የማለዳ ወግ … በጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋየ ገብረ አብ ላይ የቀረበው ክስ መረጃ አንድ እውነታ – ከነቢዩ ሲራክ

 ከነቢዩ ሲራክ

የማለዳ ወግ … በጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋየ ገብረ አብ ላይ የቀረበው ክስ መረጃ አንድ እውነታ !

  ከሶስት ቀናት በፊት ቀትር ላይ አንድ የስልክ ጥሪ ደረሰኝ ። አንድ እዚህ ጅዳ የሚገኝ ወዳጀ ነበር ። ይህ ወዳጀ በስደተኛ ዜጎቻችንና በኮንትራት ሰራተኞች ላይ የከፋ ግፍ ሲፈጸም ፣ ዜጎች በራሳችን መንግስት ተወካዮች በጅዳና ሪያድ መጠለያዎች ፍዳቸውን ሲያዩ ፣ ኢትዮጵያውያን ሲያመን ህመሙ ዘልቆ ሲያመው እና የአረቡ መገናኛ ብዙሃን ስማችን አጉድፈው ክብራችን ቀንሰው መረጃ ሲያሰራጩ በስጨት ብለው ከሚደውሉልኝ ወዳጆቸ መካከል ብርቱው ወዳጀ ነው። ብርቱው ወዳጀ የኢትዮጵያ ነገር አይሆንለትም …

   ያኔ የማይረባ የባድመ ድንበር ጦርነት ተቆስቁሶ የሁለት ሃገራት አንድ ህዝቦችን ታዳጊ ወጣቶች ነፍስ ሲቀጠፍ አንዳንዶች ኢትዮጵያን ተንኳሽ እያደረጉ በሳውዲ ጋዜጦች ጨለምተኛ ፕሮፖንጋዳቸውን በመንዛት የተጠመዱ እኩዮች ብቅ ብቅ ብለው ነበር ። በዚህ ጭንቅ ሰአት በጣም ጥቂት የጅዳ ነዋሪዎች ለፕሮፓጋንዳው መልስ ይሰጡ የነበረ ሲሆን ይህ ወዳጀ ደግሞ ቀዳሚ መልስ ሰጭ እንደነበር አውቃለሁ። እናም ለዚህ መሰል ሃገር ፍቅሩ ክብር አለኝ !

ይህ ብርቱ ወዳጀ ከደወለልኝ ሰንበትበት ቢልም ዛሬ ቁም ነገር ይዞ መደወሉን አላጣሁትም !
” የት ጥፋህ ባክህ! ” ብሎ መልሴን ሳይጠብቅ ወደ ጉዳዩ ዘው ብሎ ገባ … ልጆቸን ከትምህርት ቤት ለመመለስ ነበርኩና ጎረምሶች እስኪመጡ አናት ከሚሰነጥቀው የቀትር ጸሃይ በመኪናየ ውስጥ ተከልየ ብርቱ ወዳጀን ማድመጤን ቀጥያለሁ … ወዳጀ በጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋየ ገብረ አብ ዙሪያ የተጻፈውን ጽሁፍና የቀረበበትን መረጃ ከላይ እስከታች አንብቦ እንደጨረሰ ነበርና የደወለልኝ መሰሪ ባለው የተስፋየ ኢትዮጵያን የማድማት እኩይ ስራ መበሳጨቱን አውግቶኝ ሊጨርስ ሲቃረብ …”ወረቀት ካለህ ይህን ስልክ ጻፍና አጣራው? ” ሲል አንድ ቁጥር ሰጠኝ … “ስሙ ኢብራሂም ነው! ይህ ሰው በተስፋየ የመጽሃፍ ስርጭት መረብ የተስፋየን መጽሃፍ የሚያከፋፍል ነወና አጣራው! ” ብሎ የምደርስበትን እንድነግረው ተማጽኖኝ ስልኩን ዘጋን …

       ወዲያው ስልኩን እንደዘጋሁ ወደ ተባለው አካፋፋይ ወንድም በመደወል ማጣራቴን ያዝኩ … ወዳጀ የሰጠኝ ስም ትክክል አለመሆኑን እና አማን ኢብራሂም እንደሚባል በመጀመሪያው ዙር ማጣራት ደረስኩበት! … የተስፋየን መጽሃፍ ለመግዛት ጠይቄም አፈላልጎ እንደሚያመጣልኝ ቃል ተገብቶልኛል …

      በተስፋየ ገብረአብ ዙሪያ በዳኛ ወልደ ሚካኤል መሸሻ የተጻፈው በድረ ገጾች በተለጠፈ ቅጽፈት ባየውም እንደቀደመው እሰጣ እገባ ጽሁፍ መጻፉን ገመትኩ፣ ተስፋየ ኬንያ ላይ ይጠቀምበት የነበረ በኤርትራ መንግስት የተሰጠው መታወቂያ ጉዳይም ቢሆን ለወግ ማጣፈጫ የተቀነባበረ እንዳይሆን በጥርጣሬ መመልከቴ አልቀረም ። እናም መጣጥፉን ከነመረጃውን መመልከት ግድ አለኝ …

