December 17, 2018
2 mins read

ባለቤት አልባ ህንጻዎች በተበራከቱባት አዲስ አበባ በመንግስት ተቋማት ያሉ ንብረቶችን ለመቆጣጠር አዲስ መስሪያ ቤት ሊቋቋም ነው

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግስት ተቋማት ያሉ ንብረቶችን ለመቆጣጠር በቅርቡ አዲስ መስሪያ ቤት ሊያቋቁም እንደሆነ ተሰማ፡፡ ካፒታል ጋዜጣ እንደዘገበው አዲሱ መስሪያ ቤት የከተማውን አስተዳደር ተሸከርካሪዎች፣ ህንፃዎች፣ ቁሳቁሶችና የቢሮ መገልገያዎችን ሁሉ እየተቆጣጠረ የሚያስተዳድር ይሆናል፡፡

በተጨማሪም የማያስፈልጉና ያረጁ ንብረቶችንም የሚያስወግድ መስሪያ ቤት ነው፡፡ ከሁለት ሳምንት በኋላ የሚካሄደው የአስተዳደሩ ምክር ቤት ስብሰባ የዚህን የአዲሱን መስሪያ ቤት እጣ ፈንታ የሚወስን ይሆናል፡፡ በአሁኑ ወቅት የከተማው ንብረት በግል ድርጅት እየተዳደረ ይገኛል፡፡ ለአስተዳደሩ ቅርበት ያላቸው አንድ ምንጭ እንደተናገሩት እስካሁን ባለው ሁኔታ የከተማው አስተዳደር ያሉትን ንብረቶችና ህንፃዎች እንዲሁም ቤቶች በአግባቡ አያውቃቸውም፡፡

እኚሁ ምንጭ ሲናገሩ ‹‹በቅርቡ በተደረገ ጥናት መንግስት ንብረቱን በአግባቡ እያስተዳደረ እንዳልሆነ ታውቋል፡፡ አንዳንዶቹ ህንፃዎች ከከተማው አስተዳደር ጋር ምንም ግንኙነት ለሌላቸው ሰዎች ሁሉ ተከራይተዋል፡፡ አብዛኞቹ ንብረቶችም መታደስ የሚፈልጉ ናቸው›› ብለዋል፡፡ በመሆኑም አዲሱ መስሪያ ቤት ከተቋቋመ የመጀመሪያ ስራው የከተማውን አስተዳደር ንብረት መቁጠር ይሆናል፡፡
አዲስ አበባ ብሔራዊ ቴአትር ፊት ለፊት ባለቤት የሌለው ህንጻ መገኘቱ ይታወሳል:: በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በተለይ የዶ/ር አብይ አስተዳደር ከመጣ ወዲህ የተለያዩ ባለቤት አልባ ህንጻዎች እየበዙ ነው::
በተለይም ባለቤት እና ሰው አልባ ኮንደሚኒየሞች በአዲስ አበባ መገኘታቸውን ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም መዘገቡ አይዘነጋም::
https://youtu.be/fabcQQpKeQU

12
Previous Story

ካሳ ተ/ብርሃንን ጨምሮ 12 አምባሳደሮች በአስቸኳይ ተጠሩ

93183
Next Story

ገነት ደርሼ መጣሁ ያለው የጠገዴ ነዋሪ ሕዝቡን ሲያሸብር ዋለ

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop