December 17, 2018
2 mins read

ገነት ደርሼ መጣሁ ያለው የጠገዴ ነዋሪ ሕዝቡን ሲያሸብር ዋለ

93183

የጠገዴ ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ዛሬ እንዳስታወቀው አቶ ቀናው አበጀ የተባለው ግለሰብ በፈጠረው ወሬ አካባቢው ተሸብሮ ሰንብቶ ነበር፡፡ በጠገዴ ወረዳ ‹‹እርጎየ›› ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ይህ ግለሰብ ሕዳር 21 ቀን 2011 ዓ.ም ‹‹ከሌሊቱ 8፡00 ገነት ደርሸ ተመልሻለሁ፤ ሕዝቡ ሰኞ ቀን እንደሚጠፋም ፈጣሪ ነግሮኛል›› በሚል በማኅበረሰቡ ላይ መደናገርን ከፍተኛ መደናገጥን ፈጥሮ ቆይቷል፡፡ የኮሙኒኬሽን ፅ/ቤቱ እንደገለፀው ግለሰቡ ‹‹ገነት ስገባ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ነበር፡፡ በገነት ፈጣሪን ከአንዲት ሴት ጋር አግንቸዋለሁ፤ እሷም ማሪያም ትመስለኛለች›› ብሏል፡፡ በተጨማሪም ‹‹ይዤው ገነት ገባሁ›› ያለውን የጸሎት መጽሐፍ ፈጣሪ ተቀብሎ ‹‹ሕዝቡ ሰኞ ዕለት ይጠፋል›› ብሎ እንደነገረው በአደባባይ መናገሩ ታውቋል፡፡ በየትኛው ሰኞ ዕለት ሕዝቡ እንደሚጠፋ ባይታወቅም ‹‹በማኅበረሰቡ ዘንድ ሽብር ፈጥሯል›› በሚል አቶ ቀናው በቁጥጥር ስር መዋሉን ፅ/ቤቱ አስረድቷል፡፡

ግለሰቡ ገነት ደርሶ መምጣቱን እና ሕዝብ የሚያልቅ መሆኑን በእምነት እና በትምህርት ተቋማት አውጇል፡፡ አቶ ቀናው በፈጠረው ሽብር ምክንያትም ለተወሰኑት ቀናት ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠዋል፤ ነዋሪዎችም በስጋት አካባቢውን ለቀዋል ብሏል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤቱ፡፡ በመሆኑም የሀሰተኛ ወሬ በመንዛት በማኅበረሰቡ ላይ ችግር በመፍጠሩ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡
https://youtu.be/fabcQQpKeQU

93180
Previous Story

ባለቤት አልባ ህንጻዎች በተበራከቱባት አዲስ አበባ በመንግስት ተቋማት ያሉ ንብረቶችን ለመቆጣጠር አዲስ መስሪያ ቤት ሊቋቋም ነው

93186
Next Story

የቻይናው ዜድቲኢ ኩባንያ በታክስ ማጭበርበር ተከሰሰ፣ 10 ክስ ቀርቦበታል

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop