የክልሉ አስተዳዳሪ አዴፓ ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ በተቀመጠበት በዛሬው ዕለ ባህርዳር ከተማ ሁለት ዓይነት የተቃውሞ ሰልፎችን አስተናግዳለች::
https://www.youtube.com/watch?v=pKU8igiCV3I&t=500s
አንደኛው ትናንት መከላከያ ሰራዊት በምዕራብ ጎንደር ዞን የፈጸመውን ግድያ በመቃወም ሲሆን ሌላኛው ከቤኒሻንጉል ጉምዝ እና ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው በባህርዳር የተጠለሉ ዜጎች መንግስት ይረዳቸው ዘንድ ለመጠየቅ ነበር::
ከቤኒሻንጉልና ኦሮሚያ የተፈናቀሉት ወገኖች መንግስት ምንም ድጋፍ እያደረገላቸው እንዳልሆነ በተደጋጋሚ መግለጻቸውን በዘ-ሐበሻ ድምጻቸውን ስናሰማ መቆየታችን የሚታወስ ነው::