February 16, 2014
12 mins read

ወያኔ ለምን ይሸበራል?

ዳዊት መላኩ( ከጀርመን)

አባቶች ሲተርቱ ’’ፈስ ያለበት ዝላይ አይችልም ’’ ይላሉ፡፡ዝላዬን ተከትሎ ምን እንደሚመጣ ስለሚያውቅ በዝላይ አይሳተፍም ዝላይም አይወድም፡፡የወያኔ አንባገነን መንግስት ለምን ይሸበራል ብልን ስንጠይቅ መልሱ ቀላል ነው፡፡ከባዱ እና አስካሁን ብዙ በስልጣን እንዲቆይ ያስቻለው ግን በመፍትሄው ላይ በጋራ መስራት አለመቻላችን ነው፡፡ወያኔ የሚሸበረው የህዝን ሀብት ስለሚዘርፍ፤ህዝብን ስለሚገድል፤ህዝብን የሚጎዳ ስራ ስለሚሰራ የገንዛ ስራው ነው ጥላ እየተከተለ እንደሸበር የሚያደርገው፡፡
በራሱ የሚተማመን እና መልካም ስራ የሚሰራ መንግስት ማንም ምንም ይፃፍ ማንም የፈለገውን የፖለቲካ ድርጅት ይደግፍ ፤ማንም የፈለገውን የፖለቲካ ድርጅት ያቁዋቁም የሰራው መልክም ስራ ዋስትናው ስለሆነ ምንም ይመጣብኛል ብሎ አይሰጋም፡፡ወያኔ ግን ይዞት የተነሳውም አላማም ይሁን የስልጣን ኮርቻ ላይ ከተቆናጠጠም በሁዋላ የሚሰራው ስራ የተሳሳተ በመሆኑ በራሱ ስራ እና ክፉ ሀሳብ ዘወትር ይሸበራል፡፡ወያኔ ነፃ አውጪ ነኝ እያለ የዜጎችን ነፃነት በአደባባይ የሚገፍ የመደራጀት የመጻፍ መብትን የማይፈልግ የራሱ ጥላ የሚያሰደነብረው ተሸብሮ የሚያሸብር ድርጅት ነው፡፡አንድ ወቅት የወያኔው መስራች መለስ ዜናዊ የወያኔ ስልጣን የዛፍ ላይ እንቅልፍ ነው ብለው ነበር፡፡ እሳቸው ቃሉን የተጠቀሙበት ለሌላ አላማ ቢሆንም እውነታው ግን ወያኔ ሁሌም ክፉ ስራው እያባነነው ፤የንጹኃን ደም እረፍት እየነሳው ሲቃዥ እንደሚድር ሳያስቡት ያጋጠማቸውን የስነልቦና ችግር ነው ባደባባይ የዘረገፉት፡፡ለወያኔ የሽብር ምንጮች
1. ከመነሻው ዘርን መሰረት ያደረገ አደረጃጀት ይዘው ሲነሱ እና የኢትዮጵያ ህዝብ እንደቀስተ ደመና በልዩነቱ ውስጥ ባንድነት አሸብርቆ ለዘመናት ተጋብቶ ተዋልዶ አብሮ የኖር የራሱ የሆነ የፍልስፍና የባህል የአኑዋዋር ዘዴ የሚከተል በመሆኑ የስታሊን ፍልስፍና ኢትዮጵያ ውስጥ በቀላሉ እንደማይተገበር ያውቃል፡፡ስለዚህ ከመነሻው የነበረውን ታሪክ ፤ባህል፤አንድነት ማፈራረስ በመሆኑ ሰዎች ባንድነት በሀገራዊ ስሜት የጋራ አጀንዳ ይዘው የሚመጡ፤ የህዝብን ጥቅም ያስቀደሙ ጥያቄዎች ሁሉ ያሸብራቸዋል፡፡
2. ወያኔዎች ዋናው ችግራቸው የስልጣን ጥማት በመሆኑ ስልጣኑንም የሚፈልጉት ህዝብን በማስተዳደር ለሀገር እና ለወገን የሚጠቅም ስራ ከመስራት ይልቅ ስልጣንን መሰረት አድርገው የህዝብን ሀብት ያላግባብ ስለሚዘርፉ ስልጣናቸውን ባጡ ማግስት ያን ሁሉ ነገራቸው የሚያጡ ስለሚመስላቸው የሚዘርፉት የሀብት መጠን ፤ሀብቱን ያገኙበት ምንገድ ህገወጥነት ሁሌም ከዛሬ ነገ ይነቁብናል እያሉ ይሸበራሉ፡፡
3. የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎችን በማጥፋት በአማራው መቃብር ላይ ስልጣናቸውን ማደላደል ስለሚፈልጉ ከዚህ ወገን የሚመጣ የህዝብ ጥያቄ ሁሌም ያሽብራቸዋል፡፡በተለይ ጫካ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ በአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ላይ የፈፀ ሙት ከፍተኛ ወንጀል ያሸብራቸዋል፡፡ለአማራው ያላቸውን ጥላቻ ባያክልም በሌሎች ብሄረሰቦች ላይም ምንም እምነት የላቸውም፡፡በተለይ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ብሄሮች አትብቆ ይፈራቸዋል፡፡ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የኦሮሞ ተናጋሪ አንድ ቀን ሊያምጽብኝ ይችላል መቢል ድምጻቸውን ከፍ አድርገው በጮሁ ቁጥር የለመደው የሽብር ዛር ተነስቶ ያነገፈግፈዋል፡፡
4. ሌላው ወያኔን የሚያሸብረው የመገናኛ ብዙሀን ነው፡፡ ለህዝቡ እውነቱን በመደበቅ የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ሲለሚግተው ህዝቡ እውነቱን ካወቀ ስልጣኔን ላጣ ነው፡፡ስልጣን ካጣሁ ደግሞ እንደሰው ለመኖርም የሚያስችለኝ መልካም ነገር ስለሌለኝ እጠፋለሁ ብሎ ማሰብ ሌላው የሽብር ምንጩ ነው፡፡ለዚህ ነው እንግዲህ ኢሳትን ጨምሮ የነፃው ፕሬስ ለወያኔ የሽብር ምንጪ የሚሆኑት፡፡
5. ወያኔ ህዝብን አደንቁሮ ፣አደህይቶ እና አዋርዶ መግዛት ስለሚፈልግ ሰዎች ባወቁ ቁጥር ፤በኩራት ቀና ማለት ከጀመሩ ፤ እንዲሁም የዕለት ኑሮዋቸውን ባሸነፉ ቁጥር ነገ ከምግብ ያለፈ ጥያቄ ሊያነሱ ይችላሉ ብሎ በማሰብ በሰዎች ማወቅ፤በማግኘታቸው እና በልበ ሙሉነታቸው ሁሉ ይሸበራል፡፡ከምን ተነስቶ ነው እንዲህ ኩራት የተሰማው ማን አይዞህ ብሎት ነው ከጀርባው ምን ቢኖር ነው በማለት ይሸበራል፡፡
6. ሌላው ትልቁ የወያኔ የሽብር ምንጭ የፖለቲካ ድርጅቶች ናቸው፡፡በዚህ በኩል የሚመጣው ችግር ከሁሉ የከፋ እንደሚሆን ያውቃል፡፡ የስርዓት ለውጥ ለማምጣት ህዝቡን አደራጅቶ የሚመራ ሁሉን አቀፍ የሆነ የዜጎችን መሰረታዊ ጥያቄዎች አንግቦ የተነሳ የፖለቲካ ድርጅት የወያኔን አንባገነን መንግስት ነፍስ ለመውሰድ የተላከ መላከ-ሞት ስለሚመስላቸው ጠንካራ የፖለቲካ ድርጅት በተፈጠረ ቁጠር የወያኔ መሰረት ያናጣል ፡፡ከላይ እስከታች በከፍተኛ ሽብር ስር ይወድቃሉ፡፡
7. ወያኔ የዜጎችን በነጻነት የማምለክ ሰባዊ መብታቸውን በመግፈፍ ህዝቦች እምነት የለሽ የወያኔ ተላላኪ እና ጋሻ-ጃግሬ እንዲሆኑ ስለሚፈልግ እና ማንኛውም እምነት ደግሞ መልካም ስራን ፣ፍቅርን፣ሰላምን፣ይቅር ባይነትን አልፎተርፎም ከሞት በሁዋላ ስላለው ህይወት በማስተማር ህዝብን ለእውነት እንዲቆም ስለሚያደርጉ የምዕምናን ህብረት ያሸብረዋል፡፡ ለዚህም ነው ማህበረቅዱሳን ፤መጅሊስ ሳማቸው ሲጠራ ቁጥር የሚያንዘፈዝፈው፡፡
8. ሌላው ወያኔን የሚያሸብረው ምርጫ ነው፡፡በህዝብ ያልተመረጠ መንግስት ስልጣን ከሕዝብ በሚወጣ ድምጽ ብቻ ነው ስልጣን መያዝ ያለበት በተባለ ቁጥር መበርገግ መሸበር የሚያስገርም ነገር አደለም፡፡ምርጫ በመጣ ቁጥር የሚይዝ የሚጨብጠውን ነው የሚያጣው፡፡ሰራዊቱን ከቦታ ቦታ ያዘዋውራል፤መድፍ ታንክ ሳይቀር ቤከተማው እንዲርመሰመስ ያደርጋል፡፡

ከላይ ለማየት አንደሞከርነው አንድ ሻንበል ጦር የሌላቸው የፖለቲካ ድርጅቶች ወያኔን ስማቸው በመጠራቱ ብቻ ያሸብሩታል፡፡ዛሬ ወያኔ የሚሸበረው በሰማያዊ ፓርቲ፤ በአንድነት ፣በግንቦት ሰባት እና በሌሎችም ነው፡፡ እነዚህ ድርጅቶች ሰራዊት ስላላቸው የጦር መሳሪያ ስለታጠቁ አደለም ወያኔን የሚያሸብሩት፡፡እነዚህ የፖለቲካ ድርጅቶች ጥያቄዎቻቸው የህዝብ ጥቄዎች በመሆናቸው ወያኔን ማሸበራቸው የማይቀር ነው፡፡ የሚያነሱዋቸው የፍትህ ፤የነፃነት እና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ወያኔ አስቦት የማያውቀው ነገር በመሆኑ ከራሱ የተፈጥሮ ባህሪ በመነሳት ስማቸው በተጠራ ቁጥር ይሸበራል ፡፡ ነገር ግን እየተሸበረ ያለው በግድ ሳይፈልጉት ስልጣን ኮርቻ ላይ ተቆናጦ እንደመዥገር ደም እየመጠጠ ያለው የወያኔ መንግስት እንጅ ህዝቡ የነጸነት አየር የሚተነፍስበት ቀን እንዲመጣ በመጠባበቅ ላይ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ባሁኑ ሰዓት አሸባሪ ድርጅት ወይም ግለሰብ ሳይኖር ወያኔ በራሱ ተሸብሮ እያሸበረ ይገኛል፡፡በአለም አቀፍ ደረጃም እስካሁን ከተቋቋሙ የኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ አሸባሪ የተባለ ወያኔ እና ወያኔ ብቻ ነው፡፡ወያኔን የሚያሸብረው እንግዲህ ክፉ ስራው እና ፍርሀቱ ነው፡፡እንግዲህ ለወያኔም እንዲህ እየተሸበረ ከሚኖር መፍትሄ እንዲሆነው እና ከሽብር እንዲላቀቅ የሸብር ምንጪ የሆነውን ስልጣኑን ለህዝብ በማድረግ ፍትህ ሠላም እና ዲሞክራሲ የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣ እላለሁ፡፡
ድል ለኢትዮጵያ ህዝቦች!

Previous Story

ሚኒሶታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤ/ክ ለሰላምና ለአንድነት ከቆሙ ምእመናንን የተላለፈ ማብራሪያ

EthiopiaBlueNileFalls
Next Story

የአባይ ግድብና የአገዛዙ ተቃርኖዎቹ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop