April 13, 2020
2 mins read

በቡድን ተደራጅተው “ሲያግቱና ዝርፊያ ሲፈፅሙ ነበር” የተባሉ ተያዙ

በጎንደር ከተማ ሁለት በሕገወጥ መንገድ የተደራጀ ካምፕ ተገኝቷል ተብሏል አንድ የቴሌ ሠራተኛ ”ሦስት ሆነን ታግተን በገንዘብ ነው የተለቀቅነው” ብሏል

በአማራ ክልል በጎንደር ከተማ ውስጥ በሁለት መኖሪያ ቤት ከባድ መሳሪያ ጭምር ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች ላይ መንግሥት እርምጃ በወሰደበት ጊዜ አንድ ነጋዴና አንድ ሹፌር በአጠቃላይ ሁለት ሰዎችከታገቱበት መለቀቃቸውን የጎንደር ከተማ ከንቲባ አስታወቁ።በተጨማሪም ቡድኑ አራት የፀጥታ አባላትንና ሁለት ሰላማዊ ሰዎችን መግደሉን እንዲሁም አራት ሰዎች መቁሰላቸውን አያይዘው ገልፀዋል። የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው አንዳንድ ሰዎች መንግሥት በዚህ አሳቦ “በፋኖስም የተደራጁ ሰላማዊ ወጣቶችን ለማጥፋት ነው” የሚል ሐሳብ ቢሰነዝሩም ሌሎች ደግሞ “የለም በከተማው ነዋሪዎችን በተለይ ነጋዴዎች እና ገንዘብ አላቸው ብለው ያሰቡትን ሰዎች የሚያስጨንቁ” ናቸው በሚልአስተያየት ሰጥተዋል። እንደውም መንግሥት እርምጃ ሳይወስድ ዘግይቷል የሚሉም አሉ።

በሌላ በኩል “ሳንጃ” በሚባል አካባቢ ከታገቱ በኋላ ቤተሰቦቻቸው በከፈሉት 500 ሺህ ብር መለቀቃቸውን ከገለፁ ሦስት የኢትዮ – ቴሌኮም ሠራተኞች አንዱን አነጋግረናል።

(ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

 የሕብር ሬዲዮ ሚያዚያ 4/5 ቀን 2012 ዓ.ም. ፕሮግራም

Next Story

ማን አወቀው – ማንስ ለየው፣  የዛን የፅልመት ገበና ?  – አስቻለው ከበደ አበበ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop