ልብን የሚነካዉ የኢትዮጵያዉያን ጉዞ በሳዑዲ አረቢያ

ከሳዲቅ አህመድ

በሰላም እንደገቡ በሰላም የመዉጣት ግዴታን እየተገበሩ መሆናቸዉን ይናገራሉ። በአብዛኛዉ ሰላም ወዳድ ህግ አክባሪ ቢሆንም ጥቂቶች በሚፈጽሙት ደባ ሰለባ ላለመሆን “ዉጡ እስክተባልን ድረስ እነዉጣል” ይላሉ ተጓዦቹ። የትም ቢሆን የት እምነትን ተግባሪ መሆናቸዉን እያስመሰከሩም ነበር…ለሶላት ሲጠራም አይደም አዋቂዎች፤ዉሉ ያልታወቀ ጉዞን  ህጻናት እንኳ ከሰጋጆችም ነበሩ። የስንብት ዳእዋ (ሰበካ) ተደርጎላቸዋል፤መንፈስንና አካልን ለማነቃቃት እንዳቅሚቲ ኳስን የሚጫወቱም ነበሩ። ብቻ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ቢገደዱም ፊታቸዉ ላይ የተስፋ ብርሃንን ያበሩ…ሆዳቸዉን ባር-ባር ብሎት የእንባ ዘለላን በጉንጮቻቸዉ ላይ ያፈሰሱም ነበሩ።
በደል ከበዛባት ኢትዮጵያ በደልን ሸሽተዉ በሙስሊም ወንድሞቻቸዉ ጉያ ቢሸሸጉም ተሸሽገዉ እስኪያልፍ ያለፋል ቢሉም፤ ከዚያ የጥገኝነት ጉያ ዉጡም ተባሉ። ግን በመለኮታዊ-ምሪት ‘የተበደለ ሰዉ እንባ ሊፈራ እንደሚገባ ተጠቁሟል’ ለዚህ ሁሉ ምስቅልቅልታ፣ እሪታ፣ዋይታ ከሁለቱ አንባገነኖች አንዱ…ወይም ሁለቱም… የዚህን የመንፈስ-እንባ ካሳ በምድርም ካልያም በወዲያኛዉ አለም መክፈላቸዉ አይቀሬ ነዉ።
ከተመላሾቹ መካከል አንዱ አባት ያራስ-ቤት ልጁን ጸጉር እየዳበሰ እራሱን በጥልቅ ፈገግታ አንጾ ነበር! ደስ አይልምን?..ልብ ያለዉ ልብ ይበል!



 

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሽብርተኛው የኦህዴድ መንግሥት ፋኖን “ሽብርተኛ” ብሎ ሲከስ መላው ዓለም ታዝቦታል፤ንቆታል

3 Comments

  1. God Bless you,Sadik,

    There are still some Arabs who have fear of God. We can not generalize them all as our enemies. There are some Arabs who tell the truth.
    God may help Ethiopians, Amen.

Comments are closed.

Share