ግንቦት 7 ለአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ንግግር ምላሽ ሰጠ – “ኃ/ማሪያምንና ጌቶቹን እንዲህ ያቃዣቸዋል?”

ግንቦት 7 የፍትህና የዴሞክራሲ ንቅናቄ በወቅታዊ ርዕሰ አንቀጹ ከቀናት በፊት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ለጋዜጠኞች ለሰጡት ቃለ ምልልስና በተቃዋሚዎች ላይ ላቀረቡት ክስ ምላሽ ሰጠ። የግንቦት 7 ምላሽ ሙሉ ቃል እንደወረደ የሚከተለው ነው፦

ኃይለማሪያም ደሳለኝ በአንድ ወቅት ዉሸትን የማያዉቅ ጠንካራ ክርሰቲያን ነዉ ተብሎ ሲነገርለት ሰምተን ነበር፤ ታድያ ይህ ሰዉ መለስን ሲተካ ብዙዎች በጥርስ የለሽ አንበሳነቱ ቢስማሙም ዉሸት እንደ ንጉስ በነገሰባት ኢትዮጵያ ዉስጥ ዉሸት የማያዉቅ መሪ መጣ መባሉ ብዙዎቻችንን ነጻነት የተገኘ ያክል አስደስቶን ነበር። ሆኖም ከወያኔ ጋር የዋለ ሰዉ እራሱን ሆኖ መክረም አይችልምና ኃይለማሪያምም ባስቀመጡት ቦታ የማይገኝ የሌላ መንደር ሰዉ ሆኖ ተገኘ። በዚህም የዜጎችን ተሰፋ አመከነ፤ ደስታቸውንም ወደ ኃዘንና ትካዜ ለወጠው።

ባለፈዉ ሳምንት መጨረሻ ላይ በመገናኛ ብዙኋን ፊት ያየዉን አላየሁም፤ የሰማዉን አልሰማሁም፤ ያልሆነዉን ሆነ የሆነዉን ደግሞ አልሆነም እያለ ሽምጥጥ አደርጎ የካደዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝ፤ በእርግጥም ጎበዝ የመለስ ዜናዊ ተማሪ መሆኑን በተግባር አስመስክሯል። ኃይለማሪያም ባለፈዉ ዓርብ አንድ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር። ይህ ግለሰብ በዚህ ጋዜጣዊ መግለጫዉ ኢትዮጵያን ያክል ትልቅ አገር ከሚመራ ሰዉ ቀርቶ ከአንድ ተራ የቢሮ ተላላኪ እንኳን የማይጠበቅ መልስ ሲመልስ ተስተዉሏል።

ኃይለማሪያም በጋዜጣዊ መግለጫዉ ወቅት ከቀረቡለት ብዙ ዲሪቶ ጥያቄዎች ውስጥ አንዱ አገር ቤት ውስጥ እየተደረገ ያለው ሠላማዊ ሰልፍ ጉዳይ ነበር። ኃይለማሪያም አገር ቤት የሚደረጉ የተቃውሞ ሰልፎች “በራሳቸው የሚደረጉ ሳይሆኑ ከኋላ ባሉ ሌሎች ኃይሎች መሪነት የሚደረጉ” ናቸው ሲል ተናግሯል። ኃይለማሪያም ጌቶቹ ፊቱን በጨርቅ አስረዉት የኢትዮጵያ ህዝብ ችግር፤ መከራና ስደት አልታይ ብሎት ነዉ አንጂ ወያኔን የመሰለ ነብሰ ገዳይ ባለበት አገር ዉስጥ የህዝብን ብሶት የሚያስጋቡ ጥያቄዎች በየቀኑ ይመነጫሉ አንጂ ከዉጭ አገርማ አይመጡም። በሌላ በኩል ደግሞ ይሄዉ ኢትዮጵያ በቅርቡ ያፈራቸዉ ዋሾ ሰዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች የሚያደርጉት ሠላማዊ እንቅስቃሴ የአሸባሪዎች እጅ ያለበትና፤አማኞቹ ሃይማኖታቸውን የወደዱ መስሏቸው ሳያውቁ የገቡበት ስለሆነ እንዲታረሙ እንመክራቸዋለንም” ብሏል። እዚህ ላይ በግልጽ እንደምናየዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝ እመራዋለሁ የሚለዉን ህዝብ ጥቅምና ፍላጎት ፈጽሞ ሊረዳ አልቸለም፤ ስለዚህ ምክር የሚያስፈልገዉ መብትና ነጻነት ምን እንደሆኑ ገብቶት የሚታገለዉ የአትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን ኃይለማሪያም እራሱ ነዉ።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሼህ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ኪሳራ በሚነሶታ!  እውን አላሙዲ የገንዘብ ድጋፋቸውን ይቀጥሉ ይሆን?

እኛ ግንቦት ሰባቶች ወያኔን የመሰለ ጨካኝ እና ምንም አይነት አገራዊ ኃላፊነት የማይሰማውን ዘራፊና ዘረኛ ቡድን በሠላማዊ መንገድ የሚጋፈጡ ወገኖቻችንን እናደንቃለን። እነዚህ ወገኖቻችን ኃይለማሪያም ደሳለኝ እንደሚለው የማንንም አጀንዳ የተሸከሙ ሳይሆኑ የራሳቸው የሆነ አጀንዳ ያላቸውና ኃይለማሪያም በዉክልና ለሚያስረግጣቸዉ ወገኖቻችዉ መብትና ነጻነት የሚታገሉ ጅግኖች ናቸዉ። አጀንዳቸውም የተደበቀ ወይም ከጀርባውም ሌላ ነገር ያለው አጀንዳ አይደለም።አጀንዳቸው ግልጽ እና የታወቀ የነፃነት፤ የእኩልነት፤የፍትህና የሠላም አጀንዳ ነው። ኃይለማሪያም ደሳለኝ የዜጎችን ጥያቄ አድምጦ መልስ መስጠት ሲገባው እነዚህን የኢትዮጵያን ህዝብ አጀንዳ ተሸክመው የሚታገሉ ወገኖች ደካሞች አድርጎ ለመሳል የሚያደርገዉ ሙከራ አንድም በተቃዋሚዎቹ ዙሪያ የተሰባሰበውን የሰው ኃይል ካለማወቅ፤ አለዚያም ደግሞ “ሊበሏት ያሰቧትን አሞራ ይሏታል ጅግራ” እንደሚባለው ነገር ነው።

ሌላው ኃይለማሪያም የሚናገረዉ ቃል ጠፍቶት በተደጋጋሚ ሲንተባተብ የታየዉ በሽብርተኝነት አካባቢ የተጠየቀዉን ጥያቄ ሲመለስ ነዉ። በእኛ እይታ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዋነኛው አገር በቀል አሸባሪ ህወሃት እና ህውሃት ብቻ ነው። ህወሃት ስልጣን ላይ ያቆየኛል ብሎ ከገመተ የማይመሰርተው የክስ ዓይነት፤ የማያፈሰው የንጹህ ሰው ደም ፤የማያፈነዳው የቦንብ እና የፈንጂ ዓይነት እንደሌለ ከሃውዜን እስከ አዲስ አበባ ያሉ መንገዶች ቋሚ ምስክሮች ናቸው። ይህንን እኩይ ተግባሩን ዓለም ሁሉ እንደሚያውቀው በዊክ-ሊክ ላይ የወጣው መረጃም አሳይቷል።

የህውሃት ታማኝ ሎሌ የሆነዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሠላማዊ ትግሉን ለማፈን ከፈለገ በትግሉ ዙሪያ የተሰባሰቡትን ዜጎች ከሌላ ከማንም ጋር ማነካካት አያስፈልገውም። ኢትዮጵያ ውስጥ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ሁሉ አንደ ኃይለማሪያም ሞቶ የተቀበረን ሰዉ ራዕይ የተሸከሙ የአመለካከት ደሃዎች ሳይሆኑ የራሳቸው አስተሳሰብና ህያዉ ራዕይ ያላቸው ዜጎች ናቸው። አነዚህን ሠላማዊ ታጋዮች ከማይገናኝ ሌላ ኃይል ጋር አቆራኝቶ ለመምታት መሞከር ለኃይለማሪያምም ሆነ ለጌቶቹ አይበጃቸዉም። ዛሬ በወያኔ ነብሰ ገዳይ ወታደሮች ተከብቦ እዩኝ እዩኝ የሚለዉ ኃይለማሪያም ደሳለኝም የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጣ የነደደ ቀን ደብቁኝ ማለት ይመጣልና ያ ቀን ከመምጣቱ በፊት የበደለዉን ህዝብ ይቅርታ ጠይቆ የነጻነት ኃይሎችን እንዲቀላቀል ወገናዊ ምክራችንን እንለግሳለን።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኦሮሚያ የሽግግር መንግስት ? የኦሮሚያ መከላከያ ስራዊት በርግጥ ታስቧልን ? አቶ ጀዋር ሙሃመድ እና ፕሮፌሰር ህዝቄል ጋቢሳ በጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ ይጠየቃሉ

በመጨረሻም ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ስለ ግንቦት ሰባት ተጠይቆ ሲመልስ ግንቦት ሰባት “በህልም ውስጥ ያለ ድርጅት” ነው ብሏል። ታድያ ምነዉ ተኝቶ ህልም የሚያልም ድርጅት ኃ/ማሪያምንና ጌቶቹን እንዲህ ያቃዣቸዋል? ለምንስ ይሆን ወያኔና ታማኝ ሎሌዉ ኃ/ማሪያም ያገኙትን ሁሉ ግንቦት ሰባት እያሉ የሚያስሩት፤ የሚደበድቡትና የሚገድሉት? ያገኛችሁትን ሁሉ የግንቦት ሰባት አባል እያላችሁ ትከሳላችሁ? ለምንስ በግንቦት ሰባት ስም ታስራላችሁ? ትገርፋላችሁ? ትገድላላችሁ? ተኝቶ ለሚያንቀላፋ ድርጅት ለምን ትሸበራላችሁ፤ ለምንስ እንቅልፍ አጥታችሁ ትባዝናላችሁ? ግንቦት ሰባት እናንተ አልገባችሁም አንጂ መነሻውንና መድረሻውን አጥርቶ የሚያውቅ፤ ከደመናው ባሻገር ፍንትው ያለ የነፃነት ዉጋገን የሚታየው ባለ ታላቅ ራዕይ ድርጅት ነው። አስኪ ምናልባት ቢገባችሁ ተረት ቢጤ እንንገራችሁ፤

“አንዲት ሚዳቋ ነበርች አሉ። ሚዳቆ ከመሬት ገንዘብ ተበድራ ሲትኖር ከእለታት አንድ ቀን መሬት አፍ አውጥታ ብድሬን መልሽ አንጂ ብላ ትጠይቃታለች። ሚዳቆዋም ደንግጣ ከነበረችበት ቦታ ፈትለክ ብላ ወደ ተራራ ጫፍ ላይ ወጥታ እፎይ ያንን ድምጽ ከአሁን በኋላ አልሰማም አለች። መሬትም በይ ብሬን ክፈይኝ ስትል ዳግም ጠየቀቻት። እንዴ ይህች መሬት የሌለችበት ዬት አገር ሊሂድ ብላ ሚዳቆ ወደ ማይታወቅ ቦታ ተፈተለከች። ከዚያም እያለከለከች በቃ አሁንስ አታገኚኝም ስትል አሁንም መሬት ብቅ ብላ እየጠበኩሽ ነውኮ ብድሬን ክፈይ እንጂ ስትል ጠንከር አድርጋ ጠየቀቻት። ሚዳቆዋም መሬት የሌለችበት ልትደረስ ስትበር ስትበር ሳንባዋ ፈንድቶ ሞተች”ይባላል።

የፍትህ፤ የእኩልነት፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች እንደ መሬት ናቸው። የትም ሂዱ፤ የትም ግቡ ይከተሏችኋል። መስጊድ ዉስጥ አሉ፤ ቤተክርስትያናት ውስጥ አሉ። ቤተመንግሰት ዉስጥም አሉ። የሌሉበት ቦታ የለም። መፍትሄው እንደ ሚዳቆዋ መሸሽ አይደለም። መፍትሄው ዜጎች የሚያነሷቸውን የፍትህ፤ የእኩልነ፤ የነፃነትና የዲሞክራሲ ጥያቄዎችን አድምጦ ትክክለኛ መልስ መስጠትና ከዕዳ ነጻ መሆን ብቻ ነዉ ። ከዚህ ዉጭ ጥያቄን ላለመስማት ወይም ሰምቶ ለመደፍጠጥ የሚደረገው ከንቱ ሩጫ መጨረሻው እንደ ሚዳቆዋ መፈንዳት እንጂ ህይወት አይሆንላችሁም።

