April 13, 2020
2 mins read

በቡድን ተደራጅተው “ሲያግቱና ዝርፊያ ሲፈፅሙ ነበር” የተባሉ ተያዙ

E3F4D2E9 FA95 4D57 BA2F 4FCB89611E93 w1023 r1 s

በጎንደር ከተማ ሁለት በሕገወጥ መንገድ የተደራጀ ካምፕ ተገኝቷል ተብሏል አንድ የቴሌ ሠራተኛ ”ሦስት ሆነን ታግተን በገንዘብ ነው የተለቀቅነው” ብሏል

በአማራ ክልል በጎንደር ከተማ ውስጥ በሁለት መኖሪያ ቤት ከባድ መሳሪያ ጭምር ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች ላይ መንግሥት እርምጃ በወሰደበት ጊዜ አንድ ነጋዴና አንድ ሹፌር በአጠቃላይ ሁለት ሰዎችከታገቱበት መለቀቃቸውን የጎንደር ከተማ ከንቲባ አስታወቁ።በተጨማሪም ቡድኑ አራት የፀጥታ አባላትንና ሁለት ሰላማዊ ሰዎችን መግደሉን እንዲሁም አራት ሰዎች መቁሰላቸውን አያይዘው ገልፀዋል። የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው አንዳንድ ሰዎች መንግሥት በዚህ አሳቦ “በፋኖስም የተደራጁ ሰላማዊ ወጣቶችን ለማጥፋት ነው” የሚል ሐሳብ ቢሰነዝሩም ሌሎች ደግሞ “የለም በከተማው ነዋሪዎችን በተለይ ነጋዴዎች እና ገንዘብ አላቸው ብለው ያሰቡትን ሰዎች የሚያስጨንቁ” ናቸው በሚልአስተያየት ሰጥተዋል። እንደውም መንግሥት እርምጃ ሳይወስድ ዘግይቷል የሚሉም አሉ።

በሌላ በኩል “ሳንጃ” በሚባል አካባቢ ከታገቱ በኋላ ቤተሰቦቻቸው በከፈሉት 500 ሺህ ብር መለቀቃቸውን ከገለፁ ሦስት የኢትዮ – ቴሌኮም ሠራተኞች አንዱን አነጋግረናል።

(ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

 የሕብር ሬዲዮ ሚያዚያ 4/5 ቀን 2012 ዓ.ም. ፕሮግራም

Next Story

ማን አወቀው – ማንስ ለየው፣  የዛን የፅልመት ገበና ?  – አስቻለው ከበደ አበበ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop