ዶ/ር ቴዎድሮስና ሌሎቹ !

ግርማ ጌታቸዉ ካሳ
Muziky68@yahoo.com

ኅዳር 11 ቀን 2006 ዓ.ም

ኢሕአዴግን እንደ አንድ የሚመለከቱ፣ ሁሉን አባላቶቹን በጅምላ የሚፈርጁ ጥቂቶች አይደሉም። ነገር ግን ኢሕአዴግ ዉስጥ የተለያዩ ቡድኖች አሉ። አንዱ የገነባዉን አንዱ ያፈርሳል። አንዱ ሲያነሳ አንዱ ይጥላል። አንዱ ሰላማዊ ሰልፍ ሲፈቅድ፣ አንዱ በጎን የዜጎችን ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት ይጋፋል። አንዱ የታሰሩ የሕሊና እስረኖች እንዲፈቱ ሲፈልግ፣ ሌላዉ «እዚያዉ ቃሊቲ ይበስብሱ» ይላል። አንዱ በጎና ቀና ሕሊና ሲኖረዉ፣ ሌላዉ ደግሞ የጠመመና የጫካ አስተሳሰብ ያለው ሆኖ ይገኛል።

በኢሕአዴግ ዉስጥ ያለው ተቃርኖ ሰሞኑን በጉልህ ለማየት ችያለሁ። ነገሩ እንዲህ ነዉ። በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን አሳዛኝ ግፍ ለመቃወም፣ በአዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያዉያን ወደ ሳዉዲ ኤምባሲ ያመራሉ። ወዲያዉ የደህንነት ሰራተኞች ባዙቃቸዉንና እና ዱላቸውን ይዘው፣ ሰልፉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ከማድረግ ይልቅ፣ ሰልፈኞችን መደብደብ ጀመሩ። ብዙዎች ታሰሩ።

ሰልፉ፣ የደህንነት ሰራተኞችና ፖሊሶች ሳይቀሩ ሊቀላቀሉት የሚገባ ሰልፍ ነበር። በሰልፉ የተነሳዉ ጉዳይ፣ ኢትዮጵያዉያንን በሙሉ ያዋረደ ጉዳይ ነዉ። ነገር ግን ፣ የዜጎቻችን መብት ተረግጦ በሳዉዲ የተፈጸመዉን ድብደባ ለመቃወም፣ በአገሩ የወጣዉ ሕዝባችን ተደብድቦ ተመለሰ።

በዚህ ጉዳይ ላይ ፣ አልጃዚራ እንደዘገበው፣ የኢሕአዴግ መንግስት ቃለ አቀባይ፣ አቶ ሽመለስ ከማል፣ አስተያየት ሰጥተዉበታል። «ሰላማዊ ሰልፉ ሕገ ወጥ ነዉ። ፍቃድ አልተሰጣቸውም። በኢትዮጵያዊያን መካከል ፀረ-አረብ ስሜት (anti-Arab sentiments) እንዲኖር ለማድረግ እየሞከሩ ነዉ። ስለዚህ ፖሊስ እርምጃ ወስዷል» ነበር ያሉት።

አቶ ሽመልስ እንዲህ ማለታቸውን ከአልጃዚራ ዘገባ ሳነብ፣ ልክ ወላፈን በፊት ያለፈ ይመስል በጣም ደነገጥኩኝ። ለማመን አልቻልኩም። ደቂቃዎች እያለፉ፣ ፍም ላይ እንደተጣደ ምጣድ፣ ዉስጤ መንደድ ጀመረ። የኢትዮጵያዉያን ስሜት ተጎድቶ ባለበት ወቅት፣ ቆስለን ባለንብት ወቅት፣ ግፍ ለፈጸሙብን አረቦች ስሜት የምንቆረቆርበት ጊዜ ነዉን ? ይህ አይነቱ የኢትዮያዉያንን ስሜት ክፉኛ የሚጎዳ አስተያየት ከአንድ ኢትዮጵያዊ ነኝ ከሚል፣ ያዉም የመንግስት ባለስልጣን፣ ይጠበቃልን ? በእዉኑ እንዲህ አይነት፣ ለሕዝብ ስሜትና ክብር ፍጹም ደንታ የሌላቸው ሰዎች ናቸዉን የሚገዙን ?

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ ከወዲሁ ያስመዘገባቸው ድሎች - ግርማ ካሳ

«በቂ የጥበቃ ኃይል እንዲኖር ዝግጅት ስላላደረግን፣ ሕዝቡም በንዴት ዉስጥ ስለሆነ ፣ የሳዉዲ ኤምባሲን የማቃጠል ተግባር ሊፈጸም ይችላል» የሚል ስጋት ኖሯቸው ሊሆን ይችላል፣ ሰልፉን በኃይል ያስቆሙት። ነገር ግን አንድ የዘነጉት ጉዳይ ቢኖር የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨዋ ሕዝብ መሆኑን ነዉ። ላለፉት 5 ወራት በተለያዩ የአገራችን ግዛቶች በርካታ ሰልፎች መደረጋቸውን ማስታወስ እፈልጋለሁ። አንድም ድንጋይ አልተወረወረም። አንዲትም ንብረት አልጠፋችም። እንደዉም በደሴ ሰልፈኞቹ ለፖሊስ አበባ ያድሉ ነበር። በርግጥ ሕዝባችን የተከበረ፣ የሚያኮራ፣ ጨዋ ህዝብ ነዉ።

አገር ቤት ያሉ ተቃዋሚዎች ሰልፍ ለማድረግ፣ በሕጉ መሰረት ባለስልጣናት ቢያሳዉቁም፣ አሁንም ሕገ መንግስቱ ተንዶ፣ ሰልፍ ማድረግ እንደማይችሉ ነዉ በደብዳቤ የተነገራቸው። እንኳን ሌሎች ድርጅቶች ሰልፍ ሲጠሩ መከልከል ቀርቶ፣ በዚህ አንገብጋቢ አገራዊ ጉዳይ፣ እራሱ ኢሕአዴግ ሰልፍ መጥራት ነበረበት። የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲክ ሳይንስ መምህር የሁኑት አቶ ሰይፉ ኃይሉ፣ በቅርቡ በለቀቁት ጽሁፍ « why not the government has arranged even public demonstration at least in our major cities to condemn the event and send message to the world?» ሲሉ ነበር የጠየቁት።

አሁን ደግሞ ወደ ሌላ የኢሕአዴግ ባለስልጣን ልዉሰዳችሁ። የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶር ቴዎድርስ አዳኖም። ኅዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ዶር ቴዎድሮስ፣ ከሳዉዲ የተፈናቀሉ ወገኖቻችን ጊዜያዊ ማረፊያ ድረስ በመሄድ እንዳጽናኑና እንዳበረታቱ ፋና ዘግቧል። በርግጠኘንት ማረጋገጥ አልቻልኩም፣ ግን ዶክተሩ፣ ስደተኞች፣ የአገራቸውን መሬት በአይሮፕላን ማረፊያ ተገኝተው እንደተቀበሏቸው የሚገልጹ አንዳንድ አስተያየቶች ፌስቡክ ላይ አንብቢያለሁ። ከአጥር አልፎ ሕዝብ ጋር መቀላቀል ማለት ይሄ ነዉ !!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ትልቁ ችግር ያለው ከውድቀት ከአለመማር እንጅ ከመውደቁ ላይ አይደለም ! - ጠገናው ጎሹ

ቅዳሜ ኅዳር 7 ቀን ዶር ቴዎድሮስ ፣ አዲስ አበበ በተደረገ ሶስተኛዉ የአለም ቀፍ ፋሚሊ ፕላኒንግ ኮንፍራንስ ላይ ያደረጉትን ንግግርም ማንሳት እፈልጋለሁ። «ዜጎቻችን ወደ አገር ሲመለሱ፣ ነገሮች በተስተካከለ ሁኔት እንዲሄዱ ለማድረግ እንሞክራለን። ሳዉዲዎች ሕገ ወጥ ናቸው (ከአገር ዉጡልን) ቢሏቸው፣ ግድ የለም፤ የሚሄዱበት አገር አላቸው። አጠንክሬ ላረጋግጥላችሁ ፣ ዜጎቻችን በአክብሮት እንቀበላቸዋለን» ነበር ያሉት። ከአንድ ጨዋ፣ የተማረ፣ በሳል መሪ የሚጠበቅ ግሩም ንግግር ! በአቶ ሽመልስ ከማል አይነቶቹ የደማዉ ልቤ ትንሽ ታደሰ።

ምን አለ ኢሕአዴግ እራሱን ከሽመልስ ከማሎች አጽድቶ ቴዎድሮስ አዳኖሞችን ቢያበዛ ? ምን አለ ባለስልጣናቱ የሚሰብርና ለሕዝብ ንቀት የሞላበት ንግግር ከሚናገሩ፣ የሚያሰባብስ፣ የሚያነጽ፣ የሚገነባ ንግግር ቢናገሩ ? ምን አለ ዜጎችን በማሰቃየት፣ በመደብደብ ፣ ሽብርተኞች እያሉ በማሰር፣ በማንገላታት ከሚደሰቱ፣ ዜጎች ሲጠቁ ማዘን ቢጀመሩ ? ምን አለ እንደ እንስሳ ከሚሆኑ እንደ ሰዉ ቢሆኑ ?

እንግዲህ እነቴዎዶሮስ አዳኖም የሚያረጉትን እያበረታታን፣ የተለየ ትእዛዝ እየላኩ፣ ዜጎችን የሚያስደበድቡ ፣ የዜጎችን መብት የሚረግጡና በዜጎችን መቆሳቆል የሚደሰቱ፣ የአገዛዙ ባለስልጣናትን ለማጥራት ሁላችንም ተባብረን መስራት ይኖርበናል። እነዚህ ግለሰቦች ለኢሕአዴግም ሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እርግማን ናቸው!!!! አገራችንን እንዲያምሱና እንዲያወኩ ሊፈቀድላቸው አይገባም።በተለይም የኢሕአዴግ ደጋፊዎች እነዚህ ሰዎች የድርጅታቸው ጠንቅ፣ ድርጅታቸው የበለጠ እንዲጠላ የሚያደርጉ መሆናቸውን አዉቀቁ፣ እነርሱ ላይ ዘመቻ እንዲጀምሩ አሳስባለሁ።

በመጨረሻ አንድ ነገር ጣል ላድርግና ላቁም። በዚህ ወቅት የ«ጠቅላይ ሚኒስቴራችን» ኃይለማሪያም ደስ አለኝ መሰወር ነዉ። እኝህ ሰው ዝምታን ለምን መረጡ ? ጋዜጠኛ ወሰን ሰገድ፣ «አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ “እስረኛ” ናቸዉ» በሚል አዉራምባ ታይምስ ላይ ባወጣዉ ጽሁፉ፣ ጠቅላይ ሚኒስተሩ የሕዝብን ትረታ እንዲያዳምጡ፣ ከአማካሪዎቻቸው አጥር እንዲወጡ፣ እንደመሪ አገር መምራት እንዲጀምሩ ጥሪ አቅርቧል። ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለማሪያም በ3ኛዉ የአፍሮ-አረብ ስብሰባ ላይ ለመገኘት (ሳዉዲዎችም ያሉበት) ወደ ኮዌት ትላንት ኅዳር 10 2006 ዓ.ም ቀን አመርተዋል። ከዚያ በኋላ ደግሞ በቀጥታ የተባበሩት መንግስት ክላይሜት ቼንጅ ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ወደ ዋርሶዉ ፖላንድ ያመራሉ።(የአለማችን የአየር ሁኔታ በወገኖቻችን ላይ ከደረሰዉ ግፍ በልጦ ማለት ነዉ)

ተጨማሪ ያንብቡ:  «ደሸት» የብርሃን እውነት! -ወለላዬ ከስዊድን

አቶ ኃይለማሪያም የተማሩ ሰው ናቸው። በዚህ ወቅት ከአገር ምንም አይነት መግለጫ ሳይሰጡ፣ ሕዝቡን ሳያበረታቱ፣ ከአገር ዉጭ መዉጣታቸው፣ ምን ያህል ተሰሚነታቸውን እንደሚጎዳ ያጡታል ብዬ አላስብም። ታዲያ ምን ነክቷቸው ነዉ እራሳቸዉን እንደዚህ የሚያገምቱት? ወደፊት በስፋት የምንነጋገርበት ይሆናል።

18 Comments

  1. Musky
    Here you go! You start to spit waste not idea as usual. Any tplf is barbaric and racist. Adanom is a jack ass. Of course you are a jack ass too. As a jack ass you are expecting something from hyena. Maferia!!!!

  2. Ato Girma thanks for your advise not to be judgemental but you should know tplfs plam is for 1century in Ethiopia so I am not sure you are building Dr Tewodroses image for next PM elections like all tplfs do don’t get me wrong the dude seems good but if he is tplf he should have blood on his hand We must contact G/medhin Araya about his criminal background as you know they all are

  3. አድሀኖም ሲናገር የሰማሁት አምኖበትም ይሁን ሳይፈልግ ተፈቅዶለትም ይሁን ሳይፈቀድለት አንድ በሀላፊነት ላይ ያለ ሰው መናገር የሚገባውን ነው የተናገረው።
    ሽመልስ ከማል ወይ ስር የሰደደ የህዝብ ጥላቻ አለበት ወይም በህዝብ የሚያስጠላ ስራ እነዲሰራ ተሰጦት ነው። የወያኔ ስራ አንዱ ጎሳዎችን ያጣላል አንዱ ደሞ አስታራቂ ሆኖ ይቀርባል።አድሀኖም ደህና ነገር የሚያወራው ምናልባት ደደቢት በረሀ በጥይት ጩሀት ወይም በእፅ መጠቀም አይምሮው ያልተዛባ ሊሆን ይችላል።በደርግ ዘመንም አልፎ አልፎ በስይሰተሙ ውስጥ ያሉ በጎ ሀሳቢዎች በአገሪቱ ውስጥ ሊመጡ የሚችሉ ተጨማሪ ጉዳቶችን ለማገድ ሞክረዋል።አድሀኖም አጋጣሚ ካገኘ የሀገሪቱን የኢኮኖሚና የፖለቲካ መንገድ ቢቀይር ጥሩ ይመስለኛል።

  4. Whay you the opposition has two tang like snake last time dr tewodros he was attaked at south afeica by the opposition now they are trying to prise him and creat devition among tplf that dosnt work its all deplomacy …..

  5. Tigre people liberation front is a violent fascsit and thuggish organisation which practices execution, torture, imprisonment of individuals who show dissent within its ranks.

    This is the same policy they use on the people of Ethiopia.

    I have heared a story about adhanom before which tries to put him as the good guy within TPLF. If this guy is as good as we are told, he should stand up in the assembly of the so called Ethiopian parliament and explain to the house about the terrible suffering of the Ethiopian people in saud arabia.

    He is a ‘foreign’ minister, and it is the job of a foreign minister to tell people about such things happening in foreign lands to Ethiopian nationals.

    He should use his office, and his appointment as a foreign minister to start a diplomatic campaign to address these issues.

    He should make help available to the victims of arab violence in saud arabia through the Ethiopian embassy and consul.

    Thre is no embassy to protect our people , what we are hearing is that the woyane have shut down the embassy and are sitting inside doing nothing.

  6. Ato Girma

    I think you became a public relation (PR) of doctor adhanom,he is the worst foreign minster Ethiopia ever had. Do not you know that what he said about the Ethiopian immigrants in saudi, he said explicitly that there is no any ill or bad treatment against Ethiopians exceptionally done by saudis comapairing to other foreign nationals. Where as on the ground the saudis were killing the Ethiopians on the streets of riyad.Adhanom, according to his press release, the woyane foreign minster seems as if he was a saudi official.
    Any how for woyanes, the saudis are their God fathers.Since they are bandas , they do not care for Ethiopia and Ethiopians.
    In case of shimeles and hailemariam, Both shimeles and hailemariam are puppets , who do not speak their mind.It is clear that they do not have any power, the power lies in the woyanes hand, they are their to please woyanes, i really do not understand you why you focus on them. last not least doctor adhanom is accountable for our citzens ill tretment in Saudi.
    Ethiopia will Prevail

  7. I have never seen a terribly castrated opportunist woshela like Girma Kassa. How many years does it need to know the banda woyane? Yenat kifu yelew she called Girma instead of butt. Is your skull full of water or brain? I know what is coming from your pen is sewage not ink.

    Do you know what adhanom’s barbaric body guards did to Ethiopians at home when they try to express their feelings against Saudi?

    Bilash neh Bilash

  8. I think what Shimeles has done was, more than any thing else, he incited the Arabs to rise up on Ethiopians. He has performed the same job as the Rwandan genociders and their public relations tugs, and the Kenyan past election time mass killing propagaters have done.The Rwandan and the Kenyan genocide inciters and participators have and are now facing trials under ICC.

  9. Who is girma? First of all shemels is just a dog which shouts when ever he hears a sound couse he was tought to shout if any thing passes around their fence by the owners. He is just another idiot not government official” bale mulu seltan aydelem” on the other hand did u expect teqodros to approve thw killing in public or u r one the propoganda guys for 2007 election of him. They r all the same they decide together they talk individualy. Shemeles is the bad guy and tedyman is thw gud muddy guy on this movie huh I wanna know the director of this movie don’t tell me its berwket again. Nway mr girma I want to remind u that tedy has more power than shemeles and would have prevented this idiot from bluffing if he want to but he didn’t couse its not written on the script. HD is another Girma woldegiorgis I don’t even wanna talk about him.let him enjoy going around the world before they kick his ass out.

  10. Mr. or Mrs. writer, I just want to remind you that at one occasion the current president of U.S said that a pig with lipstick is still a pig. Who cares about Adhanom’s personal gesture besides may be this is a down payment to end up becoming a prime minister. We the people have a serious issue with tplf as a government and Adhanom is member of it. If Adhanom has a good track record as an individual it will be upto the court of law to determine that. Other wise all teh tplfites are the root cause of our suffering and they need to be root out by any means necessary. Yes by any means necessary!

  11. Dear Girma,
    You are just portraying your utter shallowness. How on earth you are telling us the Mr Theodros is a better fascist? It is like comparing Himmler against Hitler and we should praise the less evil? Don’t get very emotional. Think about what this guy has been doing for the past 10+ years. It is not not about individuals, it is about the system!!! TPLF is a fascist and racist organisation. Every one that support this tyrannical party is an enemy of Ethiopia, period.

  12. Dr. Tewodros adhanom will be the next priminster of ethiopia and he will be tplfs leader…death to tigray ppl haters.

  13. You all tried to reflect your own ideologies. But nonsense. You all seem to look into yourself as custodian of this country. After all, who are you? Do something else, don’t waste your time staring at facebook. Don’t sharpen your tongue to insult! Nonsense and empty!

  14. Dr. Tewodros is a nice and intelligent person with complete personality I love the man! he deserves to be the Minister of Foreign affairs and even more than that!! full hatred will take us no where please .lets adhere to some elements of morality and humanity by recognizing the positive qualities of human beings irrespective of their political and other views.

Comments are closed.

Share