ይድረስ ለጓድ መንግሥቱ ኃ/ማርያም

ከወልደ ቴዎፍሎስ (ኦታዋ፡ ካናዳ)
tewoflos2013@gmail.com
“የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል።”
ትንቢተ ኢዩኤል 2፡32፤ ሮሜ 10፡13.

የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት እና የደርግ ሊቀመንበር ጓድ መንግሥቱ ኃ/ማርያም፡ ባሉበት በሐራሬ ዝምቧብዌ ለጤናዎ እንደምን ከረሙ? መቼም “ጓድ” ብዬ ስጠራዎ ደስታ እንጂ ቅሬት እንደማይሰማዎ እርግጠኛ ነኝ፤ ይህን መጠሪያ ስለሚወዱት፡ የትግል አጋርዎችዎን ብቻ ሳይሆን ውድ ባለቤትዎንም “ጓድ” ብለው ለመጥራት ወደኋላ አላሉምና (ትግላችን፤ “ምስጋና” ገጽ ፭)።

“ትግላችን፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ የትግል ታሪክ” የተሰኘው መጽሐፍዎ ለህትመት ከበቃ ዓመት ከመንፈቅ ቢሆነውም፡ ሰሞኑን እጄ ገብቶ አነበብኩት። እኔ ያነበብኩት ለአምስተኛ ጊዜ በአዲስ አበባ በሐምሌ ወር 2004 ዓ.ም. የታተመውን ሲሆን፡ መጽሐፉ ብዙ ጥያቄዎችን ቢፈጥርብኝም ርዕሴ እንደሚያመለክተው በመረጥኩት ጉዳይ ላይ ብቻ ይህን አጭር ጦማር ልጽፍልዎ ወደድሁ።

የተወለድኩት እርስዎ እና መሰሎችዎ በኢትዮጵያ የፊውዳሉን ሥርዓት በገረሰሳችሁበት ዓመት ነው። ስለዚህ በዕድሜ አሳምረው አባቴ መሆን ይችላሉ። እንዲያውም ከመጽሐፍዎ ስለእርስዎ ዕድሜ እንደተረዳሁት ከወላጅ አባቴ በ5 ዓመት ይበልጣሉ። “ውሃ ሽቅብ አይፈስም” እንዲሉ ኢትዮጵያዊው ጨዋ ባህላችን እንዳስተማረን ልጆች በአባቶቻቸው ላይ ሂስ (ነቀፋ) መሰንዘር ባይችሉም፡ እንደ አንድ የ72 ዓመት (ካልተሳሳትኩ) ኢትዮጵያዊ አዛውንት እርስዎን በማክበር፡ ከይቅርታ ጋር መጠነኛ ምክር ልለግስዎ ወደድሁ። መቼም “በአብዮቱ ፍንዳታ ወቅት የተወለደ ልጅ እንዴት እኔን ይመክራል?”፤ “ወይኔ መንግሥቱ ተደፈርኩ!” በማለት ዘራፍ እንደማይሉ ተስፋ አደርጋለሁ። ይህን አነስተኛ ጦማር ለተለያዩ ድህረ ገጾች ለመላክ ስላሰብኩም፡ መጣጥፌን አንብበው በጽሑፍ መልስ ቢሰጡኝ ደስ ይለኛል።
ይህ ጦማር የመጽሐፍዎ አጠቃላይ ቅኝት (Book Review) ወይም ግምገማ ስላልሆነ፡ በመጽሐፉ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች ላይ አስተያየት አልሰጥም። ነገር ግን ወደፊት በሚያዘጋጇቸው ተከታታይ ቅጾች ላይ ያካትቷቸው ዘንድ፡ የተወሰኑ ነጥቦችን ልጠቁም፤
– እስካሁን ድረስ የብዙ ኢትዮጵያውያን ጥያቄ የሆነው፡ 60ዎቹ የአፄ ኃይለሥላሴ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ዘግናኝ በሆነ መልኩ ያለፍርድ የተገደሉበትን ሁኔታ መጽሐፍዎ በዝርዝር አይዳስስም። አንባቢዎችዎን ተስፋ በሚያስቆርጥ መልኩ ከሌ/ጄነራል አማን ሚካኤል አንዶም አሟሟት ጋር በማያያዝ ይህን ዐቢይ ጉዳይ በአንድ ፓራግራፍ ብቻ ነው ያለፉት (ትግላችን፡ ገጽ 219)።

– ስለ ብ/ጄነራል ተፈሪ ባንቲ ግድያ በመጽሐፍዎ ምንም ነገር አልነገሩንም። ገጽ 253 ላይ ግን፡ ስለ እኚሁ ጄነራል ማንነት በቅጽ 2 እንደሚጽፉ ስላሳወቁን ይህን በተስፋ እንጠብቃለን።

– ስለ አፄ ኃይለሥላሴ እና ስለ ሌ/ኮሎኔል አጥናፉ አባተ አሟሟት (ግድያ) የተረኩት ትረካ፡ በወቅቱ በሕይወት የነበሩ እና እውነታውን የሚያውቁ ኢትዮጵያውያንን ቀርቶ ከአብዮቱ ፍንዳታ በኋላ የተወለድኩትን እና ስለወቅቱ ቀውጢ ሁኔታ ምንም የማላውቀውን እኔን እንኳ አላሳመነኝም። በመካከላችሁ በነበረው የሥልጣን ፉክክር ምክንያት ኮሎኔል አጥናፉን ከጄነራል ተፈሪ ባንቲ ጋር የእርስዎ ከሳሽ (ገጽ 246) እንዲሁም መስከረም 13/1969 ዓ.ም. የተሞከረብዎ ግድያ “ፈጣሪ፤ መሪ እና ተጠርጣሪ” (ገጽ 250) አድርገው ያስቡ ስለነበር፡ ኮሎኔል አጥናፉ በተወሰደባቸው አብዮታዊ እርምጃ የእርስዎ እጅ ወይም ግፊት የለበትም ብሎ ማሰብ ጥበብ የጎደለው የዋህነት ይመስለኛል። የአፄ ኃይለሥላሴ እና የጄነራል ተፈሪ ባንቲ ህልፈተ ሕይወት ጉዳይም እንዲሁ።

ሞት ይርሳኝ፡ የተነሳሁበትን ጉዳይ ረሳሁት እንዴ? አይ አልረሳሁትም፤ ጥቆማዬ አላልቅ ብሎኝ ነው እንጂ። ከላይ ያነሳኋቸውን ነጥቦች አብዛኞቹ የመጽሐፍዎ አንባቢዎች ይጋሩታል ብዬ አስባለሁ። አሁን ደግሞ የጦማሬ ርዕስ ወደሚያጠነጥንበት ጉዳይ ከመግባቴ በፊት በቅጽ 2 መጽሐፍዎ እንዲመልሱልኝ የምፈልጋቸውን የግሌን ጥያቄዎች ላቅርብ፤

– እርስዎ እና ባልደረቦችዎ የተከተላችሁት የኮሚኒስት ሥርዓት፡ በእግዚአብሔር ሕልውና በማያምኑ ሰዎች (atheists) የሚመራ ስለሆነ አንድ ሰፊ ሕዝብን ለማስተዳደር የሕዝቡን የእምነት ተቋማት በመቆጣጠር ላይ ያተኩራል። ይህ አባባል የራሽያ ኮሚኒስት ሥርዓት በራሽያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን፤ እርስዎ የመሩት ተመሳሳይ ሥርዓት ደግሞ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ ባደረሷቸው ተጽዕኖዎች ይረጋገጣል። ታዲያ በቅጽ 1 መጽሐፍዎ፡ ደርግ የኢትዮጵያ መኩሪያ ከሆነችው ከጥንታዊቷ እና የአገሪቱ ብሔራዊት ቤተክርስቲያን ተብላ ልትጠራ ከሚገባት (ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን) ጋር ስለነበረው ግንኙነት ምንም ነገር ያልነገሩን ለምንድን ነው?
– በወቅቱ የነበሩት የቤተክርስቲያኒቱ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን በመጽሐፍዎ ያነሷቸው በአፄ ኃይለሥላሴ ጸሎተ ፍትሐት ጉዳይ ላይ ብቻ ነው (ገጽ 271)። እባክዎን የተከበሩ ኮሎኔል መንግሥቱ፡ በሞቴ ልበልዎና ፓትርያርክ ቴዎፍሎስን ማን እንደገደላቸው በክፍል 2 መጽሐፍዎ ይንገሩን።
– አያይዘው ደግሞ፡ ከፓትርያርክ ቴዎፍሎስ ግድያ በኋላ እርሳቸውን የተኳቸው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ-ሃይማኖት እንዴት እንደተሾሙ በዚሁ በቅጽ 2 ቢያብራሩልን ምስጋናዬ የላቀ ነው። መቼም ጓድ ሊቀመንበር፡ “እኔ ስለ ቤተክርስቲያኒቱ ፓትርያርኮች የማውቀው ነገር የለም” የሚሉ ከሆነ፡ አኔም ሆንኩ ሌሎች አንባቢዎች በጣም ነው የምንታዘብዎ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኤፍሬም ማዴቦ ሸፍጥ፤ ያይጥ ምስክሯ ድንቢጥ (ክፍል 2) - መስፍን አረጋ

ቅጽ አንድን ሳነብ፡ ከ50 እና ከ30 ዓመታት በፊት የተፈጸሙ ነገሮችን በዝርዝር የማስታወስ ችሎታዎን በጣም አድንቄያለሁ። እርስዎ የ20 ዓመት ወጣት መኰንን ሳሉ ስለገጠምዎት ጉዳዮችም ሆነ የፊውዳሉን ሥርዓት በገረሰሳችሁበት ጊዜ (ያኔ እርስዎ የ34 ዓመት ጎልማሳ ነበሩ) ስለተፈጠሩ ሁኔታዎች ያወጉን በሚገርም መልኩ ጠለቅ ካሉ መረጃዎች ጋር ነው። ጉዳዮቹ የተፈጸሙባቸውን ቦታዎች ከረጅም ዓመታት በኋላ እንኳን ቢሆን በፍጹም አልረሱም፤ በአካባቢዎ የነበሩትን ጓዶች ደግሞ፡ ከነማዕረጋቸው እና የአባት ስሞቻቸው ጭምር ላፍታ እንኳ አልዘነጓቸውም። ታዲያ በተፈጥሮ ስለተለገሱት ንቃተ ኅሊናም ሆነ የማስታወስ ከፍተኛ ችሎታ “የፍጥረታት ፈጣሪ ልዑል እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን” ብል በአባባሌ አይስማሙም?

መቼም የ72 ዓመት አረጋዊ ሆነው “የምን እግዚአብሔር አመጣህብኝ?” እንደማይሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ፤ ተስፋ እና ምኞት አይከለከልም፡ አይደል? “ኢትዮጵያ ትቅደም” የምትለዋን መፈክር በጥቁር ሰሌዳ ላይ ለደርጉ አባላት ከጻፉበት ጊዜ ጀምሮ፡ እንደ ታላቁ ኢታዮጵያዊ ጀግና አፄ ቴዎድሮስ እስከመጨረሻዋ ጥይት ሳይዋጉ ወደ ሐራሬ እስከኮበለሉበት ግንቦት 1983 ዓ.ም. ድረስ የእግዚአብሔርን ስም በስህተት እንኳ ሲጠሩ አልሰማንም። እኔ እና የእኔ ትውልድ ያደግነው የሚያንባርቅ እና እሳት የሚተፋ የሚመስል ድምጽዎን በሬድዮ እየሰማን ሲሆን፡ ክርስትናን በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የተቀበለች የታላቂቱ ኢትዮጵያ ርዕሰ-ብሔር እንደመሆንዎ የልዑል እግዚአብሔርን ስም በንግግርዎ መሀል ሲጠቅሱ ለመስማት አልታደልንም። የዚህ ምክንያቱ፡ ለቆሙለት የማርክሲስት ሌኒኒስት ርዕዮት (አመለካከት) ታማኝ ለመሆን ብለው ነው ወይስ ስለ ሀልዎተ እግዚአብሔር “እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” (መዝሙረ ዳዊት 67፡31) ከተባለላት ከኢትዮጵያችን የተማሩት ምንም ነገር ስላልነበር?

ወላጅ አባትዎ አቶ ኃ/ማርያም (ይቅርታ ሌላ የማዕረግ ስም ካላቸው) ስለፈጣሪ ምንም ነገር ሳይነግርዎ ነው ያሳደጉዎት ብዬ ላስብ አልችልም። ለመሆኑ እርስዎ በልጅነትዎ ፊደል ሲቆጥሩም ሆነ ቄስ ትምህርት ቤት ገብተው ዳዊት ሲደግሙ (እንደደገሙ በመገመት ነው) የተማሩት የዳዊት መዝሙር ስለ እግዚአብሔር ምን እንደሚል አስበው ያውቃሉ? ወይስ ይኸው የዳዊት መዝሙር “ይብል አብድ በልቡ አልቦ እግዚአብሔር – ሰነፍ በልቡ ‘እግዚአብሔር የለም’ ይላል” ስለሚል (መዝ ፲፫፡ ፩) በልብዎ ‘እግዚአብሔር የለም’ እያሉ አድገው፡ ወታደራዊ ሳይንስ በሚማሩበት ጊዜ ይህን አመለካከትዎን አጸኑት? የደርግ ቁንጮ ለመሆን በቅተው “ጓድ ሊቀመንበር” ከተባሉ በኋላ ደግሞ በእግዚአብሔር መኖር እንደማያምኑ በተግባር አሳዩን። ይህንን የምለው፡ ሌላውን እንተወውና “እግዚአብሔር ያያል፤ ኃያሉ አምላክ ይፈርድብኛል” ብሎ የሚያስብ አንድ ግለሰብ፡ ቢያንስ ንፁህ ደም በግፍ ከማፍሰስ ይቆጠባል ብዬ ስለማምን ነው። ሌ/ኮሎኔል አጥናፉ አባተ እውነት በሆነው፡ ግን ለሞት ባበቃቸው ንግግራቸው እንዳሉት፡ እርስዎ እና መሰሎችዎ “ከአገራችን ባህል፤ [ሃ]ይማኖትና ታሪክ ጋር ፈፅሞ የማይገጥምና የማይስማማ የሶሻሊስት ሥርዓት እንከተላለን [ብላችሁ] አገሪቱን የጦርነት አውድማ [አደረጋችኋት]” (ትግላችን፡ ገጽ 254)። ተቆጡ እንዴ ጓድ ሊቀመንበር? ምን ይደረግ እንግዲህ፤ “እውነቱ ሲነገር ይጎዳል” ይባል የለ?

በቅጽ አንድ መጽሐፍዎ የኢትዮጵያን የቀድሞ አፄዎች ለአገሪቱ ካከናወኗቸው ዐበይት ተግባራት አንፃር ያወዳድሯቸው ነበር። አፄ ቴዎድሮስ የመሳፍንቱን “ከፋፍለህ ግዛ” ሥርዓት አስወግደው አንዲት ኢትዮጵያን ለመመሥረት ባደረጉት ጥረት ማንም እንደማይስተካከላቸው፤ የአፄ ዮሐንስን መንፈሳዊ መሪነት፤ አፄ ምኒልክ ትምህርትን እና አንዳንድ ሳይንሳዊ ውጤቶችን ወደ አገሪቱ በማስገባት የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ መሐንዲስ ቢሆኑም የባሪያ ንግድን እና የገበሬውን ጭቆና ማስወገድ ስላለመቻላቸው፤ አፄ ኃይለሥላሴ ቀድመዋቸው ከነበሩት ነገሥታት በተለየ መልኩ የትምህርት እድል ስለገጠማቸው፡ ታላላቅ የፖለቲካ እመርታ የተሰኙ ሥራዎችን እንዳከናወኑ እና የእርሳቸው ዘመን ከደረሰበት የ እድገት ደረጃ አንፃር እርሳቸውን ከቀደምቶቻቸው አፄዎች ጋር ማወዳደር እንደማይቻል አስረድተውናል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሰማያዊ ፓርቲ የሚታገለው ማንን ነው ? (ግርማ ካሳ)

እስኪ እኔ ደግሞ በርእሴ ጉዳይ ላይ ብቻ እርስዎን ከመጨረሻው የዘውድ አገዛዝ መሪ (አፄ ኃይለሥላሴ) ጋር ለማወዳደር ልሞክር። አፄ ኃይለሥላሴ፡ እግዚአብሔርን የሚያውቁ እና የሚያምኑ መሪ እንደነበሩ ወደሌላ ዝርዝር ሳልገባ ከእርስዎ መጽሐፍ በመጥቀስ ብቻ ማረጋገጥ ይቻላል። ከዙፋናቸው ካወረዳችኋቸው በኋላ ወደ ማረፊያ ክፍል ተወስደው፡ እርስዎ “የጎደለ ነገር ካለ ለማሟላት ዝግጁ ነን” ሲሏቸው “ምንም አይደል፤ እግዚአብሔር እንደፈቀደ እንኖራለን” እንዳሉ ነግረውናል (ትግላችን፡ ገጽ 189)። ይህ ሁሉ ለደህንነታቸው እንደተረገ ሲነገሯቸውም፡ በእግዚአብሔር ላይ ያላቸውን እምነት ባንጸባረቀ መልኩ “ለደህንነታችንም የሚያውቀው ሁሉን የሚችለው አንድ አምላክ ብቻ ነው” በማለት መለሱ (ትግላችን፡ ገጽ 189)። በዚሁ ገጽ ላይ ከክብራቸው በተዋረዱባት በዚያች ቀን መጽሐፍ ቅዱስ ይዘው እንደነበርም ዘግበዋል። ከዚህ በመነሳት አፄ ኃይለሥላሴ እንደ ታላላቆቹ የአሜሪካ መሪዎች (አብርሐም ሊንከን እና ሩስቬልት) መጽሐፍ ቅዱስ የሚያነቡ፤ እንዲሁም እግዚአብሔር ለሰው ዘር ያስተላለፈውን መልዕክት ከያዘው ከታላቁ የሕይወት መጽሐፍ ጋር የሚተዋወቁ መሪ እንደነበሩ ለመረዳት ይቻላል።

እርስዎ ግን 17ቱን የመሪነት ዘመንዎ በጦርነት ተወጥረው ስላሳለፉ እና ደግሞም ጊዜ ቢኖርዎት እንኳ ለማንበብ የሚመርጡት የኮሚኒዝም ፍልስፍና መጻሕፍትን ስለሆነ ቅዱሱን መጽሐፍ ያነበቡ አይመስለኝም። በግንቦት ወር 1983 ዓ.ም. አስቀድመው በተዋዋሉበት መንገድ ወደ ዝምቧብዌ ካመለጡ በኋላ ላለፉት 22 ዓመታት በፍጥረታት ፈጣሪ በሕያው እግዚአብሔር ላይ ያለዎት እምነት ምን እንደሆነ አይታወቅም። “ትግላችን…” የተሰኘው መጽሐፍዎ ግን በባዕድ አገር ሁሉንም ነገር በሰከነ መንፈስ ማሰብ በሚችሉበት ሁኔታ እየኖሩ እንኳን፡ የእምነት ሰው ወደመሆን እንዳልተቀየሩ በመጠኑም ቢሆን ያመለክታል። መጽሐፉን ከጥግ እስከ ጥግ ያነበበ ማንኛውም አንባቢ፡ አብዮታዊው እና ተራማጁ ጓድ መንግሥቱ በስደት አገርም ቢሆን ምንም አይነት የዓላማ እና የአመለካከት ለውጥ እንዳላደረጉ ይገነዘባል።

መጽሐፍዎ “አብዮት፤ አድኃሪ፤ ጭሰኛ፤ ጉልተኛ፤ ከበርቴ፤ ምንደኛ፤ ገንጣይ፤ አስገንጣይ፤ ወያኔ፤ ባንዳ፤ ሠራዊት፤ ብርጌድ፤ ጦርነት፤ እዝ፤ ጠገግ፤ ሜካናይዝድ ጦር ወዘተ.” በሚሉ አብዮታዊ እና ወታደራዊ ቃላት የተመላ ሲሆን፡ “እምነት፤ ተስፋ፤ ፍቅር፤ ይቅርታ፤ ምሕረት፤ ቸርነት፤ በጎነት” የተሰኙት ውብ ቃላት መጽሐፍዎ ውስጥ በመብራት ቢፈለጉ እንኳ ለማግኘት ያዳግታል። አማኝ ወደ መሆን እንዳልተቀየሩ ከሚጠቁሙት አገላለጾች መካከል፡ ገጽ 55 ላይ ሙሶሎኒ ኢትዮጵያን “የምድር ገነት” እያለ ይጠራት እንደነበር ገልጸው፡ በዚህ አጠራር ላይ ያለዎትን አመለካከት “ገነት የሚባል ነገር ካለ…” በማለት አሳይተዋል። ምናልባት መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ ጊዜ ቢኖርዎት ኖሮ፡ ሙሶሎኒ ምድረ ኢትዮጵያን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የመጀመሪያው መጽሐፍ (ኦሪት ዘፍጥረት 2፡8) “የኤደን ገነት” ተብሎ ከተጠቀሰው ቦታ ጋር እንዳነጻጸራት መግለጽ ይችሉ ነበር። ደግሞም ይኸው መጽሐፍ “የሁለተኛውም ወንዝ ስም ግዮን ነው፤ እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል” (ኦ. ዘፍ 2፡13) ስለሚል የሙሶሎኒ ስያሜ ትርጉም ሊገባዎ ይችል ነበር። በሙሶሎኒ ስያሜ ላይ ከሰጡት አስተያየት የተረዳሁት ነገር ቢኖር፡ ገነት፤ ሲኦል፤ የእግዚአብሔር መንግሥት (መንግሥተ ሰማያት) የሚባሉ ነገሮች እንዳሉ አለማመንዎን ነው።

በእግዚአብሔር ህልውና እና ለሰው ዘሮች ባለው ጥባቆቱ (መግቦቱ) እስካሁን ድረስ እንደማያምኑ የተረዳሁበት ሌላው የመጽሐፍዎ ክፍል ደግሞ፡ መስከረም 13/1969 ዓ.ም. ከተደረገብዎ የግድያ ሙከራ የተረፉበትን ምክንያት ሲያስረዱ፡ “ያንን ሁሉ ጥይት ሲያፈስብን እኛን ሊፈጀን ያልቻለው፡ አንደኛ የላንድሮቨሩ ተጠባባቂ ጎማ ከኋላ ከበሩ ጋር ተያይዞ የተቀመጠ በመሆኑ ስለተከላከለልን፤ ሁለተኛ አሉሚኒየም የሆነ ወፍራም የመኪናው ገላና እንዲሁም የመኪናው የኋላ መቀመጫ ጥቅልል ሽቦዎችና ስፖንጆቹ ጥይቶቹን ውጠው እየቀነሱና እያበ[ረ]ዱልን ነው” የሚለው ነው (ትግላችን፡ 7ጽ 248)። ይህ ሁሉ ዝባዝንኬ ውስጥ ከመግባት “እግዚአብሔር አትርፎን ነው” ቢሉ ምን ነበረበት? እዚህ ላይ መልስ ከሰጡኝ፡ እንዲመልሱልኝ የምፈልገውን አንድ የመጨረሻ ጥያቄ ልጠይቅዎ፤ እርስዎም ሆኑ ባልደረቦችዎ የደርግ አባላት በሀልዎተ እግዚአብሔር የማታምኑ የሶሻሊዝም ፖለቲካዊ ርዕዮት ተከታዮች ሆናችሁ ሳለ፡ ላለመከዳዳት በገባችሁት ቃለ መሐላ ውስጥ ለምንድን ነው “በሕያው እግዚአብሔር ስም እምላለሁ” የሚል ዐረፍተ ነገር የጨመራችሁት? (ትግላችን፡ ገጽ 171)።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ነፍሴ ቸኩላለች !!

የተከበሩ ኮሎኔል መንግሥቱ፡ ይቅርታው እና ምሕረቱ የበዛ ቸሩ እግዚአብሔር ዕድሜ ለንስሐ ስለሰጠዎ፡ በብዙ ጥይቶች መካከል አልፈው፤ ምድራዊ ፍርድንም አምልጠው እስካሁን በሕይወት ይገኛሉ። በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት በዘር ማጥፋት ወንጀል ከስሶ ስለፈረደብዎ፡ በመሪነት ዘመንዎ የሠሩትን ሁሉ የኢትዮጵያን ሕዝብ እያማከሩ የሠሩ ይመስል ፍርዱን በሕዝቡ ላይ የተፈረደ ነው በሚል መንፈስ፡ “የኢትዮጵያ ሕዝብ ዘር አጥፊና የጦር ወንጀለኛ ተብሎ መፈረጁን በመስማቴ ለታሪክና ለሕዝቡ የተተወውን የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ የትግል ታሪክ እኔ እራሴ ለመጻፍ ተገደድኩ” ብለውናል (ትግላችን፡ ገጽ 5)። ፍርዱ አበሳጭቶዎት 500 ገጾችን የያዘ መጽሐፍ ስለጻፉ፡ እርስዎ ላይ ያደረሰውን አዎንታዊ ተጽዕኖ እረዳለሁ። ነገር ግን በሰከነ እና በተረጋጋ መንፈስ ማሰብ በሚችሉበት የኑሮ ሁኔታ እና የዕድሜ ክልል ውስጥ ሆነው ሳለ፡ በመሪነት ዘመንዎ በፍጹም ስህተት ሰርቻለሁ ብለው አያምኑም። በመጽሐፍዎ የመጸጸትም ሆነ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ የመጠይቅን ዝንባሌ አንድም ቦታ አላሳዩም። አቋምዎ አሁንም ‘አብዮት ልጇን ስለምትበላ የአብዮቱ ተጻራሪዎች እርምጃ ተወሰደባቸው (ተወገዱ)፤ እንዲሁም በወቅታዊው አጣብቂኝ እና አስገዳጅ ሁኔታዎች ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነጻነት እና ዕድገት ስንል አስፈላጊ ውሳኔዎችን ወሰንን’ የሚል ይመስላል።

ከሞት በኋላ ሕይወት (ያውም ዘለዓለማዊ) እንዳለ የሚያምኑ ከሆነ ግን፤ የኢትዮጵያ የቀድሞ መሪዎች ጽዋቸው ሞልቶ በሞት እንደተጠሩ፡ እርስዎም አንድ ቀን ይጠሩና ነፍስዎ ወደ ፈጣሪዋ ልዑል እግዚአብሔር ትመለሳለች (መጽሐፈ መክብብ 12፡7)። “የእግዚአብሔር እስትንፋስ” በመባል የሚታወቀው መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስረዳን “ሁላችን በክርስቶስ የፍርድ ዙፋን ፊት እንቆማለን” (2 ቆሮንቶስ 5፡10)። የነገሥታት ሁሉ ንጉሥ የሆነው ጌታም ለፍርድ ዳግም እንደሚመጣ እና ለእያንዳንዱ እንደ ሥራው እንደሚከፍለው ነግሮናል (ራዕየ ዮሐንስ 22፡12)። በእግዚአብሔር የተወሰነልዎ የዕድሜ ገደብ አብቅቶ በአካለ ነፍስ በክርስቶስ ዙፋን ፊት ቆመው በሕይወት ዘመንዎ ስለሰሩት ነገር ሁሉ ከመጠየቅዎ በፊት፡ ቃሉ “ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ፤ ንስሐ ግባ፤ ያለበለዚያ ፈጥኜ እመጣብሀለሁ” (ራዕየ ዮሐንስ 2፡5) ይላልና ዛሬውኑ ከሕሊናዎ ጋር ተማክረው ወደ እግዚአብሔር ልብዎን ይመልሱ። “አባታችን ሆይ…” ብለን እንድንጠራው የፈቀደልን መሐሪው አምላክ፡ ልጆቹ በ11ኛው ሰዓት (የዕድሜያቸው መገባደጃ) ላይም ቢሆን በንስሐ ቢመለሱ በፍቅር ይቀበላቸዋልና “አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ” ይበሉት (መዝሙረ ዳዊት 50፡1)።

በምሕረቱ ባለጸጋ የሆነው እውነተኛው አምላክ፡ የእርሱን ምሕረት እና ይቅርታን ለማግኘት ከፈለግን መጀመሪያ ከወገኖቻችን ጋር ይቅር መባባል እንዳለብን ነገሮናልና (የማቴዎስ ወንጌል 5፡24፤ የማርቆስ ወንጌል 11፡25-26) በሥልጣን ዘመንዎ ለወታደሮችዎ ባስተላለፏቸው ቀጫጭን ትዕዛዞች አማካኝነት ልጆቻቸውን ወይም ወላጆቻቸውን በሞት በመቅጠፍ ለዓመታት ደም ዕንባ ያስነቧቸውን ኢትዮጵያውያን ወገኖች በሙሉ በግልጽ ይቅርታ ይጠይቁ። አለበለዚያ እውነተኛው ዳኛ እግዚአብሔር፡ ለመጀመሪያው ነፍሰ ገዳይ ለቃየን እንደነገረው አሁንም “የወንድምህ የደሙ ድምፅ ከምድር ወደ እኔ ይጮኻል” ይላል (ኦ. ዘፍጥረት 4፡10)። ስለዚህ ከላይ የጠቀስኳቸውን የቃሉን መልእክታት በማስተዋል፡ የትዕቢት መንፈስ ቢጫንዎት እንኳ እንደምንም ይቃወሙት እና በትህትና ራስዎን ከኃያሉ አምላክ የጸጋ ዙፋን ሥር ይጣሉ። ምሕረቱን ይለምኑ፤ ቅዱስ የሆነውን ስሙንም ዘወትር ይጥሩት፡ መጽሐፍ እንደሚል “የእግዚአብሔርን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል[ና]።”

16 Comments

  1. hi i think u fifnt understand d/c he was right by him self and no one should not b forced to believe on God coz it is free obtion and read z bk correctly in detail.

  2. hi i think u didnt understand d/c he was right by him self and no one should not b forced to believe on God coz it is free obtion and read z bk correctly in detail.

  3. በጣም የምትገርም ፀሃፊ ነህ ጓድ መንግስቱ ሃ/ማሪያም ለሃገር አንድነት የታገሉ ጠንካራ መሪ ናቸው እንዳሁኖቹ ሃገርን
    ቆራርሰው አንዱን ለሱዳን አንዱን ለሌላ የሚሰጡ መሪ አይደሉም…የማታቅ ከሆነ አንድ ነገር ልንገርህ በስደት የነበሩ ኢትዮጵያኖችን እንኩዋን በጣም ያስቡዋቸው ነበር ”ህዝቤ እኔን ጠልቶ እንጂ ሃገሩን ጠልቶ አልተሰደደም” ብለዉ የሚናገሩ ጥቃት እንዳይደርስባቸው ጠንካራ ማስጠንቀቂያ የሚሰጡ ትልቅ ሰዉ ናቸው…እንዳሁኖቹ ዜጎች ሲገደሉ ቆመው አያዩም…ስለዚህ አንተ ጦማር መስጠት ያለብህ ለአሁኖቹ ነበር..ለነገሩ ከትንሽ ሰው ትንሽ አስተሳሰብ ቢወጣ አይገርምም..ትንሽ አስተሳሰብ ይዘህ አትናገር ዝም በል…ይህ የእኔ ምክር ነው

    • What the hell are you talking! Shameful! Mengistu was blood thirsty murdered who massacared nearly 2 million his fellow Ethiopians! His legacy will be remembered as one of the most brutal and ruthless killers in human history!

  4. There was not a single dose of patriotic blood in Mengistu. If there is any blood that runs in his rusty veins, it is the blood of the millions he slaughtered. Even if he confess (which I doubt) it will merely alleviates his inner moral (if he has one) conflict. After butchering millions, he is the one who declares that he has not even killed a mosquito. After deluding his piglets that he was Emperor Tewdros, the Second, he tuck his tail (sure he has one) and rushed to Zimabwe. Patriotic…kiss my ass

  5. Sile haimanotachew ye,miagebah neger yelem yetenagerkewn le.woyanewoch asreda negergin “guad mengistu” hager afkary nachew !

  6. otawa yemitnorew sdetegna yetesededkew beweyane ymeslegnal be menigsitu aymeslegnm bemenigsitu kehone agerih giba beterefe enideweyane balefe bareje neger atinkotakot lemagn kemehon agerihin neta lemawtat mokir were ayseram siletafik awaki adelehim baligeh sew atabalig tnx

  7. “a person who has no job at hand tears his clothes and sew them back”.

    Do not you have something another and other burning issues to write about?

  8. Mengeistu is the one who massacred millions of Ethiopians and finally made great escape to Zimbawe by disbanding the huge Ethiopian military force which allowed the woyane thugs to freely over run the country and establish an apartheid like system of rule in this country, How come some people adore this cannibal as a hero ,unless they have same feather or they must be mentally deranged or having blood on their hands ,Mengistu and woyane differ in form not in content , Mengistu never love his country and its people . He loves his power than anything .otherwise he would have not left his country and people. He run to save his soul while Ethiopian people were in very dangerous situation. Had he not been selfish , he could have done something to turn the table by going to the extent of dying in action as patriot. Unfortunately this brutal Mengistu knows only how to kill innocent Ethiopians not those Ethiopian enemies. I think this tyrant and hench men and his accomplisers shall sooner or later face trial when the woyane regime doomed once and for all.

  9. What are commenting man? It is really futile ;Who are u to criticize his religious stand? You better talk or ask about the then political and administration drawbacks and it’s out come to our people and country.

  10. The writer raised a legitimate question. I grew up in DERG era like the writer is, and I know where he is getting at. Communist, Bolsheviks, Marxists, or Socialists who came to power in our beloved country were godless. They are cruel, and that explains as to why they destroy precious human life at will. Tplf should be numbered with this group as well. In the near future, we will witness atrocities committed by tplf to be far worse that the DERG. Wait and see! One can argue, once atheists and godless people started to lead our country, the climate itself started to change, the country became barren, the green started to disappear gradually. Our country used to be more beautiful that now when our for father worshiped Him with owe and adoration. God was, is, and will be. Atheists are fools and losers. Our country suffered for almost 40 years because of them. If one believes that there is no God, then it is more likely that this individual may find it easy to kill, to loot, to be greedy, to be insensitive to human suffering, to be cruel, to abuse fellow human, and to do all wicked and ugly things to support his luxury living. But of course, some so called intelligent people may deny the existence of God. That is fine. They might ask some tangible evidence. The Pentagon is currently experimenting with an arm that was produced by more than two dozens scientists for US soldiers who lost their arm during wars. The cost of that arm is about 3 million US dollars. After more than two dozens scientists and 3 million dollars, the arm barely lifts a soda can. Kudos for those scientists because it was one of a kind in this planet. Now, look at your arm you atheists who deny the existence of our God. Who designed it? You do not dare to say that it came about by chance would you? The evidences are countless for the existence of God who designed our life. For instance, human eye is one of our amazing and marvelous organs. We do not see just for the sake of seeing. It is our retina cells in our eyes that enable us to see. They have the ability to interpret light. Their numbers are ten billions. One of those cells circulates 500 simultaneous non-linear differential equations in 10 milliseconds. That would take about a couple of hundred years for your PC. We see because all of these cells do the circulations to interpret objects. Only an insane atheist believes our eyes are a product of chance. Moving on, Mengistu or meles are atheists who care about only for their power. Their greediness, cruelty, and murderous rampage came from atheist books they read. To name the few-cultural revolution and das capita, but we need a leader who read books that inspire to do good the Bible being one. We need a leader who sees all life as equal. Most of all, we need a leader who loves US and our country. Finally, does any atheist can support his belief that God does not exist? Then he can prove it to us.

  11. Like Tebebt Weiys like likawunt?
    Emnet yegil new Comrade Mengistu begilachew yefelegutn emnet meketel mebtachew new. Gen Andit Tiyake liteyikwot
    Ke Ersewo Agelaltse endeteredahut bebete krstian sen megebare Tanisew yadegu yimeslalu.
    Ewnwt lemenagerem lemesmatim yemigedwot aymeslegnim.
    Begziabher Yemayamnut ene guad mengistu lehizb ena lebetekristian keserut antsar erswona kedemtochwo mene seran belew raswon yiteiyku
    1.be 1965 yewello hizb be dirk siregif the clergy (yebete kiristian sewoch) yehizbu chigir sayitayachew kerto neber wey? Min yiseru neber? Le Niguse negestu lemesafintuna lemekwanintu Edme kemelemen bashager le second enkwan wegenochachewn astawsewalne?
    2. Ersewo bekefitegna kibir yetekeswachewna yawedeswachew Niguse Negest Hageritun bemigezu gize seyume egziabhere nachew eyalachihu ye Ethiopia hizb besachew endiamelk Esachewm mastewal endiatuna bersachew ena beteketayochachew yemifetsemibetin gif ende arba ken edilu endikotir tedergual.
    3. Yebyotun findata teketilo
    Bzeke (migib) bicha yitedaderu yeneberu miskin kesawust demewez endikoretlachew, Leteleyaye zerefana mizbera betegalete melku yikahed yeneberew yebetekristian gebi serat yizo na kemengistim budget temedibo enditedader mederegu
    4. Beteleyaye zikir betekiristian yemimeta migib wet na tela weiym lela metet eyemeretachihu nedayanen satasibu wedebetachu chimir yemitwesdu lehodachihu ena le albale neger yemitbeletu aydelachihumne?

    Tadia endet tedergo new erswo yihin yemesele yesine migbar gudlet kalebachew be egziabher amagn nen kemitilu yewahan mekakel Comrade Mengistu lai his lemesenzer yemoral bikat yeminorwot?
    Beyetignaw memezegnas new yehageritu habt yehonew meret lehizb endiset hizb endimar bewektu beneberew huneta besewoch mekakel yezer yekelem yegosana yehaimanot liyunet sayidereg ekul yemesrat byetignawm yehageritu kilil serto yemenor mebt yastebeke mengist meri yenebru sew migebare kemetsehaf kidus kal betkarno yemitayew? Weyis metshaf kidus besewoch mekakel bezer bekelem liyunet andu sew belelaw tikesha benoru yamnal? Ayimeslegnim.
    Beabyotu hidet berkata sehitetoch endeteseru comrade Mengistu Alkadum. Behulum gora teselifew wud heiwotachewn meswit yekefelut birk ye Ethiopia lijoch nachew. Yih asazagn tarikachin new. Lezih hulu gin Comrade mengistu bicha teteyakina tesesach nachew malet gif new. Egziabher Endesew Adlawi ayidelem. Yanin hulu yetederege dirgit Letifat bilew kefetsemu kesu fird ayameltum.
    Fekadwo kehone
    Wedefit besefiw be Amarigna tsife enweyayalen
    Yegize telewawachinetin endegibeat tetekimew Ewnatawn lemazabat metar agbab ayidelem
    Ketalak \yikreta gar Amesegnalehu.
    Comrade Mengistu Ebakwotin Metsehaftochun Yafatnulin. Yederg abalatim Eyetsafu Selehone Leemawedader Yamechenal

  12. Thank you A huge thank you to the writer. People make mistakes in their like, some light some grave affecting human lives and an entire continent. God forgives and receives whoever repents.

    I grew up and was raised exactly like the writer in Mengea’s time (if I am allowed to say it). He has committed atrocities due to incompetence and shear arrogance. But i have no doubt he loved the country, he worked not for money or fame but from his sincere heart. A good friend of mine has his picture posted in his home todate. And many of us still have huge respect for him despite the errors. No woyane banda land sellers can sit with him side by side. Mengea will NEVER compromise on the unity of Ethiopia and the development of the country. I respect other people’s opinion but I still have huge respect for him.

    I strongly wish he repents and aligns his path with God for the real judgement. For one day the foot slips and we reach a dead end with no return if we do not repent and receive Jesus.

  13. Yene wendim lemindin new mengistu kirstosin endiyamin yefelekew? Ersu eko yager(yehulum haimanot teketay hizib) meri eko new. He was not religious, he was socialist. M A H I B E R E S E B A W I. Mahibereseb degimo haimanot ena zer yelewum.

  14. As a young military officer, Mengistu has done untold crimes. There is no bandage that can cover his crime. Much can be said about the Derg’s time on power. Nevertheless, that is not what is gripping the Ethiopian people. It is the TPLF. Mengistu never cared about your ethnic affiliation. As long as you adhere to their twisted outlook you are a comrade. Try that with the TPLF, you neck will be cut as soon as you join them. The order is to stay at your ethnic enclave. You do as they tell you. They work and operate as the Italian Mafia. I was in Ethiopia recently, and have asked youngsters as well as people that survived Mengistu’s terror. Majority of them told me they long for the past. That is very striking. I have never thought I will see a day people will want Mengistu’s time than the current one. Die hard Derg supports may attempt to justify the killings of the past. Stop that rubbish. There is no justification for that. Yet, there is one justification that is still justifiable. The Derge, especially Mengistu loved and operated under the unity of the country. What is not shining in this story is, the way Mengistu went about to achieve his goals and objectives.

  15. Kale hiwot yasemalen! Wodaje yehager meri ena yehaimanot meri eneley enji. Endew tegegne teblo ema aylekelekim gobez. Be Egziabher biyamnu melkam neber bergit.

Comments are closed.

Share