የረዳት አብራሪ ኃይለመድህን ተግባር

ናትናኤል ካብትይመር (ኦስሎ ኖርዌይ)

ስለ ረዳት አብራሪ ኃይለመድህን ብዙ ተብሏል ብዙ ተፅፏል ቢሆንም የጀግንነት ተግባሩ ስላኮራኝ እኔም የበኩሌን ልበል። ጥቂቶች በተለይም የወያኔ ህወሃት አባላትና አቀንቃኞች እንዴት ጀግና ይባላል ሲሉ እያስተዋልኩ ነው ፡ ነገር ግን እኔም ሆንኩ በርካታ ሰዎች ረዳት አብራሪውን ጀግና ያልንበት ዋነኛ ምክንያት “በጭቆና ስርዓት ውስጥ ላሉና ብሶታቸውን ማሰማት ላልቻሉ ድምፅ የሆነና ብሶታቸው እንዲሰማ ብሎ ራሱን መስዋዕት ያረገ ሁሉ ጀግና ስለሆነ ነው” እንላለን።
በአየር መንገድም ሆነ በተለያዩ ከፍተኛ አገልግሎት ሰጪ የመንግስት ተቋማት በሚያገለግሉ ከወያኔ ዘር ወይም አባል ባልሆኑ የተለያዩ ባለሞያዎች ላይ ገሃድ የወጣ የመብት ረገጣ እየደረሰባቸው እንደሆነ እናውቃለን። በማናለብኝነትና በዕብሪት ላይ የተመሰረተ የመንግስት ጣልቃ ገብነት በርካታ ለሃገር እድገት ከፍተኛ ጥቅም የሚሰጡ ባለሞያዎችን በአግባቡ አላሰራና አላፈናፍን ማለቱን ማንም ኢትዮጲያዊ ያውቃል።
የኢትዮጲያ አየር መንገድም በተለያዩ ግዜያት የመንግስት ጣልቃ ገብነት እያማረረው እንደኖረ የቀድሞ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ግርማ ዋቄ በተለያዩ ግዜያት ለመጠቆም ሲሞክሩ አስተውያለው። የኢትዮጲያ አየር መንገድ እንደ አለማቀፍ ድርጅትነቱ ከሌሎች ሃገራት አምሳያ ድርጅቶች አንፃር ሲታይ የበለጠ የሰራትኞች ስራ መልቀቅ (Employee turnover) በእጅጉ የሚያጠቃው እንደሆነ በርካታ ኢትዮጲያዊያን ያውቃሉ። በርካታ ወጣትና አንጋፋ ባለሞያዎች በአየር መንገድ በተለያዩ ሞያዎች በአብራሪነት ፣ በበረራ አስተናጋጅነት ፣ በቴክኒሺያንነት ፣ በአስተዳደር ፣ በማርኬቲንግ እና በደንበኞች አገልግሎት ስራ የተሰማሩ ድርጅቱ ለስልጠናና መሰል ክህሎት ማጎልበቻ ከፍተኛ ወጪ ያወጣባቸው ሰራተኞች ባለው የህወሃት ሰዎች አጉል ጣልቃ ገብነት በፈጠረው መጠነ ሰፊ አስተዳደራዊ በደል ተማረው ስራቸውንና የሚወድዋትን ሃገራቸውን ጥለው ወደተለያዩ የሌላ ሃገራት አየር መንገዶች ሄደው እንደሚሰሩ የሰነበተ የአደባባይ ሚስጥር ነው። በወያኔ አስተዳደራዊ መድሎና ብልሹነት በርካታ ለሃገር ጠቃሚ የህክምና ባለሞያዎች ፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራን እንዲሁም በርካታ የተለያዩ ክህሎቶች ባለቤት የሆኑ ባለሞያዎችን ሃገራችን ስታጣ መቆየቷ ሁላችንም ስናየው የኖርነው ሃቅ ነው። የእድገት ፣ የስልጠናና የደሞዝ ጭማሪን የመሳሰሉ የሰራተኞች የኑሮ ደረጃና ክህሎት ማሳደጊያ ለተወሰነ ዘርና ሰዎች ብቻ የማረግ ሌሎችን የበይ ተመልካች በማድረግ መግፋት መረን ወጥቶ በኢትዮጲያ አየር መንገድ ከፍተሻ ሰራተኛ እስከ ዋና ስራ አስፈፃሚ ድረስ የወያኔ ህወሃት አባላትና አቀንቃኞች መቆጣጠራቸውን በሌሎች መንግስታዊ ተቋማትም እንዲሁ መሆኑን ማንም ኢትዮጲያዊ ያውቃል።
ረዳት አብራሪ ኃይለመድን በአጠቃላይ የወያኔ ህወሃት አካሄድ አጉል የሆነና ሃገርን የሚጎዳ መሆኑ እንዲሁም በተለያዩ መንግስታዊ ተቋማት የተንሰራፋው አስተዳደራዊ መድሎ በሃገር አቀፍ ደረጃ ስር ሰዶ ሃገራችንን ባለሞያ አልባ እያረጋት እንደሆነ የተረዳ መሆኑና ለዚህም የጀግንነት ተግባር እንደፈፀመ እንዲሁም ለሌሎች በሃገራቸው ተምረው በሞያቸው ሃገራቸውን ለማሳደግ ፣ ህዝባቸውንም ለመጥቀምና ለማገልገል አላሰራ ላላቸው ጨቋኝ አገዛዝ ድምፅ መሆኑን ሁላችንም ገብቶን ጀግና ብለነዋል።
አሁንም ሁልግዜም አምባገነናዊነትን አጥብቀን እንቃወማለን !!
natnaelkab@gmail.com

ተጨማሪ ያንብቡ:  ልብን የሚነካዉ የኢትዮጵያዉያን ጉዞ በሳዑዲ አረቢያ

6 Comments

  1. በእውነቱ ሃይለመድህንን ጀግና የሚል የጀግንነት ምንነት በውል ያልተገነዘበ ግለሰብ መሆን አለበት በዚህ ድርጊት አየር መንገዳችን ላይ የተወሰነ ጉዳት ሊደርስ ይችል ይሆናል ይህ ደግሞ በአገራችን ጥቅም ላይ የሚደርስ ጉዳት ነው የሚሆነው እንጂ በወያኔ ላይ የሚደርስ ቅንጣት ያክል ጉዳት አይኖርም በኢትዮጵያ ህዝብ አንጡራ ሀብት የቀሰመውን ዕውቀት ያስተማረውን ህዝብ ጥቅም ለመጉዳት ሲያውለው መመልከት በጣም ያሳዝናል በዚህ ድርጊት ወያኔ ይጎዳል ብሎ ማሰብ ትልቅ ጅልነት ነው ወያኔን የሚጎዳ ነገር መለየት አለመቻል ደግሞ የበለጠ ጅልነት ነው

  2. @Kurabachew,

    Do you have another approach how to oppose the TPLF dirty politics as an individual at an international level in provided that you are in his position? If you have alternatives I really appreciate you. Otherwise, with out justification if you write a message of opposing what PILOT Hailemedhin did ids just like WOLEFENDY. Do not worry about the name of Ethiopia at this time. More than what Hailemedhin did the world kno Ethiopia very much in positive and negative sides. Of course, more on the negative sides – remember recently what the Saudi did on the Ethiopian nationals, see all reports of the international community classification where Wthiopia belongs ( its rank is all above the last rank). In additon, the recent report released from the world bank and the TPLF administration confirm that more than 6,000,000 people need food assistance. All these group of people need food assistance through out the year.i.e., the country is grouped in to chronically food aid need country. Do you have more argument point about our country position in the world. That is why I said we Ethiopians national pride is diminished since long time ago not by what Hailemedhin did it. You understand my friend? Think over it!! All justification points help Woyanes on behalf of Ethiopia did not work.

  3. Getaw I read ur suggestion about what Hailmedhin did and tried to justify but according to my opinion what u said is wrong I know and I agree that our country is known for its positive and negative side. but this doesn’t mean Hailmedhin’s deed is a solution rather it intensifies the problem. because He didn’t go to bring bread for the needy Ethiopians. we can regain our pride by being hard working and having innovate ideas . but not by fleeing to developed countries by damaging our own country property (wealth). Even though I don’t have a difference that our country is still poor I do have a difference in the solution of alleviating our poverty. I always think separating the benefit of my people and country from the existing regime. Let God bless U my friend

Comments are closed.

Share