November 20, 2013
19 mins read

የሳምንቱ የአብርሃ ደስታ በፌስቡክ ላይ የተለቀቁ ምርጥ ጽህፎች

Abrham Desta

የነቀዘው የሙስና ትግል!
————————-

ስለ “የነቀዙ ህሊናዎች” አንድ የነቀዘ ፅሑፍ አዘጋጅቼ ስጨርስ መብራት ሃይል ነቀዘብኝና መብራት ሲጠፋ ፅሑፌን አብሮ ጠፋ። የፅሑፉ መሰረተ ሐሳብ ባጭሩ እነሆ።

የኢህአዴግ መንግስት የነቀዘውን ዘጋቢ ድራማ (ዘጋቢ ፊልም አላልኩም) በማቀናበር “ሙስናን ከልቤ እየታገልኩ ነው። እየታሰሩ ያሉ ባለስልጣናት በስርቅ እንጂ በፖለቲካ አለመሆኑ ይታወቅልኝ፣ ሰው ግን አያምነኝም” አለን። መንግስት ለሚናገረውና ለሚያደርገው ነገር ህዝብ እንደማያምነው ማመኑ አንድ ትልቅ ነገር ነው። ችግሩ ግን አሁንም በድራማው ማመን አለመቻለ ነው።

እኔ “የነቀዙ ህሊናዎች”ን ድራማ መንግስት በፈለገው መጠን አልተቀበልኩትም። በኔ እምነት በሙስና ሰበብ የታሰሩ ሰዎች በትክክል በስርቅ (ሙስና) የተያዙ አይመስለኝም። የታሰሩት በፖለቲካ ሊሆን ይችላል። ይህን የምልበት ምክንያት የታሰሩት (ወይ የተያዙት) ባለስልጣናት ሙስና አለመስራታቸው (አለመስረቃቸው) ወይ አለመስራታቸው (አለመስረቃቸው) ማስረጃ ስላለኝ ወይ ስለሌለኝ አይደለም። የኔ መከራከርያ ሐሳብ ‘በኢህአዴግ መንደር ሙስና የሰራ (የሰረቀ) ይታሰራል ወይ?’ የሚል ነው። ሙስና የሰራ የሚታሰር ቢሆን ኑሮ አብዛኞቹ ባለስልጣናት ይታሰሩ ነበር። አሳሪዎቹም ጭምር ይታሰሩ ነበር። የኢህአዴግ ሙሰኞች የታሰሩት ሰዎች ብቻ ናቸው? ከነሱ በባሰ ሁኔታ በሙስና የተዘፈቁ ግን ያልታሰሩ የሉም?

ኢህአዴግ ልናምነው ከፈለገ ሙስና የሰሩ ባለስልጣናት ሁሉንም መታሰር አለባቸው። የተወሰኑ እያሰረ ሙስና መስራታቸው ቢነግረን የታሰሩት በሙስና ነው ብለን ለማመን ይከብደናል። ምክንያቱም የሰረቀ ሁሉ እንደማይታሰር እያየን ነው። ብዙ ግዜ ኢህአዴግ የራሱ ልጆች የሚያስረው የፖለቲካ ልዩነት ሲፈጥሩ ነው። ለምሳሌ አቶ ስየ አብርሃ በሙስና ሰበብ የታሰረው ከመለስ ጋር አለመግባባት ከፈጠረ በኃላ ነበር። ስየ በትክክል ሙስና ሰርቶ ከሆነ የሰረቀው ከክፍፍሉ በኋላ ነው? ሊሆን አይችልም። ስየ ሰርቆ ከሆነ ከክፍፍሉ በፊት ነው መሆን ያለበት። ከክፍፍሉ በፊት ግን አልታሰረም። ስለዚህ ስየ ከመለስ ዜናዊ ጋር ባይጣላ ኑሮ ያለመታሰር ዕድል ነበረው ማለት ነው። ባይታሰር ኑሮ ሙስና መስራቱ አንሰማም ነበር።

ስለዚህ በኢህአዴግ የሚታሰር ሁሉ ሙስና የሰራ ስለመሆኑ እርግጠኛ መሆን አይቻልም። እናም ኢቲቪን አላመንኩትም። ለመታመን ከፈለገ የሰረቁት ሁሉ ይታሰሩ።

