December 4, 2013
2 mins read

ልብን የሚነካዉ የኢትዮጵያዉያን ጉዞ በሳዑዲ አረቢያ

10430

ከሳዲቅ አህመድ

በሰላም እንደገቡ በሰላም የመዉጣት ግዴታን እየተገበሩ መሆናቸዉን ይናገራሉ። በአብዛኛዉ ሰላም ወዳድ ህግ አክባሪ ቢሆንም ጥቂቶች በሚፈጽሙት ደባ ሰለባ ላለመሆን “ዉጡ እስክተባልን ድረስ እነዉጣል” ይላሉ ተጓዦቹ። የትም ቢሆን የት እምነትን ተግባሪ መሆናቸዉን እያስመሰከሩም ነበር…ለሶላት ሲጠራም አይደም አዋቂዎች፤ዉሉ ያልታወቀ ጉዞን  ህጻናት እንኳ ከሰጋጆችም ነበሩ። የስንብት ዳእዋ (ሰበካ) ተደርጎላቸዋል፤መንፈስንና አካልን ለማነቃቃት እንዳቅሚቲ ኳስን የሚጫወቱም ነበሩ። ብቻ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ቢገደዱም ፊታቸዉ ላይ የተስፋ ብርሃንን ያበሩ…ሆዳቸዉን ባር-ባር ብሎት የእንባ ዘለላን በጉንጮቻቸዉ ላይ ያፈሰሱም ነበሩ።
በደል ከበዛባት ኢትዮጵያ በደልን ሸሽተዉ በሙስሊም ወንድሞቻቸዉ ጉያ ቢሸሸጉም ተሸሽገዉ እስኪያልፍ ያለፋል ቢሉም፤ ከዚያ የጥገኝነት ጉያ ዉጡም ተባሉ። ግን በመለኮታዊ-ምሪት ‘የተበደለ ሰዉ እንባ ሊፈራ እንደሚገባ ተጠቁሟል’ ለዚህ ሁሉ ምስቅልቅልታ፣ እሪታ፣ዋይታ ከሁለቱ አንባገነኖች አንዱ…ወይም ሁለቱም… የዚህን የመንፈስ-እንባ ካሳ በምድርም ካልያም በወዲያኛዉ አለም መክፈላቸዉ አይቀሬ ነዉ።
ከተመላሾቹ መካከል አንዱ አባት ያራስ-ቤት ልጁን ጸጉር እየዳበሰ እራሱን በጥልቅ ፈገግታ አንጾ ነበር! ደስ አይልምን?..ልብ ያለዉ ልብ ይበል!



 

3 Comments

  1. God Bless you,Sadik,

    There are still some Arabs who have fear of God. We can not generalize them all as our enemies. There are some Arabs who tell the truth.
    God may help Ethiopians, Amen.

Comments are closed.

Previous Story

የኢሕአደግና የግንቦት ስባት ድርድር ? ግርማ ካሳ

Next Story

የካርቱም ድራማ፡ እነ ኃይለማርያም ደሳለኝ ሕዝቡን ስብሰባ ጠርተው እነርሱ ቀሩ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop