የሕወሐት ኢሕአዴግ መንግስት በልጆቼ ለምን ዘመተ? (ከኣስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል)

ሁለተኛ ልጄ ክብሮም እንደ ወንድሞቹ የእስር ሰለባ ሆነ፡፡እኔ ለኢትዮፕያ ህዝብ ጠላት ሳልሆን ፍፁም ወዳጁ ነኝ መጀመርያ ደርግን 17 ኣመት በመታገል ፋሽሽታዊ ደርግ በማስውግድ ኣስተዋፅኦ ነበረኝ፡፡ ህውሃት ኢህኣደግ ስልጣን ከያዘ በሃላም ለንሮየ ለደሞወዝ ሳላስብ 17 ኣመት ሙሉ የታገልኩበት ኣላማ ስለተቀለበሰ በተጨማሪ የህውሓት መሪዎች ለኢቲዮፕያ ሉኣላዊነትና ኣንድነት ታማኝነት ስላጎደሉ የኢትዮፕያ ሕገመንግስት በሚፈቅደው መሰረት በግልም በፓርቲ ተደራጅቼ እየታገልኩ ቆይቼ ኣሁንም እታገላለው ታድያ እኔ በሃገራችን ሕ/መንግስት በሚፈቅድልኝ መሰረት መታገሌ እንደ ሃጠያት ተቆጥሮ የቂም በቀል ፖለቲካ ወደ ልጆቼ ምን ኣመጣው ይህ ለማለት የፈለጉኩት፡፡

1.የማነ ኣስገደ ልጄ ምንም ሳይፈፅም በገጠር ቤተሰብ ለመጠየቅ ሄዶ ታስሮ ብዙ ግፍ ተፈፅሞበታል በተፈፀመበት ግፍ ጠንቅ ታሞ እናቱ የመከላክያ ኣባል ስለሆነች በመከላክያ ሚኒስተር ሆስፒታል ብዙ ጥረት ተደርጎ ሊያድኑት ስላልቻሉ ወደ መቀሌ ዓይደር ሪፈራል ሆስፒታል ከስልጣን በላይ ብለዉት ሂወቱ ተርፎ ኣሁንም በቤቱ ታሞ የኣልጋ ቁራኛ ሆኖ ይገኛል፡፡ በተማረው መሰረት ለሃገሩ እንዳያገለግልም እንደማይሰራ ኣካል ጉዳተኛ ኣድርገዉታል ወደ ውጪ ወስድን እንዳናሳክመው ኣቅም የለም፡፡

2.ኣሕፈሮም ኣስገደ ልጄም ከስራ ገብታው ኣፍነው ወስደው ታስሮ በፖሊስ ጣብያ 6 ወር ታስሮ ክስ ሳይመሰረትበት በቀዳማይ ወያኔ ፍርድ ቤት ምድብ ችሎት ከ 15 ጊዜ በላይ ቀጠሮ ጊዜ እየተባለ ሲመላለስ ከርሞ በመጨረሻ ክሱ የዋስ መብት የሚከልክለው የፀረ ሙስና ኣንቀፅ በሙስና የተከሰሰ የዋስ መብት ኣይፈቅድም የሚል ሽፋን ልጄን ከእሱር ላለማውጣት ክሱ ወደ ፀረ ሙስና ኮሚሽን በማዞር የፀረ ሙስና ጉዳይ ደግሞ በወረዳ ስለማይታይ 6 ወር ሙሉ ሲያንገላቱት ከርመው ክሱ በመቀሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንደ ኣዲስ ተመስርቶ በ 28/1/2006 ዓ.ም በዞኑ ፍርድ ቤት ቀርቦ ፀረ ሙስና ኮሚሽን ደግሞ ሌላ ተጠርጣሪ ስላለና ስለታጣ በጋዜጣ ኣሳውጀን እስከ ምንፈልግ ኣሕፈሮም በወህኒ ቤት ይግባ በማለቱ ልጄ ያለ ፍርድ በወህኒ ቤት ተወርውሮ ይገኛል የጊዜ ቀጠሮ እየተባለ 7 ወሩ በስቃይ ይገኛል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልፈለጉት መጠን… ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው - ሰርፀ ደስታ

3. ሌላ ያሁኑ ይባስ ክብሮም ኣስገደ የሚባል የ 10ኛ ክፍል ተማሪ የስብእና መሳት ስነ ኣእምሮ ችግር ያለው ይህም በሃኪም ክትትል ላይ ያለ በፍርድ ቤትም ታይቶ ያደረ በካስ ሜዳ እየተጫወተ እያለ ፖሊሶች ይዘው በእስርቤት ኣግብተው በኣንድ ጨለማ ቤት ለብቻው ኣስረው ከወላጆቹ ከሃይማኖት ኣባት ከህግ ኣማካሪ እንዳይገናኝ ኣድርገው ኣፍነዉት ይገኛሉ የምንሰጠው ምግብ ለማን እንደሚሰጥ ኣናውቅም ለፍትህ ቢሮ ፖሊስ ኣዛዞች ኣመለከትን ፍትህ ኣልተገኘም ዳኛ እንድያገናኙን በስልክ ነግሮዋቸው ፖሊሶች ኣልተቀበሉትም ኣሁን 80 ሰኣት በላይ ታስሮ ቤተሰብ ልናገኘው ኣልቻልንም ይህ ዘመቻ በእኔ የጀመረው ልጆቼም የግፍ ሰለባ ሆነዋል የኔ ጉዳይም የህውሓት የ17 ኣመት ታሪክ በመፃፌ ከኣንድ ዜግነቱ ኣሜሪካዊ ትውልድ ኢትዮፕያዊ በሰዎች የተቀናበረ ሴራ ተከስሼ 3 ኣመት ባስቆጠረ ክስ ላይ ነኝ ገና መቃጫ ኣላገኘም፡፡

ይህ ጉዳይ የእኔና የልጆቼ ብቻ ችችግር ኣይደለም ብዙ የሚናገርላቸው ያጡ ዜጎች በስቃይ ላይ ይገኛሉ ስለሆነ ሁሉም ዜጎችና ለፍትህና ለዲሞክራሲ ለሰብኣዊ መብት የምትታገሉ ያላችሁ ተቃዋሚ ሃይሎችም ዝምታ ከመምረጥ ብትነጋገሩበትና ብትቃወሙት ጥሪየን ኣቀርባለው፡፡

በተለይ በኣሁኑ ጊዜ ኣንድ ኣንድ የፖሊስ ከፍተኛ መኮነኖች በታሰረው ልጄ ኣሕፈሮም ኣስገደ ከታሰረበት የእስር ቦታ ሄደው ኣባትህ ኣስገደ ተው ኣርፈህ ተቀመጥ ትእግስት ኣድርግ እስከማለት ሄደዋል ለዚሁ አንደ ምሳሌ ኮማንደር ገ/ሂወት ካሕሳይ የመቀሌ ከተማ ፖሊስ ዋና ኣዛዠ ይጠቀሳል በዛ በሰጠው ማስፈራርያ ታድያ ልጄ ኣሕፈሮም በትልቅ ስጋት ላይ ይገኛል ታድያ ከዝሂች ኣገር ኣገሬ የት ልሂድ ንፁህ ዜጋ ነኝ እና በዚህች ኣገር የዳኝነት እና የህግ የበላይነት መረጋገጥ ኣለበት ወተደራዊ ኣገዛዝ እንዳይደገም እንጠንቀቅ ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  ጭራቅ አሕመድ ግርማ የሺጥላን ገድሎታል - መስፍን አረጋ

እባካችሁ የቂም በቀል ፖለቲካ ለልጆቻችን ኣናውርሳቸው ሰላም ፍትህን ዲሞክራሲን እናውርሳቸው፡፡

9 Comments

  1. የባህላዊ ቡድን ማንነት ፖለቲካ ኣራማጅነት ኣንዱ መገለጫ ይሄ ነው። ወያኔ ኣንድ ተቃዋሚ የሰላ ተቃውሞ ካቀረበበት ቶሎ ማጥቃት የሚፈልገው የዚያን ተቃዋሚ የትውልድ ቦታና ባህላዊ ቡድን ነው። ወያኔ የሚያስበው በዘር እየሰፈረ ነው። ከዚህ ኣስተሳሰብ መውጣት ኣልቻሉም።

  2. የባህላዊ ቡድን ማንነት ፖለቲካ ኣራማጅነት ኣንዱ መገለጫ ይሄ ነው። ወያኔ ኣንድ ተቃዋሚ የሰላ ተቃውሞ ካቀረበበት ቶሎ ማጥቃት የሚፈልገው የዚያን ተቃዋሚ የትውልድ ቦታና ባህላዊ ቡድን ነው። ወያኔ የሚያስበው በዘር እየሰፈረ ነው። ከዚህ ኣስተሳሰብ መውጣት ኣልቻሉም።

  3. Yebekel politics merzu kifu new? Mechèm be aregawi edmewo eyayu yalew gif yemaninim balehilina lib yemisebr new. 17 ye afla wetatinet zemenwon sewitew yegedelulet ena yekoselulet sirat endih sibediliwo min yahil kentu lifat ena kisara be hager lay endaderesu sitaseb yasafiral. 17 amet metagelwo ager lematifat mehonu ayakoram. Tagyalehu kalu enho letifat mehonun kersiwo belay misikir yelem! Beza betìgle zemen yegedelachuachew ena yemotubachu wegenoch yewodemew habt ena nibret yebakenew edmè kentu yekentu kentu kisara neber. New. Bametacìhut sirat miknyat enderswo yakomutin mengst tegedadrew sayhon bezer ena be haymanotachew miknyat bicha ke afer gar wilew afer meslew yeminoru zegoch tasrewal motewal tesedewal tesekaytewal. Bekel yikir yalut lenegew new enji zarema sint gif erswo arbegna behonulet sirat tefetsme!

  4. አቶ አስገደ የኖሩበት እና የታገሉበት ድርጅት ሰው በላ መሆኑ ጠፍቷቸው ሳይሆን የመጣውን ሁሉ ለመቀበል ዝግጁ ሆነው የገቡ ይመስለኛል:: ሆኖም ግን ማር ሲበዛ ይመራል እንደሚባለው እየተደረገ ያለው ነገር መፈጠርን የሚያስጠላ በመሆኑ ሁላችንም የምንችለውን የማድረግ ግዴታ አለብን። በሽዎች ለሚቆጠሩ ኦሮሞ አማራ ትግሬ …. እስረኞች ድምጻችንን አጠንክረን ሃይላችንን አስተባብረን ነጻ ልናወጣቸው እንነሳ እላለሁ::

  5. Why is DERG fascist? DERG was brutal and tyrannical, but not fascist. The characteristics of fascism is found only in woyanne. DERG is a military junta that does not care about anyone’s tribe. It just trampled on everybody’s right throughout Ethiopia. I also might add that DERG was patriot. It loved Ethiopia, and it was ready to defend it. It can not be said the same for wicked woyanne. It’s defense force is not for the protection of our beloved country, but it is solely designed for the dominance of a few Adwa mendertegna. Meles once said he no longer accept the dominance of Amara, but of course we have to accept the dominance of his Adwa half Eritrea friends simply because they have got guns.

  6. How people fail to know their organization in 17 years? Sory I don’t believe agames and Eretrians. They are so unpredictable. It was dead wrong to struggle for weyane in the fitst place. I don’t trust anybody who has worked and is working with shabia and weyane. I think this guy and Abraha o the mekele are trying to fool us as if they are real oppositions. Don’t trust any Tigrey after seeing Tesfaye G/Ab.

  7. @Gudu ewnetim gud neh ante. Bematawkew lemin tizebarikaleh. Politica eko eka eka aydelem. Silemitawkew new metsaf yalebih. Yihe sewye yeweyanien maininet betiru hunet lemechiw tiwlid metsihaf siletsafe new endezih eyasekayut yalut ena ahun esu egnan bilo simeta alaminihim tilewaleh. Egziabher mastewal yisten lehulachin. Ato Asgede Egziabher yirdah. Hulachinim beminichilew eniredahalen.

  8. በመጀመርያ ሁሉም የመጻፍ, የመናገር የመቃወም መብታችን ለማስከበር ብለው ነበር የታገሉት ስንቶቹን ህይወታቸው የተሰውት፡ ትግራይን ከተቆጣጠሩ በኃላ ራሳቸው ወጣቶችን ያለ ምንም ጥፋት ማሰቃየት ማሰር መግደል ሆነ ስራቸው። ደርግ እንካን የብጥይት ክፈሉና ሪሳችሁን ውሰዲ ነበር የሚለው እንጅ በወላጅ ሰበብ ልጆችን ኣላሰረም ኣላስውቃየም። ኣስገደ እኮ ስብእና ስላለው ነገረን እንጂ ስንቶቹን እኮ በእስር የሚማቅቁ ኣሉ። በኤርትራ ጦሩነት ሔሊኮብተሩ ስለተመታች የተሰዋ ነባር ታጋይ የነበረ ሽሻይ በላይ በወንድሙ ቢተው በላይ ምክንያት ልጆቻቸው እኮ ለስንት ኣመት በመለስ ኣስተዳደር ተሰቃይተዋል። ለመድረክ ደገፍክ ብለው የስንት ኣባት ኣረጋዊ በዱላ ደብድበው ኣልገደሉትም እንዴ፣
    የሚገርመው ደግሞ እነዚህ ኣሳሪዎችና ደብዳቢዎች ወላጆቻቸው በደርግ የተሰቃዪና የተገደሉ እኮ ናቸው ደግሞ ምንሊክ ኣማራ በደለን እያሉ የጥላቻ ምርዝ ይነዛሉ ወይ ትግራይ በእነ ማን እጅ ወድቀሻል

Comments are closed.

Share