 

“ከህወሓት የባስክ ትሆናለህ” አሉኝ
———————————–

“ጨቋኝ ስርዓት አልፈልግም” ብዬ በፃፍኩት ላይ አንድ የፌስቡክ ወዳጄ “አንተ ራስህ ስልጣን ብትይዝ ከህወሓት የባስክ አምባገነን ትሆናለህ” አለኝ።

እኔም እላለሁ፣

ከህወሓት የተሻልኩ እንደምሆን እርግጠኛ አይደለሁም (ራሴ ለግዜው እንደ ፓርቲ ልቁጠር)። ስለ አንድ ነገር ግን እርግጠኛ ነኝ። እኔ ሰለማዊ ታጋይ ነኝ። ስልጣን የምይዘው በህዝባዊ ምርጫ እንጂ በጠመንጃ አይደለም። የምወዳደረው በሐሳብ እንጂ በሃይል አይደለም።

ስለዚህ ስልጣን ስይዝ የራሴ ወታደር፣ ፖሊስ፣ ዳኛ ወዘተ ይዤ አልመጣም። ስልጣን የምይዘው በሕገመንግስት መሰረት እስከሆነ ድረስ በኔና በወታደሮቹ ያለ ግንኙት ሕገመንግስታዊ ይሆናል። ስለዚህ ወታደሮቹ እንደፈለኩ የግሌ የስልጣን ጥም ለማርካት አላዝዛቸውም። ዳኞችም ነፃ ይሆናሉ።

ስለዚህ እኔ ስልጣን ከያዝኩ በኃላ ከህወሓት ካልተሻልኩ በህዝብ ምርጫ እንደወጣሁ ሁሉ በሚቀጥለው በህዝብ ምርጫ ከስልጣን እወርዳለሁ። ከስልጣን ላለመውረድ ምንም ዓቅም የለኝም፤ ምክንያቱም በምርጫ ስልጣን የያዘ አካል የግሉ ወታደርና ፖሊስ የለውም። የስልጣን መሰረቴ የህዝብ ድምፅ ከሆነ በስልጣን ለመቆየት ስል ህዝብን አልጨቁንም። ከጨቆንኩ ደግሞ ህዝቡ ያወርደኛል።

የኢህአዴግ መንግስት ሰለማዊ ትግልን አጨልሞብኝ በትጥቅ ትግል ስልጣን ከያዝኩ ግን አምባገነን የመሆን ዕድል አለኝ። ምክንያቱም የስልጣን ምንጬ ጠመንጃ እንጂ ህዝብ አይደለም። ለህዝብ ታማኝና አገልጋይ የምሆንበት ዕድል ይጠባል። ስለዚህ በምርጫ ስልጣን የያዘ መንግስት ቢያበላሽ እንኳ በምርጫ ይወርዳል። አሁን የቸገረን በጠመንጃ የመጣ መንግስት ነው።

ዓላማችን ስልጣን መያዝ ብቻ ሳይሆን ስልጣን በጠመንጃ ከመያዝ በምርጫ የምያዝበት ስርዓት መገንባት ጭምር ነው።

(ስልጣን የመያዝ ዕቅድም ፍላጎትም የለኝም። የኔ ፍላጎት በነፃነት የፈለኩትን ማድረግ ነው። እኔ የሌሎችን መብት ሳልዳፈር የፈለኩትን የማድረግ ነፃነት እንዲኖረኝ የህዝብ መንግስት ወይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት አለበት። ስልጣን መያዝ ነፃነትን ይገድባል)።

 

‘ኢትዮዽያዊነት’ ምንድነው?
——————————

የህወሓት በስልጣን የመቆየት ስትራተጂ መከፋፈል ነው። ለመከፋፈል ወዳጆችና ጠላቶች መለየት ነው። ህወሓት ከትግራይ ህዝብ ድጋፍ ለማግኘት “ሸዋ አማራ” ጠላቱ እንደሆነ ይሰብካል (‘ዓረና ከጠላቶቻችን ጋር እያበረ ነው’ የሚል ፕሮፓጋንዳ መሰረት እናድርግ)።

እንዴት ነው አንድ ህዝብ ለሌላ ህዝብ ጠላት የሚሆነው? የህዝብ ጠላት ሊሆን የሚችለው ገዢ መደብ ነው። ህዝብን የሚጨቁን ገዢ የህዝብ ጠላት ነው። ስለዚህ መወገድ ይኖርበታል። ህዝብ ግን የሌላ ህዝብ ጠላት ሊሆን አይችልም።

‘የሸዋ አማራ’ የትግራይ ጠላት መሆኑ የሚነግሩን ደርግ በትግራይ ህዝብ ላይ የፈፀመውን ግፍ በማጣቀስ ነው። ደርግ ጨካኝ የነበረው ለትግራይ ህዝብ ብቻ አይደለም፤ አማራውም፣ ኦሮሞውም ሌላውም ተጨቁኗል። የአማራ ህዝብም “ደርግ አማራ ነው፣ የኛ ነው” ብሎ ከሌሎች ህዝቦች የተለየ ድጋፍ ለደርግ አልሰጠም። ደርግም “ለአማራ ህዝብ የቆምኩ ነኝ” አላለም። ደርግ “ለኢትዮዽያ የቆምኩ ነኝ” እያለ ሁሉም ኢትዮዽያውያንን በደለ።

ህወሓት ከስልጣን የሚወርድ ከሆነ ትግራይ ኢትዮዽያ እንዲሆን የሚፈልግ አይመስልም። ህወሓትና የትግራይ ህዝብ በተመሳሳይ ዕድሜ መመዘን ግን ስህተት ነው። ምክንያቱም የህወሓት የስልጣን ዕድሜ አጭር ነው። የትግራይ ህዝብ ግን ለዘላለም ይኖራል። በሌላ ስርዓት ሌላ ታሪክ ያስመዘግባል። ህወሓት ግን በምርጫ ወይ በጠመንጃ በቅርብ ግዜ መውደቁ አይቀርም፤ የተፈጥሮ ሕግ ነውና።

“ኢትዮዽያዊ ነኝ” ካልክ “የሸዋ ልሂቃን ደጋፊ ነህ” ይሉሃል። ኢትዮዽያ የሸዋ ፖለቲከኞች ብቻ የግል ንብረት ነች እንዴ? ኢትዮዽያኮ የሁላችን ነች። የትግራዮች፣ የአማራዎች፣ ኦሮሞዎች፣ ሶማሌዎች፣ ቤኑሻንጉሎች፣ ጋምቤላዎች፣ ዓፋሮች፣ ደቡቦች … የሁሉም ናት።

ኢትዮዽያዊ ማንነት ለተወሰኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ከሰጠነው ተሳስተናል። የፖለቲካ ተፎካካሪዎቻችን “ኢትዮዽያውያን ነን” ስላሉ እነሱን ለመቃወም “ኢትዮዽያውያን አይደለንም” ካልን ችግሩ የኛ ነው። ምክንያቱም ኢትዮዽያዊነታችን በራሳችን ፍቃድ ለሌሎች አሳልፈን ሰጥተናል ማለት ነው። ኢትዮዽያዊነት ለተወሰኑ ሰዎች ብቻ ማን ሰጠው? ኢትዮዽያውነት’ኮ የጋራ ማንነታችን ነው።

እያንዳንዱ ሰው የራሱ (የግሉ) የሆነ ማንነት አለው። በወረዳ፣ ዞን፣ ብሄር ወዘተም ቡድናዊ የግል ማንነት አለው። በኢትዮዽያ ደረጃ ደግሞ የሁላችን የጋራ የሆነ ኢትዮዽያዊ ማንነት አለን።

ፖለቲከኞች “እነዚህ ሰዎች ኢትዮዽያዊ ስሜት የላቸውም፣ በዘር ያስባሉ፣ ትክክለኛ ኢትዮዽያውያን እኛ ነን ወዘተ …” ብለው ካሰቡ ተሳስተዋል። ምክንያቱም ኢትዮዽያ የየተወሰኑ ግለሰቦች አይደለችም። ኢትዮዽያ የሁሉም ነች። ኢትዮዽያዊነት የተወሰነ ብሄር ወይ ክልል ወይ አውራጃ የሚወክል አይደለም። ሁሉም የኢትዮዽያ ህዝቦች የሚወክል ነው።

የኢትዮዽያ ህዝቦች እንደ አንድ ሰው አንድ ዓይነት ሃይማኖት፣ ባህልና ማንነት ሊኖራቸው አይችልም። በአንድ ሀገር የተለያዩ ሰዎች እስካሉ ድረስ የተለያየ ማንነት አለ (በብሄር፣ ወረዳ ወዘተም የተለያየ ማንነት ነው ያለው)። ስለዚህ ኢትዮዽያዊነት የአንድ ሰው ማንነት ሳይሆን የብዙ ሰዎች ማንነት ድምር ዉጤት ነው።

ስለዚህ ኢትዮዽያዊነት የጋራ ማንነት ነው። ኢትዮዽያዊነት አብሮነት ነው። እናም አንድ ግለሰብ ወይ የፖለቲካ ድርጅት “እኔ ነኝ ትክክለኛ ኢትዮድያዊ” ካለ ኢትዮዽያዊነት ወደ አንድ አከባቢ (ብሄር ወይ ክልል ወይ መንደር) አውርዷታል ማለት ነው። ይህም ስህተት ነው።

ኢትዮዽያዊ መሆን ከደበረን ችግር አለ ማለት ነው። ችግሩ ጭቆና ሊሆን ይችላል። ጭቆና (ለምሳሌ የብሄር ጭቆና) ካለ ጭቆናውን ለማስወገድ ሁሉም ኢትዮዽያውን ህዝቦች ተባብረው መፍታት ይኖርባቸዋል። ሁላችን ከተባበርን ችግሮችን (ብሄራዊ ጭቆናን) ማስወገድ እንችላለን።

ጭቆና ስለበዛብን ከኢትዮዽያ መገንጠል (አብሮነትን መቃወም) መፍትሔ ሊሆን አይችልም። እንበልና በትግራይ ህዝብ ወይ በኦሮሞ ህዝብ ላይ ብሄራዊ ጭቆና ተፈፅሟል። አሁን መታገል ያለብን በነዚህ ህዝቦች ላይ የነበረውን ብሄራዊ ጭቆና በማስወገድ ነፃነትና እኩልነት ማረጋገጥ ነው። ለዚህ ጉዳይ ሁሉም ዜጎች መተባበር ይኖርባቸዋል።

“ብሄራዊ ጭቆና ስለነበረ (ስላለ) መገንጠል እንፈልጋለን” የሚለው ሐሳብ አይመቸኝም። ምክንያቱም ጭቆናው ከነበረ አሁንስ ቢሆን እንዴት በመለየት መቅረፍ ይቻላል? ትግራዮችና ኦሮሞዎች ጭቆና የደረሰባቸው ባለፉ ስርዓቶች ከሆነ ላለፈው በደል አሁን በመገንጠል እንዴት መቅረፍ ይቻላል? ብሄራዊ ጭቆናው ያለው አሁን ድረስ ከሆነም ለመለየት ከመምረጥ አብሮ ታግሎ ጨቋኝ ስርዓቱ በመጣል እኩልነትን ማስፈን እየተቻለ ለመገንጠል ማሰብ ምን አመጣው?

ጨቋኝ ስርዓቱ ለማስወገድ አቅሙ ከሌለን ለመገንጠልም አቅሙ አይኖረንም። ምክንያቱም ከመገንጠል ስርዓቱን መቀየር ይቀላል። ምክንያቱም ለመገንጠል ብቻህን ነው የምትታገለው፤ ስርዓት ለመቀየር ግን ከኢትዮዽያውያን ወገኖችህ ጋር ነው የምትታገለው። ደግሞ በመገንጠል ጭቆና አይወገድም። ለእኩልነት ጠንክረው በመታገል እንጂ በመገንጠል ጭቆናን ያስወገዱ ህዝቦች የሉም።

ኢትዮዽያዊነቴ ለማንም አሳልፌ አልሰጥም። ኢትዮዽያዊነት ለ”ሸዋ አማራ” ብቻ የተሰጠ ማንነት አይደለም። ኢትዮዽያዊነት የሁላችን ነው።

 

ስም የማጥፋት ዘመቻ!???
—————————–

ህወሓቶች በኔ መጨነቅ የጀመሩ መሰለኝ (ስም የማጥፋት ዘመቻ መጀመራቸው ሳስብ ነው)። እርግጥ ነው የኔ ስም ማጥፋት / ማፍረስ አይችሉም። ምክንያቱም የኔ ስም አልተገነባም። ያልተገነባ አይፈርስም። እኔን አጀንዳ ማድረጋቸው (በዚህ ሳምንት በተለይ) ግን ለምን ይሆን?

መልሱ ቀላል ነው። ያሁን የህወሓት መሪዎችና የቀድሞ የህወሓት ታጋዮች መለየት በመቻሌና ለይቼ በመምታቴ ይመስለኛል። ህወሓቶች ከትግራይ ህዝብ ተለይተው እንዲታዩ አይፈልጉም። ምክንያቱም ተቃዋሚዎች የትግራይን ህዝብ ከህወሓት ጋር ደርበው ዒላማ ሲያደርጉት ህወሓት ከትግራይ ህዝብ ድጋፍ ያገኛል።

ስም ለማጥፋት አንዴ “አብርሃ የሚፅፈው ዉሸት ነው” ይላሉ፤ ሌላ ግዜ “የትግራይን ማንነት ትቶ ኢትዮዽያዊ ለመሆን ጥረት ያደርጋል” ይላሉ። የምፅፈው “ዉሸት” ከሆነ ለምን ት ሸበራላቹ? ዉሸት ከሚፅፍ ሰው በዉሸት የሚሸበር ሰው የባሰ ከንቱ ነው (እኔ የምፅፈው ዉሸት ነው ብላቹ ካመናቹ)። አዎ! አሁንም ኢትዮዽያዊ ነኝ። ምክንያቱም ትግራይ ነኝ። ትግራይ ደግሞ ኢትዮዽያ ነው።

ህወሓትን ከትግራይ ህዝብ ነጠልነው። አሁንም ከቀድሞ ታጋዮች ስንነጥለው ተሸበረ። አዎ! ለይተን አነጣጥረን መምታት አለብን።

ስም የማጥፋት ስትራተጂ የውድቀት መንገድ ነው።

 

 

17 Comments

  1. I wish opposition politicians have the same strategy of alienating WOYANE from the people of Tigray and by countering Woyannes anti Tigray sentiment that is the people of Amharas are not their enemies rather they are one of the most subjugated people by the same regime Woyannes refer as the AMHARA regime the WOLLLo famine and the subsequent GoJJAm peasant rebellion against heavy land taxes resulted in the bombardment of the GOJjAm peasants by both Hailesilassie and DERg

  2. Dear Abraha Desta! I always read your articles with deep interest. You are indeed one of those true democrats which our beloved Ethiopia badly needs.I admire the way you see things in our tormented homeland. Please take care of yourself in your daily life. God bless you!

  3. Ato Abraha Desta

    Sitting in Mekel ( The birth place of TPLF) I see you writing and speaking what comes to your mind. What kind of democracy are you expecting. I know there is no perfect thing in this world. As an ” intellectual” how do you see this.

  4. I see you are in the midst of fire, yet you are proudly proclaim that you a proud Ethiopian. That is courage in first order, my brother. Please do keep it up! I rebuke woyanne for the misrule it renders to my beloved country and its people simply because that is wrong. I am proud to see the Tigray that produces the likes of nega and zenawi who trouble our land for their benefit also gives us a young man like you. Yenat hod zigurgur yilol.

  5. This is- great message for blind supporter of TPLF . Every were you go if you oppose their idea , they named you Ahmara, but I am Amhara and Tigre but before my ethnic back ground I am Ethiopian , what is wrong with that., for me it. Is showing fear , inferiority complex, there is nothing to it . No one brag what ethnic back ground came from in our previous regimes just with woyanne but it will hunt them and pay the price for it . More power for Ethiopiawine !!!!

  6. What an interesting Ethiopian, keep it up.
    It takes a courage to think rationally from where you’re, brother.

  7. the main problem of the ethncicist fascist tigre people liberation front is accepting themselves as Ethiopians. If anybody calls himself Ethiopian, in the interpretation of TPLf, this means you are amhara. In the eyes of Tigre liberation front it is only the amharas who call themselves Ethiopians.

    If Amharas claim themselves to be Ethiopians, it is by choice. Anybody else can do the same. tplF CANNOT TELL THE AMHARA NOT TO CALL THEMSELVES AS ETHIOPIAN.

    TPlf have been working hard for 40 years, to erase the name Ethiopia from the face of the earth, because they see Ethiopia the same as amhara.

    But Ethiopia lives in the heart and minds of all its children within the current boundary of the country. Our fathers and forefathers died in the battlefield, in ADWA, in DOGALI, at METEMA, MAICHEW, in the OGADEN in Gudeberet, etc to build a country that we all know as Ethiopia.
    Whatever TPLF does to destroy Ethiopia and to cause mistrust, division, hatered and violence among its population Ethiopians will still come together and say NO to tplf. Ethiopia will live. TPLF WILL DISAPPEAR.

  8. Abreha,

    I am back with an idea to share. Yes, you are right you could claim to be a Tigre-Ethiopian or Amhara-Ethiopian. I think this kind of thinking is also a product of TPLF Ethinic based Federalism. I grew up in Addis and I do not remember labeling any of my friends as such. May be some Eritreans used to show it slightly. Assuming they were still Ethiopians.
    The other side is you can see yourself first Ethiopian and when it comes to details you would say “from Tigrai or Gojam,Gonder,Wolaita, Jimma…” It is specially true to those of us who live in abroad.

  9. በጣም ከማከብራቸው በጣምም ከማደንቃቸው ኢትዮጵያዊ መህል አንዱ ነህ ምንም መፈናፈኛ በሌለበት የምታወጣቸው ጹሁፎች እንዴት የሚያስብሉ ናቸው።ምክኒያቴ ምን መሰለህ የመጀመሪያው ፍጹም ነጻነት በማይታሰብበት ትግራይ ውስጥ ሆነህ ወያኔዎችን ስታጋልጥ እርኩስ ስራቸውን ስታጋልጥ ዝም ማለታቸው ሁለተኛው ምክኒያቴ ደግሞ ሆዳም አማራውን ሆዳም ኦርሞውን ያሌሎችን ብሄረሰቦች እንደ አላማ አምነውበት ሳይሆን በጥቅም የተገዙትን ትተህ ቁንጩዎቹ የወያኔ መሪዎች ይሁንኝ ብለው ኢትዮጵያን ለማጥፋት ላይ ታች ሲሉ ክትግራይ ተውላጆች ብዙ የሚሰማ እንደአንተ በአደባባይ በድፍረት የወጣ ሰው አልነበረም

    [ ይህንን ስል እነ ዶክተር ሀይሉ አ ር አያ እነ ገብረመድህን እና ሌሎችን ረስቼ አይደለም

    በጣም የማደንቅህ በጥምም የማከብርህ ኢትዮጵያዊ ነህ ከዛች የትግራይ ምድር እንዳንተ ስለ እውነት ስለ ወገን ስለ ሀገር በአደባባይ በመውጣት የሚያጋልጡ ያብዛልን አንተንም እንደ ሰው ተፈጥረው እንደ አውሬ ከሆኑ የዘመኑ የምድራችን ጉዶች እግዚአብሄር ይጠብቅህ

    እነዚህ ድሮም ቢሆን ይታወቃሉ ስለ ሀገር ብዙ ብለዋል ።

Comments are closed.

Previous Story

Sport: ዋሊያዎቹ የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ዋንጫ ላይ ይሳተፋሉ

Next Story

መድረክ በሳዑዲ መንግስት ላይ ስልፍ እንዳይወጣ በከለከለው ኢሕአዴግ ላይ ሰልፍ ሊወጣ ነው

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop