“ሣንሞት መቀባበር መቼ ይሆን የሚቆመው?

“እውነት ቤት ሥትሰራ ውሸት ላግዝ ካለች፤
ሚሰማር ካቀበለች
ማገር ካማገረች
ጭቃም ካራገጠች
ቤቱም አልተሰራ እውነትም አለቆመች።”

ለእውነት መቆምና እውነትነት በሌለው ነገር ግን ; እውንት በሚመሰል; ማንኛውም አይነት መሀበርም ሆነ እድር;
መሰባሰብ እውነቱ ሲገለጥ መጨረሻው መፈረሱ ሀቅ ነው።

በሀገራችን ባሕል ሰው በደል ሲበዛበት ሲጨንቀው ይጮሃል፤ ጎረቤትም ይደርሰለታል። ሊደርሰብት ካለው
ችግርም ይድናል። ይኸ ሲወረድ ሲዋረድ የመጣውና ዘመናት የማይሽረው ታላቁ ባሕላችን ነው። ዛሬም በትውልድ አገሩ
ፈትህ አጥቶ መከራውና ፈተናው ቁም ሰቅሉን ሲያሳየው “በዘር” እንዲያሰብ፣ እንዲበተንና እንዲሰደድ ተጽእኖ
ሲደረገበት አሁንም እየታደገው እና እያቻቻለ በጽናት ያቆመው ይኸው ታላቁ የመቻቻል ባሕሉ ነው።

በሰለጠነው አገር እነዲህ ያለውን ጩኸትና የፍትህ መዛባት ግን የሚሰማ የህግ ቦታ አለና የሰው ጩኸት ከንቱ ሆኖ
አይቀርም።
ከላይ እንደመንደርደሪያ አድርጌ የተጠቀምኩበትን የመገቢያ ሀሳብ ሰትመለከቱ ምን ሊልን ነው ደገሞ፤ የምንሰ
ቀብር ነው በሚል ልትገረሙና ልትደነቁ እንደምትችሉ ለመገመት አልቸገርም። ሆኖም የመልዕክቴ ፍሬ ሃሳብ ግን ይኸ
ሳይሆን የሚከተለው ነው። ሰሞኑን አነድ የሕግ ኮርሰ በሰትረጅና መጦሪያ ይሆነኛል በዬ በአነድ ኮሌጅ እየተከታተልኩ
ነበርና “መምኸሩ” ለመወያያ ብሎ ያቅረበው የሕግ ምሳሌ የእኛው ጉድ በመሆኑ እጅግ አሰደነቀኝ እጅግም አሰደነገጠኝ።

እናንተንም ለግምገማው ያመቻችሁ ዘንድ እሰቲ ተመልከቱት ? እኔን ያሳዘነኝ ጉዳዩ ባሰተዳደር በኩል ሊፈታ
የሚቸል እንደነበር ከ 20 በላይ የሆኑት ተማሪዩዎች በመሰማማታቸው እና አሰተዳደሩ ምን ያሕል ደካማና የውሰጥ ችግር
ያለበት እንደሆነ ያሳያል። ነፃ በሆነ አካልም (Independent investigation) ሊመረመር የሚገባና ጥፋቱ ከተረጋገጠ በሆላ
አሰተዳደሩ በሙሉ እሪዚይን (Resign) ማድረግ አለበት የሚል አሰተያየት መሰጠታቸው ነው። ለምን አሳዘነህ ብትሉኝ
በየትኛውም መሀበራዊ ሰብሰባችን ውሰጥ ጎልቶ እየታየ የመጣው ሹክቻ ምን ሊሆን እንደሚችል ሰለምረዳና አንባቢያንም
እንደምትረዱ ሰለማምን ነው። የሚከተለውን ሊንኩን በጥሞና አንብባችሁ ሌላውን የራሰን አሰተያየትና ፍርዱን አሁንም
ለናንተ ትቼዋለሁ። http://www.canlii.org/en/on/onhrt/doc/2014/2014hrto208/2014hrto208.html
ታዲያ በዚየው ሰሞን ከአንድ ወዳጄ ጋር በከተማው መካከለኛ ቦታ ላይ በሚገኝው ሰታርባክሰ (Starbucks
Coffee) ቤት ቁጭ ብልን ቡናውን ፉት ዕያልን ሰለሀገራችን ችግር አንድ ባንድ እያነሳን ሰናወጋ ከቆየን በሆላ ፤ እንደው
እኮ ይገርማል አለኝ ወዳጄ ጫወታውን ሲጀምር፣…. እንደው…… በሁለት ዶላር ($ 2.00) አንድ ኪሎውን ቡና ካገራችን
ገዝተው በሶሰት ($ 3.00) ዶላር አንድ ሲኒ ቡና ለኛ እዚህ ሲሸጡልን አይገርምም ? በሚል ሁለታችንም ተደንቀን ፈገግ
በማለት ጫወታውን ቀጠልን።
ወዲያው ወዳጄ እንዲህ ሲል ጀመረ፡ ሰሞኑን አንድ የሚያሳዝን ነገር ሰምቼ አዝኛለሁ አለኝ። እኔም ለመሰማት
በመጓጓት ምን ተፈጠረ ? ብዬ ጆሮዩን ኮርኩሬ መሰማቴን ቀጠልኩ። ይገርምሃል አንድ ለበርካታ አመታት እንደተነገረው ለ
14 አመት ነው። በኮሚቴ አባልነትና በአባልነት በመልካም ተሳትፎዋ የምትታወቅን እህት የእደሩ የኮሚቴ አባላት ግንባር
ፈጥረው ከአባልነት በማሰወገዳቸው፤ በርካታ አባላት ተበሳጭተዋል። የሚገርመው ነገር ጉዳዩን በቀላሉ መፍታት
ባለመቻሉ ወደ ሂዩማን እራይት (Human right ) ተላልፎ ጉዳዮ በፍረድቤት እየታየ ነው። ሲለኝ እኔም በመገረምና
መደነቅ ፤ ተሞልቼ በትምህርት ቤት የተወያየንበት ጉዳይ እንደሆነ እንኳን ሳላጫውተው፤ ግን ለመሆኑ የእድሩ አላማ
ምንድነው? ለምንሰ ተቋቋመ ? ብዬ ጠየቅኩት ? መልሱንም ሲሰጥ እንዲህ ሲል ጀመረ፤

ተጨማሪ ያንብቡ:  የዘመን መለወጫ መልእክቶቻችንና መሪሩ እውነታ - ጠገናው ጎሹ

አላማውማ የተቀደሰ ነበረ። በውጪ የሚኖርውን ኢትዩጲያዊ በማሰባሰብ የተቸገረውን ለመርዳት፣ አልፎ ተረፎም
ሀዘን ሲደርሰ በቅርብ ሆኖ እርሰ በርሰ መጽናናት የሚቻልበትን ሁኔታ በማመቻቸት ለመረዳዳትና፣ ከዚህም በላይ አንድ
አባል በድንገት በሞት ቢለይ አሰከሬኑን ወደሃገርቤት መላክ ካለበት የሚያሰፈልገውን ወጪዎችን በመሸፈን ትብብርና
እርዳታን የሚያደርግ ። መላክ ከሌለበትም በዚሁ በሚኖርበት አገር አሰፈላጊውን ወጪ በመሸፈን ተዋጾ የሚያደርግ በጎ አላማ ያለው በከተማችን የተቋቋመ አንጋፋው ማህበር ነው በመልካም ሰነምግባሩ ለሌሎች አዲሰ ለተቋቋሙት መልካም
አራአያ በመሆን ፋንታ ድርጊቱ አሳዛኝ ሆነ እንጂ።

ዳሩ ምን ያደርጋል በአሰተዳደር ድክመትና ብቃት ማነሰ፤ በቁም እየተቀባበርን ተቸገርን እንጂ፤ በማለት ቀጠለ ።
ወቸው ጉድ፤- በውሰጥም በውጪም በርካታ በጎ ሰራዎችን እንዳልሰራን፤ አሁን ግን እየሄድንበት ያለነው አቅጣጫ እጀግ
አሳዝኖኛል። “እረ ፤ ሰንቱ” ብሎ…በረጅሙ በመተንፈሰ ሃዘኑን ሲገልጽልኝ፤ በእውነትም ልቤ ተነካ፤ አዘንኩ አባል ሆኜ
በሰበሰባ ቦታ በመገኝት መሰተካከል ሰለሚገባቸው ነገሮች ሀሳብ መሰጠት ባልችልም በኢትዮጲያዊነቴ የተሰማኝን መገለጽ
እችል ዘንድ ብዕሬን አነሳሁ እላችዃለሁ። አዎ ያሳዝናል። እኛ ኢትዮጲያዊያኖች ከሕብረታችን ይልቅ ልዩነታችን እየጎላ
ባደባባይ እየወጣ መሰማቱ በጣም ያሳዝናል፤ያማልም። እሰቲ ልብ ብላችሁ ተመልከቱት ቸግር ሲደርሰብኝ ይረዳኛል ሰሞት
ይቀበረኛል ብለው ወደውና ፈቅደው ለ አመታት የአባልነት መዋጮ ሲከፍሉ ቆይተው በተልካሻ ምክነያት ውጣ፤ ውጪ፤
የሚል ፍርደገምድላዊ የአሰተዳደር ወሳኔ ሲፈጸምና ጉዳዩን በውሰጥ አሰተዳደር ቅን በሆነ መንገደ ተመልክቶ በጎ የሆነ ውሳኔ
መሰጠት ሳይቻል ቀርቶ ወደ ፍርድቤት መድረሱ በግሌ እጀግ አሳዝኖኛል፡፡

የበርካቷችንም ወንድሞችና እህቶች ልብም ሰብሯል አሰቆዘሟል። ለምን ቢባል እንደባሕላችን “እድር” በሀገራችን
ከፍተኛ የሆነ የመሀበራዊ መገናኛ ምሰሦ ነውና ነው። እሰከማውቀው ድረሰ ከእድር ሰው ተባረር ሲባል ሰምቼ አላውቅምና
ነው። የእድር መዋጮ መክፈል ላልቻለ ድንኳን እንዲተክል ወይም የእድር እቃ እንዲያወጣ ሲወሰነበት እንጂ ሲባረር
አላውቅምና ነው። እሱ ድሮ ቀረ ብላችሁ እንደማትመልሱልኝ ተሰፋ በማድረግ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ኢዜማና የመግለጫ ፖለቲካ ጨዋታው  (ጠገናው ጎሹ)

ፍርድቤቱም ምን ያኸል እንደሚታዘበን፣ አልፎ ተርፎ ኢትዮጲያዊያኖች፤ እንኳን በቁማቸው ተሰማምቶ
መኖርና፤ ለመሞትም አልታደሉም፤ ብለው ከፍተኛ ትዝብት ላይ እንደሚጥሉን ለመገመት አልችገርም።
በእኔ እይታ ለዚህ አይነት አሳፋሪና አሳዛኝ ውደቀት ያበቃን በግልጽና በጋሀድ እንደሚታየው ያሰተዳደር ብቃት ማነሰ ነውና
፤ እንዲህ አይነት የማቻቻል፤ የማግባባትና እንደ ባሕላችን የማሰማማት አሰተዳደር በመሀበራዊ ኑሮአችን እንዳይጎለብት
በክፋትና በጠባብነት በሰመ ኮሚቴ አባልነት ተሰልፈው ያሉትን ወንድሞችም ሆኑ እህቶች ልቦና ይገዙ ዘንድ ከህሊናችው
ጋር ይነጋገሩ ዘንድ፣ ከራሳቸውም ጋር ይታረቁም ዘንድ የዘወትር ጸሎቴ ነው። ወያኔዎችም ከሆኑ ፍርዱ ከላይም አይቀርምና
ወደሕሊናችሁ ተመለሱ ከማለት አልቦዝንም።

አባላትም እንዲህ ያለ የራሰን ገበና በመወያየትና በመቻቻል ኮሚቴው መፍታት ለምን እንዳልቻለ የመጠየቅ
መብታቸውን ተጠቅመው ብቃት የሌላቸውን ኮሚቴዎች ብቃትና አርቆ ማሰተዋል በሚችሉ መተካቱ፤ አላሰፈላጊ ካልሆነ
የፍርድቤት ውጣውረድና የፈርድቤት ወጪ አልፎተርፎም መሳለቂያ ከመሆን ያድናል እና ይታሰብበት እላለሁ። ከዚህ
የከፋም አሳዛኝ ደርጊት ከመፈጸሙ በፊት መቻቻልን እናዳብር። ሳይሞቱሰ በቁም መቀባበር መቼ ይሆን የሚያበቃው
እያልኩ አባካችሁ ሌላ አሳዛኝ ድርጊት ከመፈጸሙ በፊት በፍጥነት መላ በሉ። ለዛሬው የታዘብኩትን በዚህ መልክ ጀባ ልበል
ብዪነውና፤ በጥሞናና በቅንነት እንድትመለከቱት አደራ እላለሁ። በቸር ይግጠመን።

አመሰግናለሁ ። ከታዛቢ አነዱ

Share