ኦኖሌ፡-ሀርከ-ሙራ

እንዲህ ነው በ1860ዎቹ ንጉስ ሚኒሊክ ገና አፄ ሳይባሉ አፄ ቴዎድሮስ ሸዋን ባስገበሩበት ወቅት የተወሰኑ የጎንደሬ ሰራዊት አባላት በሸዋ እንዲቀሩ ተደርጎ ነበር፡፡ እነዚህ የጎንደርና የወሎ ፈረሰኞች ከንጉሥ ሣህለሥላሴ ዘምን ጀምሮ በአርሲና በጨርጨር ሰፍረው ነበር፡፡ አፄ ምኒሊክ ብዙውን ጊዜ በአርሲና በሐረርጌ በማቅናት ዘመቻው በኦሮሞ ላይ ጭፍጨፋ እንደፈፀሙ ተደርጎ ተወርቷል ብዙ ተብሏል፡፡
መራሩ ሀቅ ግን ይህ ነው፡፡

ኦኖሌ፡-ሀርከ-ሙራ

ከማርቆስ ወልደዮሀንስ ዶ/ር
drmarkjohnson@yahoo.com

በአኖሌ የተቆረጠው የማን እጅ ነው? በሂጦሳ አኖሌ የአንድ ኩሩ ኢትዮጵያዊ አርበኛ እጅ ተቆርጧል፡፡ ይህ ሰው ልጅ አበበ ኮላሴ ብሩ ይባላል፡፡ታሪክ ፀሃፊዎቹ ተክለፃዲቅ መኩሪያና ብላቴን ጌታ ኀሩይ ወልደሥላሴ በታሪክ መዛግብቶቻቸው የልጅ አበበን ስም በመጥቀስ የአባታቸውን ስም ለመጥቀስ ያልፈለጉበት ዐብይ ምክንያት ቤተሰቡ በሐረርጌና በሸዋ በነበረው ከፍተኛ ተሰሚነት ነው፡፡ ፊታውራሪ ተክለሃዋሪያት ኃይለሥላሴን ለማንገስ በቅድሚያ የጎንደሬውን ጦር ማሳመን ያስፈልጋል እንዳሉት ለልጅ አበበ አባት ሰም አለመጠቀስ ዋነኛው ምክንያት ፊታውራሪ ኮላሴ ብሩ ይመሩት የነበረው የጎንደሬ ጦር የነበረው ተዳማጭነት እንዲሁም በፍርድ አሰጣጡ ላይ ፍትሐ ነገስቱ በሚያዘው መሰረት ንጉስን ለመግደል መሞከራቸው ይቅርታ የማያሰጥ ወንጀል በመሆኑ ቤተሰቡም እንደዘመኑ ህግ በማመኑ ነው፡፡

በዐፄ ምኒሊክ አጎት በመርዕድ አዝማች ኃይሌ በተጠነሰሰው መፈንቅለ መንግስት ጎንደሬው ደጃዝማች መሸሻ ወርቄን ጨምሮ ከመቅደላው እስር ቤት አፄ ምኒልክን እንዲያመልጡ የረዱ የምኒሊክ ዘመን ታላላቅ ሰዎች ምኒሊክን በመርዕድ አዝማች ኃይሌ ለመተካት የወጠኑት ውጥን ከሸፈ፡፡ ልጅ አበበ ኮላሴ የተመረጠው ለአፄ ምኒልክ ከነበረው ቅርበት የተነሣ ምኒልክን ከደርብ ላይ ገፍትሮ በመጣል ለመግደል ስምምነት አድርጎ ነው፡፡ ልጅ አበበ ኮላሴ የስሜኑ ራስ ውቤ እና የእቴጌ ጣይቱ የስጋ ዘመድ ነበረ ለእቴጌይቱ ከነበረው ቀረቤታና በንጉስ ምኒልክና በእቴጌ ጣይቱ መሃከል በሰተመጨረሻ ጋብቻ እንዲፈጸም ምክንያት የሆኑ የሰሜኑና የሸዋን መሳፍንቶች በማቀራረብ ረገድ ክፈተኛ ሚና የነበራቸው ልጅ አበበ ኮላሴ በእልፈኝ አስከልካይነታቸው ከእራሳቸው የተሻለ ምኒልክን የሚቀርብ ባለመገኘቱ የዐፄ ምኒልክ አጎት በሆኑት በመርእድ አዝማች ኃይሌ አማካኝነት ተመለመሉ፡፡ ልጅ አበበ ኮላሴ ወደ ሸዋ የመጣው ምኒሊክ ገና የሸዋ ንጉስ በነበሩበት በ1860 ዎቹ አጋማሽ ነው፡፡ ከመቅደላው ጦርነት በኋላ አባታቸው ሰራዊታቸውን ይዘው ወደ ምኒልክ በመግባታቸው የጎንደሬ የላስቴ እንዲሁም የሸዋ ሰራዊት እጅግ የተከበረ ነበር፡፡በዚህ ሰራዊት ውስጥ ፊታውራሪ ዋዠቁ እንዲሁም የአቶ አዲሱ ለገሰ አያት ቀኛአዝማች ቀረኩራት ነበሩበት፡፤ ይህ ጦር የጎንደሬ ጦር በመባል የሚታወቅና በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች አገርን በማቅናት ረገድ ተወርዋሪ ኃይል የነበረ የሰራዊት ክፍል ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከግብጾች እንማር - ግርማ ካሳ

ይህ ታላቅ ሰራዊት በመጀመሪያ በእንጦጦ ቀጥሎም አሁን ግቢ በሚባለው ስፍራ ከከተመ በኋላ ምኒልክ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በአደረጉት እንቅስቃሴ ከፍተኛና ጉልህ ሚና ተጫውቷል፡፡በእነዚህ የተለያዩ ዘመቻዎች አንቱ የተባለ ክንውን ከፈፀሙ በኋላ ስማቸውን የታሪክ መዝገብ ሳያየው ካለፈ ቤተሰቦች ውስጥ ቤተ-ኮላሴ ወይም ወረ-ኮላሴ የሚባሉት ቤተሰቦች ዋንኞቹ ናቸው፡፡

በሶዶ ፣በቤተ ጉራጌ ፣በአርሲና ባሌ ፣እንዲሁም በሐረርጌ ወደ ማዕከላዊ መንግሰት መምጣት የዚህ ቤተሰብ ሚና ቀላል አልነበረም፡፡ ምስጋና ለፈታውራሪ ተክለሐዋሪያት ኦቶ ባዮግራፊ ወደ አድዋ የዘመተው አብዛኛው የራስ መኮንን ጦር በበላይነት የሚመራው በወንድማማቾቹ በፊታውራ ኮላሴ እና በፊታውራሪ አለሙ የጎንደሬ ሰራዊት መሆኑ በአፅንኦት የተጠቀሰ ቢሆንም ይህንን ታሪክ ፈልፍሎ በማውጣት ረገድ የታሪክ ምሁራኖቹ ከተወሰነ ስፍራ ላይ በመወሰናቸው ዛሬ ኦነግና አህዴድ ለሚያናፋሱት አዳዲስ የፈጠራ ወሬዎች ህዝቡ ሰለባ ሆኗል፡፡በአድዋ ጦርነት የሐረርጌን ሰራዊት አድዋ ድረስ ይዘው በመሄድ የተዋጉት ፊታውራሪ ኮላሴ ብሩና ቤተሰባቸው ወደ አድዋ የዘመቱት ልጃቸው ልጅ አበበ ኮላሴ በምኒሊክ አጎት በተጠነሰሰው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ እጅና እግር ካጡ ከአስራ አምስት ዓመት በኋላ ነው፡፡ የልጅ አበበ እጅና እግር መቆረጥ የፈታውራሪ ኮላሴ ብሩ ና ልጆቻው እንዲሁም ከጎንደርና ላሰታ ተሰባስቦ የተከተላቸውን ሰራዊት በአገሩ ላይ እንዲደራደር አላደረገውም፡፡ በአድዋ ጦርነት በራስ መኮንን መሪነት ታላላቅ ጀብዱዎችን ፈፅመው አገራቸውን ኢትዮጵያን አኩርተዋል፡፡ በአፄ ምኒልክ ይህንን መሰል ቅጣት ለመቀጣት የመጀመሪያው ቤተሰብ ኦሮሞ ወይም ትግሬ ሳይሆን የአማራ ልጅ ነፍጠኛ ነው፡፡ ይህም የተፈፀመው በልጅ አበበ ኮላሴ ላይ ነው፡፡ፊታውራሪ ኮላሴ ብሩ ከእረፍታቸው በኋላ የደጃዝማችነት ማእረግ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ደጃዝማች ኮላሴ ብሩ(ሐረርና የአውራጃዋ ግዛት የሚለውን በ1950ዎቹ ይታተም የነበረ መጽሔት) ማየት በቂ ነው፡፡

በልጅ አበበ ኮላሴ ላይ የደረሰውን ቅጣት በአሁን ዘመንና መነፅር አይቶ ምኒልክ ትክክል ሰርተዋል አልሰሩም ለማለት በወቅቱ የነበረውን የዕውቀት የንቃተ ህሊና ደረጃና የፍትህ ስርዓት አንፃር መገምገሙ ተገቢ ነው፡፡ በተመሳሳይ ዘመን በአውሮፓ ጊሎቲን የአንገት መቁረጫ ማሽን ተዘጋጅቶ አንገት የሚቆረጥበት ዘመን ጋር ብናስተያየው በእኛም ሀገር ይፈፀም የነበረው ተመሳሳይ ድርጊት መሆኑን ማስተዋል ይገባል፡፡እንደአጋጣሚ በአኖሌ ጦርነት አልተደረገም፡፡ ጥንትም ይሁን ዛሬ አኖሌ ከተማ ሳትሆን ጥቂት ባለርሰቶች ይኖሩባት የነበረች ጠፍ መሬት ነበረች፡፡ መቶ ሃያም ሆነ መቶ ሰላሳ ዓመት ሩቅ አይደለም፡፡ በጣም ያልራቀ ዘመን በመሆኑም ድርጊቱ የተፈጸመባቸው ቤተ-ኮላሴዎች ጦር ሰብቀው አገር ተሳድበው አልኖሩም፡፡ ስርዓቱን እንዲሁም የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በማስከበር ተፋለሙ እንጂ፡- ከእረፍታቸው በኋላ የደጃዝማችነት ማዕረግ የተሰጣቸው የኮላሴ ብሩ ቤተሰቦች ንጉሰ ነገስቱ በጄነቭ የተባበሩት መንግስታት ስብሰባ ሲሄዱ አገሪቱን አደራ ብለው ከተሰናበቷቸው ውስጥ ናቸው፡፡ ፊታውራሪ ጓንጉል ኮላሴ በአኔሌይ ከኢጣሊያ ወታደሮች ጋር ተፋልመው ያገኙትን ውጤት በማድነቅ ወደ ጄኔቫ ያመሩት አፄ ኃይለስላሴ ከስደት መልስ እነዚህን የታሪክ ባለውለታ ቤተሰቦች አላኮሯቸውም ታሪካቸው ደምቆና ጎልቶ እንዲወጣም አላደረጉም፡፡ ይህ ታሪክን አድበስብሶ ማለፍ አዳዲስ የፈጠራ ታሪኮች እንዲፈበረኩና በዚህም ብዙዎች ዕዳ ከፋይ የሆኑበት ሁኔታ ታይቷል፡፡የምጣዱ ሳለ የዕንቅቡ ተንጣጣ እንዲሉ እጅና እግር የገበረው የአማራ ብሔር ነፍጠኛው ሆኖ ሳለ በኢትዮጵያ የጦርነት ታሪክ ታይቶም ሆነ ተሰምቶ የማይታወቅ የክርስቲያን ጦር ጡት ቆረጠ የሚል ማስረጃ የማይቀርብበት የሐሰት ታሪክ ትንታኔዎችን በማቅረብ በተራ አሉባልታና በሬ ወለደ የፈጠራ ታሪክ ሕዝብን መንዳት መሞከር ታላቅ ወንጀል ነው፡፡ታቦት ይዞ የሚዘምት ሰራዊት ሴትን በጥፊ መምታት እንኳን እንደወንጀል የሚመለከት ማህበረሰብ ምን ለማግኘት ምን ለማትረፍ የሴት ጡት ይቆርጣል፡፡ የአበበ ኮላሴን እጅና እግር መቆረጥና መቀጣት እንዲሁም የኤርትራ ባንዳ ሰራዊትን እጅና እግር መቆረጥ የተረኩ የታሪክ ጸሐፍት ማንን ፈርተው ለምን ብለው ይህንን ታሪክ ሳይዘግቡት ቀሩ ቢባል፡ መልሱ ድርጊቱ ፈጽሞ ያልተካሄደ በመሆኑ ብቻ ነው፡፡በጣም የሚያኮራውና የሚያስደስተው ቤተ-ኮላሴዎች የፖለቲካ ትርፍም ሆነ ሌላ ነገር ለማግኘት በየትኛውም ስርዓትም ሆነ ዘመን ይህንን ታሪክ አጉልተው አልተናገሩም አልዋሹም አልቀጠፉም፡፡ኢትዮጵያን ግን ጠበቁ፡፡ ሞቱላት ደሙላት፡፡ይህ ታሪክ የኦህዴድ ታሪክ የኦነግ ታሪክ ቢሆን ስንት ዘርፍና ቅጥያ ወጥቶለት ሌላ ሃውልት በቆመ ነበር፡፡ይህ ታሪክ የአንድ ኩሩ ኢትዮጵያዊ ቤተሰብ ታሪክ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የመርገም አርማ የጥላቻ ዜማ! - ከቴዎድሮስ ሃይሌ

ልጅ አበበ የተቀጣበት ስፍራ የአሁኗ አኖሌ ነበረች፡ በስፍራው የነበሩ ሰዎች ልጅ አበበ ኮላሴን በኦሮሚኛ ሃርከ ሙራ -እጀ ቆራጣ ለማለት የሰጡት ስም ዛሬ ከበሮ እየተደለቀበት ያለ በተለይም ድህረ ኢህአዴግ ሀርመ ሙራ የምትል ቅጥያ የኦነግና የኦህዴድ ካድሬዎች በማከላቸው ጡት ጭምር ተቆርጧል አስብሎ በሀሰት የፖለቲካ ትርፍ ፕሮፓጋንዳና ሃውልት በመስራት በሚለዮኞች የሚቆጠር ብር ቢዝነስ በሚያጧጡፉ ግለሰቦች ሀሰት እውነት ተደርጎ መዘገቡ አሳፋሪ ነው፡፡ እውነት ነው የልጅ አበበ ኮላሴ ቀኝ እጅና ግራ እግር የተቆረጠው በንጉሳዊ ትእዛዝ ነው ፈፃሚዎቹም ከአሁኗ እንጦጦ ወደ አርሲ ሄደው የሰፈሩት ወረ-ሂጦመሌ በሚባል የሚታወቁት የኦሮሞ ጎሳዎች ነው፡፡ የተገላቢጦሽ እንዲሉ በፈሰሰው የነፍጠኛው የልጅ አበበ ኮላሴ ደም ዛሬ ከፍተኛ የፖለቲካ ትርፍ ለማትረፍ የሚንቀሳቀሱ ዋሾዎችን ማየት አሳፋሪ ከመሆኑም በላይ መንግስት ጉዳዩን በዝምታ መመልከቱ አሳሳቢም ጭምር ነው፡፡መንግስት በዚህ ሃውልት መቆም አምንበታለሁ ካለም በበደኖ በአሶሳ በአርሲ ነገሌ በአርባጉጉ በጂማ አንገታቸው ለተቀላ ደማቸው እንደጅረት ለፈሰሰ ሰማዕታት ሃውልት የማቆም ግዴታ ይኖርበታል፡፡
የፊታውራሪ ኮላሴ ቤተሰቦች በሁለተኛው የኢትዮ ኢጣሊያ ወረራ ወቅትም ከፍተኛ ተጋድሎ አድርገዋል፡፡

ፊታውራሪ ጓንጉል ኮላሴና ወንድማቸው ኃይለማሪያም ኮላሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ታንክ የማረኩ መሆናቸውን ጳውሎስ ኞኞ አልተወራላቸውም እንጂ በማለት በኢትዮጵያና በኢጣሊያ ጦርነት ወቅት ስለፈፀሙት ተጋድሎ በመጽሐፉ ዘግቧል፡
ሻምበል መብራቴ ኮላሴ የጥቁር አንበሳ ሰራዊት አባል ማይጨው በጀግንነት ወድቀዋል ተክለፃዲቅ መኩሪያ ዘግበውታል

የይፍቱ ስራ ኮላሴ ልጅ ፊታውራሪ ነገደ ዘገየ በጎንደርና በሐረር ከኢጣሊያ ጋር በመዋጋት ከፍተኛ ተጋድሎ ፈጽመዋል፡፡ ልጅ አበበ ኮላሴ በፈጸሙት ስህትት ተቀጥተዋል፡፡ እጅና እግራቸው ከተቆረጠበት አርሲ አኖሌ በተቆረጠ እጃቸው አንበሳ ገድለው ለአፄ ምኒልክ የአንበሳ ጎፈር ልከዋል፡፡ ምኒልክም የእጄን በእጄ በማለት መፀፀታቸው አሁን ድረስ የሚወራ ታሪክ ነው፡፡ እናም በአማራው ላይ ለተፈፀመው ድርጊት በኦሮሞ ላይ እንደተፈፀመ ተደርጎ በፈጠራ ድርሳን የሚወራው ወሬና ሕዝብን ከሕዝብ የማለያየት እንቅስቃሴ በአስቸኳይ መቆም አለበት፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  በረከት ነው መርገምት? -ጠገናው ጎሹ

12 Comments

  1. Tola hake wota min tihon tadiya zim bileh beneger batichmelalek tiru new masamegna kaleh akrib alblzya

    • Esu
      These people do not deal with evidences. For instance, if one sincerely believes that the earth is flat, you may be able to change that belief by providing scientific evidence to the contrary, including satellite photos carrying his face on it, but not so with the Oromo first squads. They pick and choose what to believe. One can conclude that these squads are not from this planet, may be, just may be they are from parallel Universe. That Universe being Garyosh Sirate mahber!!!!! At the dawn of freedom, we will ask them if we can build a memorial for tplf victims.

    • Kkkkkk..’.Libwolde eko ‘reference /Matakesha /yelewum. But the Dr has given enough references written by the previous famous writers of the era. You better differentiate between Fact and Fiction. Great Dr!

  2. Tadia min yetebes? Kehawultu meretu yitekim neber! Silcha kelkelo, Kelokelo silicha- – –
    Obo Tomosa nefsachew yimarachew.

  3. Dear poor Dr.

    Do you know the meaning of Kolase or wore-Kolase, is that an Amharic name?

    Check you fact again, before you claim Abebe is Amhara Neftegna

  4. This narration further proof that Menelik has been practicing the cutting both on indivduals as well as communities. Other important point is Menelik has evicted Oromos from their village and made them to scattered in all direction as the case of wara-lixosa. The writer also ignorant of the roots of wara Kolasse as they are Oromos.

  5. Thank you !!! but i see no reason to ask woyane to pay heed for the distorted and fabricated lies of the olf and opdos knowing that the woyane is manipulating the whole show using these extremist olf and opdo elements as chess piece.

Comments are closed.

Share