ተጨማሪ ያንብቡ:  የዐድዋ ፡ ዘላለማዊ ፡ ድል ፡ ባተራማሽና ፡ ባጥፊ ፡ ስያስ ፡ አይደብስም  - ኢ.ሀ.ሥ.አ

እኛ ግንቦት ሰባቶች ዘረኛዉንና አሸባሪውንና የወያኔ ስርዐት ለመደምሰስና ህዝብ በነፃነት ያለፍርሃት የሚኖርበትን አገር ለመፍጠር ቆርጠን ተነስተናል። ከእንግዲህ የሚያቆመን ምንም ነገር የለም። የምንታገለዉ ለህዝብ ጥያቄያችንም ህዝባዊ ጥያቄ ነዉና እኛም አንደጥያቄዉ በየመስጊዱ፤ በየቤተክርሲቲያኑና በየሰፈሩ ዉስጥ አለን።እኛ የሌለንበት ስፍራ የለም። በዚህ አጋጣሚ የዘመናት ትግላችን ፍሬዉ የሚታይበት ቀን እጅግ በጣም ቅርብ ነዉና የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም አገር ተረካቢ የሆነዉ ወጣቱ ትዉልድ እራሱን፤ ወገኖቹንና እናት አገሩን ለማዳን የሚደረገዉን የነጻነት ትግል እየመጣ እንዲቀላቀል ወገናዊ ጥሪያችንን አቅርበናል። ኑ እና ተቀላቀሉን።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

15 Comments

  1. Batam be genefele semet yetetsafe new. Poletikegna eko endih hono aytsefem. Binadedem eskiberdelet adro new. Dr. Behanu! Ante yalebih chigir yeh new. Esate gemora tehonaleh. Kentiba betehon noro teqews neber. Degmos ya telalaki endih yemetawaredut lemindin? Telalaki meri linager yemichelewn neger menager aychilem belachehu new? Telalaki eko yehonew dengay selehone aydelem. Dr. Berhanu ante yadegehew be ber mankia eyebelah new. Sewn telalaki yemiyadergewn cheger atawkewm. Yehen deha hizb bezih amelekaketeh letastedaderew new yemetemegnew? Mejemeria newr ewek! Ye Ethiopia bahel akber! deha atezlef!

  2. Hailemariam Deslaegne is a circus tiger. Circus tigers perform or react according to the will of their circus masters. They are trained to jump up and down, roll over or play dead depending on the # of spanking they get in the ass. The Ethiopian circus tiger who has the luxury of having four baby sitters around the clock roared straight from Addis warning the opposition to stand down. Leaving his theatrical performance aside, I see a clear present danger in the message he was trying to convey.

    The post Meles woyane which was in the brink of disaster due to division amongst its rank seems to have recovered enough to go on the offensive signaling to strike a blow to opposition camp. In other words, one faction (best guess Sebhat’s) has emerged as a clear winner and feels comfortable to go on the attack against the opposition.

    This is not a threat the opposition should take lightly. Now that the Muslim Ethiopians cry for justice has been muffled and died down to the point of silence since the Addis Ababa stadium shake down, and Semayawi/Andinet protests fizzled out leaving them to sue woyane in its court as if they will find justice there–what next? where do we go from here? Can we afford feeding the beast (woyane) Ethiopia’s best children forever without a tiny victory in return? It seems to me woyane is preparing to detain leaders of Semayawi and Andinet using the false accusation of collaborating with terrorist groups. That will leave the opposition back to square one sort of a vicious circle. The opposition better put its plan B to work ASAP before its too late. If that doesn’t work, there will be one alternative left–armed struggle!!

    LONG LIVE ETHIOPIA!!!!
    FREE ALL POLITICAL PRISONERS IN ETHIOPIA!!!!

  3. Viva Ginbot-7, the only organization which carries the hopes and aspirations of the people of Ethiopia. We are all ready to join this unique and fearless crack party to redeem our country and the tyrannized population from the jaws of the extremely brutal and rapacious Tigre junta. Unless we are still shivering in fear, there is no reason why we don’t join up with Ginbot-7. We all know about the patriots who are paying the ultimate sacrifice, who assured us their endeavors on our behalf. Lets all able bodied Ethiopians join them to speed up the journey towards freedom.

