December 17, 2018
2 mins read

ገነት ደርሼ መጣሁ ያለው የጠገዴ ነዋሪ ሕዝቡን ሲያሸብር ዋለ

የጠገዴ ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ዛሬ እንዳስታወቀው አቶ ቀናው አበጀ የተባለው ግለሰብ በፈጠረው ወሬ አካባቢው ተሸብሮ ሰንብቶ ነበር፡፡ በጠገዴ ወረዳ ‹‹እርጎየ›› ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ይህ ግለሰብ ሕዳር 21 ቀን 2011 ዓ.ም ‹‹ከሌሊቱ 8፡00 ገነት ደርሸ ተመልሻለሁ፤ ሕዝቡ ሰኞ ቀን እንደሚጠፋም ፈጣሪ ነግሮኛል›› በሚል በማኅበረሰቡ ላይ መደናገርን ከፍተኛ መደናገጥን ፈጥሮ ቆይቷል፡፡ የኮሙኒኬሽን ፅ/ቤቱ እንደገለፀው ግለሰቡ ‹‹ገነት ስገባ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ነበር፡፡ በገነት ፈጣሪን ከአንዲት ሴት ጋር አግንቸዋለሁ፤ እሷም ማሪያም ትመስለኛለች›› ብሏል፡፡ በተጨማሪም ‹‹ይዤው ገነት ገባሁ›› ያለውን የጸሎት መጽሐፍ ፈጣሪ ተቀብሎ ‹‹ሕዝቡ ሰኞ ዕለት ይጠፋል›› ብሎ እንደነገረው በአደባባይ መናገሩ ታውቋል፡፡ በየትኛው ሰኞ ዕለት ሕዝቡ እንደሚጠፋ ባይታወቅም ‹‹በማኅበረሰቡ ዘንድ ሽብር ፈጥሯል›› በሚል አቶ ቀናው በቁጥጥር ስር መዋሉን ፅ/ቤቱ አስረድቷል፡፡

ግለሰቡ ገነት ደርሶ መምጣቱን እና ሕዝብ የሚያልቅ መሆኑን በእምነት እና በትምህርት ተቋማት አውጇል፡፡ አቶ ቀናው በፈጠረው ሽብር ምክንያትም ለተወሰኑት ቀናት ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠዋል፤ ነዋሪዎችም በስጋት አካባቢውን ለቀዋል ብሏል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤቱ፡፡ በመሆኑም የሀሰተኛ ወሬ በመንዛት በማኅበረሰቡ ላይ ችግር በመፍጠሩ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ገልጿል፡፡
https://youtu.be/fabcQQpKeQU

93180
Previous Story

ባለቤት አልባ ህንጻዎች በተበራከቱባት አዲስ አበባ በመንግስት ተቋማት ያሉ ንብረቶችን ለመቆጣጠር አዲስ መስሪያ ቤት ሊቋቋም ነው

93186
Next Story

የቻይናው ዜድቲኢ ኩባንያ በታክስ ማጭበርበር ተከሰሰ፣ 10 ክስ ቀርቦበታል

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop