ቪ ኦኤ ወይስ የኢትዮጵያ/ወያኔ ሬዲዮ ?

ከመስፍን ደቢ
በዚህ ባለንበት ዘመን አለማችን በሚገርም ፍጥነት ለመከታተል ፋታ በማይሰጥ ሁኔታ የፖለቲካ ለውጦች እየተካሄዱ ነው። ሶቭየት ህብረት ሲፈረካከስ ትልቁ ስባሪ ዩክሬን ነው። ዛሬ ዩክሬን እየተናጠ ነው አለምም አተኩሮበታል ። በቤንዚዌላ ቀውጢ ሆኗል ፤ አብዛኞቹ የአረብ መንግስታት ተፋጠዋል፤ በኢትዮጵያችን ደግሞ የወያኔ የመጨረሻ ምዕራፍ መድረሱ ይተነበያል። ወያኔና ደጋፊዎቹ ሽብር ላይ ናቸው። እንዲህ በምትናወጠው አለማችን የሆነውን በትክክል ማን? የት? መቼ? እንዴት? የሚለውን አንዱም ሳይቀር እንድናውቀው የሚያደርጉን ጋዜጠኞች ናቸው። ለሙያቸው ትልቅ ክብር አላቸው፣እውነተኞች ናቸው፣ ደፋር ናቸው፣ ለህሊናችው ብቻ የሚታዘዙ ናቸው፤ እውነትን ፈልገው ለኛ ሲያቀርቡና እንድናውቅ ሲያደርጉን እነሱ እስራት፣ ድብደባ፣ ስቃይ፣ ሞትም አለባቸው። እነዚህን ቁርጠኛ የእውነት አርበኛ ጋዜጠኞች እላቸዋለሁ። ስለአገራችን ብቻ ብናገር ኢትዮጵያ እንዲህ ባሉ ጋዜጠኞች ታድላለች። ተሰደውላታል፣ ታስረውላታል፣ ሞትንም ቀምሰውላታል።
ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ እና በዲያስፖራው ሁለት አይነት ጋዜጥኞች አሉ። አንዱ ክፍል የወያኔ አገልጋይ የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ የሆኑ ያሉበት ነው። ሌላው ክፍል ደግሞ ለጋዜጠኝነት ሙያ ተአማኒነቱ የበረታ እውነቱን ማቅረብ ዋጋ ቢያስከፍልም ቆርጠው የሚጋተሩ ያሉበት ነው። እንዲህ ባለ አጠቃላይ ምደባ ብንጠቀም የሚቀር አንድ ክፍል አለ። የስራ ተቋማቸው በሌሎች መንግስታት የተመሰረተ ሆኖ ኢትዮጵያ ተኮር ዜና የሚያቀርቡትን ለማለት ነው። ይህም ቪኦኤ እና የጀርመን ሬዲዮ የመሳሰሉ ናቸው። በተለይ እነዚህ ተቋማት ቪኦኤ የአሜሪካን ጀርመን ሬዲዮ የጀርመን ናቸው። ኢትዮጵያ ተኮር ዜና በአማርኛ፣ በትግርኛ፣ በኦሮምኛ፣ በሱማሊኛ ያቀርባሉ። ኢትዮጵያውያን በአገር ውስጥ እና በውጭ እንደ አማራጭ የዜና ምንጭ ይጠቀሙባቸዋል። በእነዚህ የዜና አውታሮች ያሉ ጋዜጠኞች የአሜሪካን ወይም የጀርመን መንግስትን አቋም እንዲያንጸባርቁ ቢገደዱ እንረዳቸዋለን ከዚህ በተረፈ ግን ለተግባራቸው መሪ ህሊናቸው ብቻ ነው ብለን እናምናለን። ለእውነት መቆምን፣ ሚዛናዊ መሆንን ያለውን እንዳለ የሆነውን ያለተጨማሪ አስተያየት ለአድማጩ ማቅረብ ሙያው የግድ ይላል ፡የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ጋዜጠኛ የኢትዮጵያ ሬዲዮ የለቀቀውን ውሸት ቢያስተጋባው የምንታዘበው ይሆናል። ቪኦኤ የኢትዮጵያ መንግስታዊ የዜና ተቋም ያለውን ቢያስተጋባ ትዝብት ላይ ይጥለዋል:: ቪኦኤ በዲያስፖራው ካሉ የወያኔ “የዜና” የፕሮፓጋንዳ ጋዜጠኞች መለየት አለበት ። ቅዳሜና እሁድ በመጣ ቁጥር አምባሳደር ኢንተርቪው የሚያደርጉና ስለልማት የሚያወሩ ባዶ ገረወይና የሆኑ አሉ። ቪኦኤ ከነዚህ መለየት አለበት።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ግንቦት 7, 97 የታየውን የለውጥ መነሳሳት ለመድገም ጠንካራ ሰላማዊ ትግል የግድ ይላል

ቪኦኤ በሞያቸው የተከበሩ ጋዜጠኞች ያሉበት ተቋም ቢሆንም ደግሞ ደጋግሞ ስህተት የሚፈጽም ረቀቅ ባለ መንገድ የወያኔን አቋምና መልእክት የሚያቀርብ ጋዜጠኛም አለበት። ይህ መሆኑ ደግሞ ያሳዝናል ። ለምሳሌ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላንን አቅጣጫ አስቀይሮ ጄኔቭ እንዲያርፍ አድርጎ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቀው ረዳት አብራሪ ሀይለመድህን አበራ ድርጊቱ በአለም የዜና አውታሮች ሁሉ ቀርቧል። ከሁሉም የዜና አውታሮች ግን ቪኦኤ እና የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቲቪ የዘገቧቸው ይመሳሰላሉ። ሁለቱም ያተኮሩት የሀይለመድህን የአእምሮ ሁኔታ ላይ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት ስለ ሀይለመድህን አእምሮ ማተኮር የፖለቲካ ብሶቱና በደሉ እንዳይሰማ እና እንዳይተኮርበት ለማድረግ ነው። የቪኦኤውም “ጋዜጠኛ ” ይህን የማድረግ ግዴታ የለበትም ሚዛናዊ በሆነ መልኩ መዘገብ በቻለ ነበር። በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ያለ የተዋጣለት ወጣት ሙያተኛ ምን ምክንያቶች ላደረገው ድርጊት ጋፋፉት ብሎ ጥያቄውን ወርውሮ ማለፍ ይችል ነበር፤ ግን መልእክቱን ጋዜጠኛው ከኢትዮጵያ ሬዲዮ ጋር በረድፉ ለማሰለፍ የቆረጠ ስለሚመስል የአእምሮ ሁኔታ ላይ አተኮረ፤ ሁኔታውም ካለማወቅ አይመስልም።
ዛሬ ዘመናችን አማራጭ የዜና ተቋማትን ቴክኖሎጂ ያንበሸበሸን ዘመን ነው። እንደ ዱሮው ቪኦኤ ወይም የጀርመን ሬዲዮ ብቸኞቹ የነበሩበት ግዜ አይደለም። የኢትዮጵያ ህዝብ በሀገር ቤትና በውጭው ይህን እውነታ ያውቃል። ቪኦኤ ለራስህ ብለህ ጣፍጥ ነው መልእክቱ ። ልጅ ያቦካው ለራት አይበቃም እንዲሉ ምራቃቸውን ዋጥ ያደረጉትን ጥቅም ሊያማልላቸው የማይችሉትን የእውነት አርበኛ የሆኑትን ጋዜጠኞች ከፊት ረድፍ ቢያሰልፉ ለቪኦኤ ጠቀሜታ ይኖረዋል። ቀድሞ እንደተባለው ኢትዮጵያ የጀግኖች እና የእውነተኛ ጋዜጠኞች ባለ ጸጋ ነች፤ ገና ብዙ ታፈራለች።ብዙ ጀግና ጋዜጠኛ የሚወለድበት የለውጥ ማእበል እያስገመገመ ነው። መጥኔ ለቪኦኤ እራሱን ካላረመ፤ ሰሚ ያጣ ጋዜጠኛ ከመሆን ሰውረኝ ነው።
ቪኦኤ አንዱ ጋዜጠኛው አግባብ የሌለውን ተግባር ቢፈጽም እንደ ተቋም መጠየቁ አይቀርም። ሄኖክ ሰማእግዜር ባደረገው ነገር ትዝብት ብቻ ሳይሆን በጣም አዝነናል ቆይቶ ደግሞ ህዝባዊ ቁጣ ማስነሳቱ አይቀሬ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በደመ ነፍስ የምትነዳ ሀገር -

7 Comments

  1. It has been a while since I have listened to VOA but when I did if I did not know any better I would have thought Henok worked for ETV than VOA. Just listen to his interview with Straight Talk Africa after Abebe Gelaw incident with the late dictator back in May 2012 and you will be the judge.

  2. Henock is a typical woyane agent deployed to serve his masters as under cover journalist.Though it is up to him to be or not to be a woyane ,but it is unethical to use the noble profession for cheap political propaganda . This pseudo journalist use to have exploiting his position many a times unashamedly either by presenting exaggerated woyanes fabricated development stories or echoing overly his master’ s propaganda like the one mentioned by Mesfen. i think the voa board has to pay heed what this gutter journalist is doing before too late.

  3. I AGREE THAT VOA IS NOW ETV OR RADIO FANA, I REMEMBER THE ENTERVIW ABOUT THE HERO (HIJACKER) WITH THE PUBLIC OFICCE THAT ‘ALL THE MEIDIA TALKING ABOUT FREEDOM IN ETHIOPIA, SO WHY THE ETH AIRLINES HIDDIND INSTAD OF SAING SOMETHINE OR REPLY WHAT THEY R TAKING ABOUT???

  4. I think VOA become increasingly tplf servant: I have written a protest to VOA and as I promised it is a while since I stop listening VOA. The official tplf agent who is working at VOA Henock “The Adwa BOY” Semagzier is totally out of line. It Easley can be dictated how he is trying to manupulated the news to shield the woyane crime against the Ethiopian people. The case in point is his recent report against the pilot (our hero) to defame him in colabration with the tplf media : he said ” a co pilot is not allowed to land a plane with out the presence of a captain” there fore he said “landing the aircraft by itself is a crime”. wow !!! Even the tplf spokesman refuted that claim. in fact it is a regular practice that the co pilot is allowed to do so”. On the other hand, also his interview with the elder brother of the pilot was the same question raised by the “Reporter and ETV news”. I think VOA should be boycotted by all Ethiopians. We have many glaring evidence that Henok “The Adwa Boy” Semaegzier is a planted spy of the tplf. No doubt about that.

  5. ይህ ሔኖክ ሰማእግዚአር የሚበል ፍጡር ምን ወንዝ ምን ቤተስብ ያፈረው ርካሽ ግለስብ ነው? የሀይለመድህን ብቸ አይደለም የአበበ ገለውም፧ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስም፧ (ወዘተ) ብዙ ነው ተወርቶ አየልቅም ። ብቻ ቀን ያገጥመን።

    ቁጭ በል ጠላቴ ወደጄን መስለህ፤
    ዐውድማ አግኝቺ እሰከ አባረይህ፤

  6. VOA is a balanced news out let not like others one sided .please learn from them how to be an ethical journalist.Thank you VOA.

Comments are closed.

Share