ሞትን የመረጡ ወጣት ሴቶች የመጀመሪያውን ብቻኛ የነፃነት ተጋድሎ ምዕራፍ ከፈቱ። የምዕተ ዓመቱ ማህጸን ተስፋን ሰነቀ!

ከሥርጉተ ሥላሴ (ሲዊዘርላንድ ዙሪክ)

„የእመቤት ጣይቱ የመንፈስ ንጥር ፍላጎት „ሚሚ ሳራ ለምለም ሜላት እሙዬ“ ቀድመው ዓወጁት፤ ይህንን የጥበብ ውጤት እንደ ዘወትር ጸሎት ቁጭ ብዬ አዳምጠዋለሁ። ፍለጎቱና ሊያስተላልፍ የፈለገው መልዕክት ምንድ ነው በማለት። ፍልስፍናውስ? ነጻ የሆነች ሀገር ፤ ትንቢት፤ ራዕይ፤ ተስፋ የትናንት የሴቶች ብቃት፤ የዛሬ መጋፋትና መገለል፤ መረሳት ለምን? ነገስ በዚህ ከተቀጠለ ምን ይሆን ዕጣው? መፍትሄውስ? የልጆቹ የከበረ ተግባር ሁሉንም አመሳጥሯል። ጥያቄውንም እራሱ ቁልጭ አድርጎ መልሷል። እጠብቀዋለሁ! ለእኔ በጣም ትርጉም አለው። እንዲሁ አልተመልኩት ነበር። ምክንያቱም የኢትዮጵያ ህዝብ ፍጹም የተለዬ ህዝብ ነው። ሲወድም ሲጣል አስተምሮ ነው። ዬኢትዮጵያ ህዝብ መምህር ነው ተንባይም!

በተጨማሪ እኔ የረዳት አውሮፕላን አብራሪ ሃይለመድህን አበራ ወላጅ እናት የሰጡት ቃለምልልስ አጋጣሚ እሱ ባለቤቱ ያሰናደው ነው። በዬትኛውም ሁኔታ የትም ቦታ የምትገኝ ሴት ብቃቷን እንድናይ፣ እንድናስተውል መስታውት እንዲኖረን እግዚአብሄር ሁኔታውን አመቻችቶ የፈቀደበት አጋጣሚ ነው ብዬ ነው ያሰብኩት። አሁን ማን ይሙት ከዛች የጣነ ሃይቅ ዳርቻ ነፋሻማ በጣም ትንሽዬ የቅመም ምርት ገጠራማ ከተማ ከደልጊ ተፈጥረው፤ እርግጥ በኑሯቸውም ባህርዳር ከተማም ትልቅ ቢሆንም ሴት ቀና እንዳትል ያለው ማህበራዊ ተጽዕኖ ሁሉ ተቋቁሞ የበለጸገው ብቃታቸው እንደዛ አይነት የለማ የመንፈስ ብስለት ሳዳምጥ ፈጽሞ የማይገመት ነበር። እኔ ብቻ ሳልሆን ያዳመጠው ሁሉ በተመስጦና በአድናቆት ነበር የገለጸው። ይህ ሁሉ ለሁላችንም አንድ ነገር ይነግረናል „ሴቶችና የተመሰጠረው ብቃታቸው ከጊዜ ጋር መምጣቱን“ ዓይናችን – እዝነ ልቦናችን ከፍተን እንድንመረምረው …. ከልብ ሆነንም እንድናዳምጠው አሳስቦናል። „አስተውሉ“ ይላል ቃሉ ….

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሱሰኛ አማራ ሆይ! ተሱስህ ተላቀህ ወደ ጎበዝ አለቃህ! - በላይነህ አባተ

ስለሆነም ነው የዘንድሮ የ2006 የካቲት መግቢያና መሸኛው ገድል እዬሠራ ያለው። እነሆ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊ ወጣት ሴቶች ውስጣቸው የተቃጠለበትን መራራ ዬጎጥ አስተዳደር፤ ፊት ለፊት ወጥተው አወገዙ። „አትከፋፍሉን! አሉ በድፍረት። አንዲት ሀገር! አንድ ህዝብ! በማለት አወጁ። ኑሮ ከበደን፣ ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ሲሉም የሽፍታውን አስተዳደር የወያኔን ልማትና ፖሊሲው ቅብ ጭላጭ መፈክር አፍርድሜ አሳጋጡት።
ነፃ ትውጣልን አብነታችን ርዕዮት አለሙ ሲሉ በአንድ ድምጽ አስተጋቡ። ወንድሞቻችን አርበኞቻችን ይፈቱልን በማለት በቁርጠኛ ድምጽ ገለጹ አቡበከር፣ እስክንድር፣ ውብሸት፣ አንዷለም፣ ናትናኤል፣ በቀለ፣ የፖለቲካ እስሮኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈቱ! ነፃነት፣ ነፃነት፣ ነፃነት እንዴት ያለ ዕጹብ ድንቅ የሚመረምር የገዘፈ ተግባር ከወኑ።
ይህ ንጹህ መንፈስን ዘረኛው ወያኔ እንዴት መግፋት እንዴት መገፍተር ይቻልል? የፍርሃቱ ማስታገሻ ካቴና ነውና አደረገው። ነገም ግን ህዝባዊ አመጽ ከዚህም ብሶ ጠንክሮ ይቀጥላል። ዛሬ ጸጥ ለጥ ብሎ የሚገዛው የወያኔ ህግ „እንብኝ“ ሲገንፍል ቦታ የለውም። የተከፋ ህዝብ፤ የተባሰ ህዝብ በማናቸውም ጊዜ አምቆ ያዘውን እሳታዊ ቁጣ ያፈነዳዋል … ዋ! ያች ዕለት! ዋ! ያቺ ሰ ዓት!

ይህ መሰል የአደረጃጃትና የእንቅስቃሴ መንገድ ማቆሜያ የለውም፤ ሰንሰለት፤ ባሩድ፤ አፈና፤ ማስፈራራት፤ ወቀሳ፤ አይገድበውም። ሱናሜን የትኛው ሳይንስ አስቆመው፤ ገታው። የህዝብን አመፅም ምንም ማንም ኃይል ሊያስቆመው ከቶውንም አይችልም። የነፃነት ራህብ፤ የዜግነት ራህብ፤ የዴሞክራሲ ራህብ ፈጽሞ የማይቆም መገድ ነው። ብራቦ! ሰማያዊ የልብ አድርሶች ናችሁ።

ተመስገን! ነገ ሰው አለው። እናት ሀገር ኢትዮጵያ ተተኪ አላት፤ ዳምኖ ጨፍግጎ የነበረው ተስፋችን ብሩኽ ጨረር በወጣቶቻችን በራ! ደመቀ! አንድነትና መኢህድድ አዘጋጅተውት በነበረው ሰልፍም ወጣት ሴቶቻችን አብረው በአጋርነት በግንባር ቀደምትነት „ከባዶ ጭንቅላት በዶ እግር ይሻላል“ ሲሉ ነበር የተደመጡት። ተደገመ!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሶስት ሀቆች  የባንዳ ውላጆች ለሆናችሁት የህወሀት ርዝራዦችና ለተረኛ ኦሮሙማዎች - ወይራው እርገጤ

በአፍሪካው አህጉራዊ ጽ/ቤት፤ በኢትዮጵያ ዋና ከተማ በአዲስ አባባ የጣይቱ ልጆች፤ የምንቴ ልጆች፤ የዘውዲቱ ልጆች
„እንብኛ! አሻም! በቃህ ጎጠኛ ወያኔ!“ ከረፋኽን አሉት ነገሩት …. ያንገሸገሻቸውን የጎጥ የከፋፍለህ አስተዳደር በሰላማዊ ትግል ድምፃቸውን አሰሙ። ይህ ነው የሚፈለገው። በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ „በቃኝ“ ማለት። ትግሉ አሁን እዬተከላከለ አይደለም። እያጠቃ ነው። ይግርማል ሴቶች በዚህ ደፋር ድንቅ ሞገዳም ድምጽ የነፃነትን አንደበት ሞሸሩት! ኮራንባችሁ እነ – አርበኛ! ተስፋችን ጣልንባችሁ እነ – ሰማዕት! እግዚአብሄር ይስጣችሁ። ይጠብቅልንም። እኛም ከጎናችሁ ነን።

ሴቶች በቃኝን በብዙ መልኩ መግለጽ ይችላሉ። ሆድ አደሩ ቢወዳችው፤ ቢያፈቅራቸው ሀገርንና ህዝብ ከገደለ ጋር
አብሬ ጎጆ አልመሰርትም በማለት፤ ሲሞት ቀብር ባለመገኘት፤ የወያኔ ቡችላ ሱቆች ላይ ግብይትን በማቆም፤ በወያኔ ማናቸውም ተቋምት አማራጭ አስከ አላቸው ድረስ ማዕቀብ በመጣል፤ በማህበራዊ ኑሮ የወያኔ ቀንዶኞችን ሰላምታ በመንሳት „ እንቢተኝነት“ በሁሉም ቦታ በማናቸውም ጊዜ ማደረግ ይችላሉ። ከዚህ በላይ ምን መከራ ሊመጣ ነው?! በሀገር በህዝብ ታሪክና ክብር የሚቀና ምቀኛ የሽፍታ አስተዳደር እኮ ነው ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው።

እንደ እኔ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ምቹ የሆኑ ህሊናዊ ሁኔታዎች ተሟልቷዋል። ሙሴው ደግሞ „ዕንባ“ እራሱ ነው። የወ/ሮ ዘነቡ እራቅን ስለመሆናቸውም በዚህ ተገለጠ። „በቃን! ገማህን!“ ባዶ ቀፎ ባዶ ሳጥን ነው። ልቅላቄ የሌለው ሙጣጭ አተላ …..

እነክላራ ትግሉን ሲጀመሩት በዚህ መልክ ነበር። ልክ በ103ኛ ዓመቱ የመጀመሪያው ብቻኛ የኢትዮጵያ ሴት እህቶች ድምጽ ራሱን ችሎ ተደመጠ። ተስተጋባ። ኮፐን ሀገን አዲስ አበባ ላይ – ወሸኔ የእኛ ቀንበጦች። ይህ የተጋድሎ ታሪክ ነገ አፍሪካንም ሊያካልል የሚችል አዲስ ገድል ነው። አፍሪካ ተማሪ ኢትዮጵያ አስተማሪ። ወያኔ እንዲህ ይራገፋል። ወያኔ እንዲህ መለመላውን ይቀራል። በወያኔ ላይ ያልሸፈተ ልቦናና መንፈስ ከቶውንም የለም። ከሊቅ እሰከ ደቂቅ፤ ከታዳጊ እሰከ አዛውንት።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሕወኃት - ጨዋታው እያበቃ ነው!!! Game Over!!  የሕወኃት መፍረክረክ የቅርብ ጊዜ ምልክቶች፣ መንስኤዎችና አንደምታዎች

እሺ እኛስ የእነኝህ እህቶቻችን እስር ቢቀጥል ምን ማድረግ ይኖርብናል? አዲስ ፈንድ አቋቁመን ቤተሰቦቻቸውን ቀጥ አድርገን መያዝ አለብን። ለእኩልነት መታገል ማለት ይሄው ነው። ለኣለም አቀፉ ማህበረሰብ ዝርዝሩን እዬተከታተልን
በባለቤትንት ማሳወቅ አለብን። ድምጻችን፣ ፍላጎታችን፤ ውስጣችን፤ ለገለጸ ኃይል ማናቸውንም መሰዋዕትነት ለመቀበል መዘጋጀት ይኖርብናል። ቀጠሮ የለም ዛሬውን መጀመር አለብን። ጊዜ ሳናባክን። በማናቸውም ሁኔታ ተገናኝተን። እኛ ሴቶች ውጭ የምንኖረው የነፃነት ትግሉ ቤተኞች ለእህቶቻችን አጋርነታችን በተግባር መግለጽ ይኖርብናል። ይህ አመት በሁሉም ቀዳዳ ተገኝተን ትንቢቱን ዕውን ለማድረግ መትጋት ይኖርብናል። የእኛ ነፃነት ከሀገራችን ነፃነት፤ የእኛ የእኩልነት ጥያቄ ከህዝባችን እኩልነት ጋር የተጋባ ነው። ለዘለቄታ ሥር ነቀል ለውጥ ጠንክረን እንሥራ።
ለነበረን የከበረ ጊዜ ምስጋናዬ በፍቅር ላኩኝ – ለእኔዎቹ።

ሴቶች በመሆን ይገለጻሉ!
ሴቶች በበልህነት ይተረጎማሉ!
ሴቶች አስቀድሞ በማዬት ይታወቃሉ!
ፈተናን ከመፈጠሩ በፊት አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር ኢትዮጵያዊነት!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

6 Comments

  1. የኔ ጀግኖች አኮረችሁኝ፡ የሀገሬ ኢትዮጵያ ከክብሮ እና ከነፃነቶ ገር ለዘላለም መኖሮ ተረገገጠ። በኢትዮጵያና በምወዳቸው ልጆቼ ሰም ቃል እገባለሁ ከእነንተ ጋር ነኝ።

  2. The ones who are doing the fighting in the country have small words. But those watching the action from afar have lots of slogan tarnished words even for a title like the above. stop talking too much in the name of those who are acting. You are increasing the number of those who are irrelevant in what they write these days.

  3. “ቀኑ የሴቶች ነው!የመናገር፣ የመፃፍ፣ የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታቸውን መግለጫ ቀን ነው። የቤት እመቤትነትና በመሀበር ታቅፎ መንቆፍቆፍ መቆም አለበት። የሴቶች ቀን ይከበር ሲባል ብልጣብልጦች ካኒቴራ፣ቲሸርት፣ ሻርብና የአንገት ልብስና አባባ እየሸቀሉ ይክበሩ ማለት አይደለም። ሴቶችን እኛ በእኛ የተፈጠራችሁ ያልነበራችሁ እኛ ብቻ ስንኖር የምትኖሩ እያሉም ሊያላግጡባቸው አይገባም…!የሴቶችም ድምጽን ጥያቄ ይሰማ…ምላሽም ያግኝ ጠፋ ተባለው ታሪክ ተዳፍኖ ከሆነ ሴቶች ብልሃተኞች ናቸውና…የኢህአዴግ ብልቱን ቢጠነቀቅ ይገባዋል እንላላን..የቆጡን አወረድ ብላ ብብቷ ታየ እንዳይሆን አንቺ ኢህአዴግ(ኮመዲ) ሆይ፣ ዋ የመጣሁ እንደሆን አለ….በቸር ይግጠመን ወይ ፍረድ ወይ ውረድ በለው!

  4. ወድ የኢትዮጵያ ሴቶች ሆይ የእናንተ መብት መክበር ያለበት ገና ከመወለዳችሁ ጀምሮ መሆን ነበርበት ሆኖም የምትወልዷቸው ወንዶች ከየት እንደመጡ ይረሱታል ፡ያለመታደል!! አሁንም የሴት መብት ሲባል፡ መጀመሪያ አንገትን አዙሮ መመልከት ያሽል፣ እህትን፣ እናት፣ሚስትን፣ሴት ልጁን እንደሚያያት ሁሉ ባጠቃላይ የሴት መብት በኢትዮጵያችን መከበር አለበት ተብሎ በ66ቱ የተክፈለው መስዋትነት በቂ ማስረጃ ነው አሁንም እነ አበራሽ በርታ ርዮተ ዓለሙ ወ.ዘ.ተ የሚከፍሉት ዋጋ ለነጻነት ለፍትህ ለአድነት ስለሆነ የሴት እህቶቻችን ጥያቄ የሁላችንም ጥያቄ ነውና፡ በጎናችሁ እንስለፍለን፡ መከፈል ያለበትንም መስዋት ለመክፍል ዝግጁ ነን፡መሃል አዲስ አበና ዲያስፖራ

  5. ውደ የኢትዮጵያን ሴቶች ጥያቄ የማንናውም ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ነው ከጎናቸው መቆም የማንኝወም ሕዝብ ሃልፊነትና ግዳጅ ነው!!!!

Comments are closed.

Share