  4. aye hailemariyam desaleg beselam betwered ayeshalem?anegeteh kemekoret?ene gedafim endate honew new mechersh endeh yehonut….wered bakehen…pls wered…

  5. viva genbot 7 the only organzation who can give us hope ebakachu we have only u long live ethuiopia long live genbout 7

  6. ግንቦት 7 እናንተም እንደ ወያኔ ከሻዕቢያ ጋር አብራችሁ
    ኢትዮጵያን እና ህዝቦችዎን ለማዋረድ የተሰለፋችሁ እንደሆናችሁ
    ጠንቅቀን እናዉቃችሁለን ። ነፃነታችንን ደግሞ በአገር ዉስጥ
    ሰላማዊ ትግል እንቀዳጃለን በእነ ኢሳያስ አፈወርቂ የሚደገፍ ሌላ
    የወያኔ አይነት ነፃ አዉጭ አንፈልግም ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ሞት
    ለኢትዮጵያ ጠላቶች በእራሳችን ትግል ነፃ እንወጣለን ።

  7. Dear g7, you have no politics. Your doctrine is not politics, but hatred, revenge only. Telalaki or messenger is a work. There is no bad work. Do you think Telalalki is an insult? or do you think someone who is telalaki is low iq? You are exposing only how useless you are. You have no politics, but only hate. There is no such politics anywhere. You do not even learn from wherever you live. This is the main diaspora problem. This is why diaspora politics never move one step forward. No basis, no doctrine or ideology except the ideology of narrowism and hatred, racism. How are you going to remove woyane in this way? by insulting people ? if you think telalaki is bad? then u just do not know even yourself who you are and u wanted to be my leader? no ways, you better quit politics and do not waste your time. Because HD said something you do not like, you called him Telalaki? It seems HD has to join G7 to be not Telalaki?

  8. Never seen a depraved persons like Dr. Birhanu Nega and his acquaintances , who are trying to bring peace with war by begging money and some other assistance from Eritria , a country youth generation are in sordid poverty and demising every day due to migration. It is clear that this money will definitely bring curse to Ethiopia . Dr. Birhanu once was vilifying Meles’s father for corroborating with Italians. But now Birhanu is doing the same thing even in most worst way. So let the political parties in Ethiopia who are close to the people decide and act with courage and dauntless you birhanu nega and the other do not have . If not because of you, they would have not been targeted at first place.
    One Ethiopia
    One Love
    Death for G7 and Weyane

  9. @lala,

    G7 MESSAGE IS SIMPLE AND CLEAR. freedom, democracy, justice and equality.

    It is not right that Tigre people liberation, TPLF controls the economy of Ethiopia
    It is not right that TPLF assigns 98 generals out of 101 in the military and call this justice, democracy or equality.
    It is not right that TPLF locks up journalists and politicians for demanding equal rights and freedom of speech and labelling them as terrorists,
    etc etc

    wake up and surrender to the truth

  10. @anonymous- how smart your comment is! u r killing two birds with a single pebble. u must be working for ETV or ENA. foolish. u can’t fool anyone except urself.

  11. @Sam Tir have you ever heared an etv or ena say death for woyane? I represent myself not junkies like eprdf or g7. ONE ETHIOPIA !

  12. The article does not qualify for G7 ,it seems as if written individually when one is in a state of unstability .I was expected better reply by justifying how H/M’s points are wrong & sorting out all his inability of leadership since he become PM .
    H/M is not only in able for political leadership but also devil under cover of religion .

  13. @anonymous: in principle you right but choosing the next best alternative is compulsory so that woyane can not overthrough without army struggle in addition to that peacefull strugggle can not be catagorized to down fall woyanes reigm in this land…… ( yetim fichiw duketun amchiw) ; one thing to sum up for you ,G7 is not structured as a tribal group but it is full of Ethiopianism but what about weyane ! I think you know well about that shit. Finally we don’t care about shabias support to G7 cause of don’t forget that” the enemy of my enemy is my friend” so at a moment the worst enemy of TPLF not EPRDF is EPLF(shabia) in this case the game is entirly offensive : poletics is not game but it is full of conspiracy like tplf what does in our momyland(Ethiopia)…… So our best alternative is G7 whether you like or not so every youth dwellers in Ethiopia lets stand together wiz G7 and you the Diasppora community you must have to contribute your roles to this courageos army strrugler group by making financial aid and co-operating others to in from other western countries mostly from USA, Western Europe, Far East, Middle East bla bla ….. & all over the world ……. Death to TPLF, VIVA To chikunu hizb!

Comments are closed.

Share