“የትግራይ ክልል መንግስት አዝዞ ነው”

በወልቃይት አካባቢ በዛሬማ ወንዝ ላይ በመገንባት ላይ የሚገኘው የዛሬማ ሜይዴይ የመስኖ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ለስቲዲዮ ጋሊ ኢንጂነሪንግ አማካሪ ድርጅትና ለኤፈርቱ ሱር ኮንስትራክሽን በህገ ወጥ መንገድ መሰጠቱን በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=pKU8igiCV3I&t=500s
ፕሮጀክቱ ሲጀመር 4 ቢሊዮን 180 ሚሊዮን ብር ነው ተብሎ የተያዘለት በጀት ሲሆን አማካሪ ድርጅቱ በ347.7 ፐርሰንት ጨምሮ ወደ ብር 14 ቢሊዮን 533 ሚሊዮን ከፍ እንዲል ማድረጉንና የ10 ቢሊዮን 353 ሚሊዮን ብር ልዩነት እንደተገኘበት በኦዲት ግኝቱ አስረድቷል
በኦዲት ግኝቱ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የውሃ፣መስኖ እና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኢታ ዶ/ር አብረሃም አዱኛ የዛሬማ ሜይዴይ የመስኖ ግድብ ግንባታ በስኳር ኮርፖሬሽን የተጀመረ መሆኑን በመግለፅ በቂ መረጃ እንደሌላቸው ተናግረዋል።
ፕሮጀክቱ ለሕወሓቱ ሱር ከንስትራክሽን እንዲሰጥ የተደረገበት ምክንያት የትግራይ ክልል መንግስት አዝዞ ነው ብለዋል::

ተጨማሪ ያንብቡ:  ከዋሽንግተንና አካባቢዉ የጋራ ግብረሃይል የተሰጠ መግለጫ

1 Comment

Comments are closed.

Share