (በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ)

1 Comment

Comments are closed.

Share