   ከተስፋየ ጋር በጉርብትና ይኖር ነበር ከተባለው ወጣት አክቲቪስት አለማየሁ መሰለ መረጃው ተገኘ ፣ ዳኛ ወልደ ሚካኤል መሸሻ ይርዘም እንጅ በግሩም የመረጃ ግብአትን እያስዋቡ የአለማየሁን ውሃ የሚያነሳ ሰነድ አሳዩን ፣ አስነበቡን ! የሃገሬ ጉዳይ ያገባኛል ለሚል መጣጥፉ ረጅም ቢሆንም ወግ በወግ የተሰናዳ በመሆኑ አይሰለችም ። በጉጉት ፣ በአግራሞት እና በአድናቆት አነበብኩት! ከላይ ከጅዳው ብርቱ ወዳጀ የተሰጠኝም ስምም የተስፋየን መጽሃፍ ጅዳ ውስጥ የማከፋፈል ስራውን የሚያሂዱ ግለሰብ መሆናቸውን የሚጠቅሰውን ሰነድ ኮፒ ገጽ 31 ላይ ቁልጭ ብሎ ተቀምጧል! እንዴት ነው ነገሩ ? አልኩ ! ! !

ተጨማሪ ያንብቡ:  የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት እና የአንድነት መሪዎች እንደ ጋንዲ! በግርማ ሞገስ

    ወዳጀ መነሻ ሆኖኝ በግል ዳስሸ ያገኘሁት ተጨባጭ እውነታ እና በቀረበው መጣጥፍ የቀረበው ሰነድ እውነታ በውስጤ ሌላ ስሜት መፍጠር ያዘ ፣ ቀድሞውኑ ስል ተስፋየ ገብረአብ ተጽፎ ሳይ “በተስፋየም በተቃዋሚዎቹም የቀጠለው ስም የማጠልሸት እስጣ ገባ አለያም የተስፋየ ገብረአብ ቀጣይ መጽሃፉን ለማሻሻጥ የተደረገ ረቂቅ የገበያ ፍለጋ ዘመቻ ነው !” የሚለውን ጥርጣሬ ነበረኝ! ከሰአታት በፊት ያነጋገርኩት አከፋፋይ አና ከመጣጥፉ ጋር የቀረበው ሰነድ ግን አጉል ጥርጣሬየን ብንን አድርጎ አጠፋብኝ … !

    በአለማየሁ በኩል ከጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋየ ገብረአብ ጉያ ተገኙ ከተባሉትን ሰነዶች መካከል ማረጋገጥ የቻልኩት ሰነድ ብዙ አርቆ አሳሰበኝ … በዚህ ዙሪያ ከራሴ ጋር ስሞግት ግራ የተጋባችው ባለቤቴ ቁርጠት የሚያጣድፋትን እርጥብ ልጃችን ማህሌትን ከደረቷ ላይ ለጥፋ ከምታባብልበት ቀረብ አለችና ” አብረን ማንበብ ጀመረን ብቻህን ጨረስከው አይደል? ” ብላ ስትጠይቀኝ የሆነውን ሁሉ አጫወትኳት … “ምን ሆነሃል እኔም ደስ አላለኝም ፣ ይህ ነገር እውነት ሳይሆን አይቀርም ! የቡርቃ ዝምታን አንብበው እስኪ ?” በማለት ከመጽሃፍ መደርደሪያው የተወሸቀውን የተስፋየ ገብረአብ የቡርቃ ዝምታ መጽሃፍ የት አንደገዛችው እና በጅዳና አካባቢው በሰፊው የተከፋፈለበት መንገድ አወጋችኝ! ኢትዮጵያን ትወዳለችና የመረጃውን እውነታ የቀረበው ሰነድ ተጨባጭነት አጉልቶ እንዳሳሰባት አጫዎተችኝ … ወደዚህ አለም ከመጣች ገና አስራ አምስት ቀን የደፈነቸው ልጃችን ማህሌት ይህን ሶስት ቀን ንጭንጭ ብላ ታለቅሳለች! ከትናነት በስቲያ ሃኪሟ ዘንድ ሄጀ “አዲስ ለተወለዱ ህጻናት ይህ መሰል ቁርጠት ከወተት ጋር የሚመጣ የተለመደ ነው!” ብሎ ምክር ቢጤ ስለሰጠኝ ብዙ አላሳሰበኝም አልልም ! ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአለማየሁ ተገኝቶ በዳኛ ወልደ ሚካኤል የቀረበው መረጃና ያጋጠመኝ ግጥምጥም ጉዳይ ሳይሆን ቢቀር አሳስቦኛል! እናም ብርቱ ወዳጀን ያመመው ኢትዮጵያዊ ህመም አመመኝ ! ግን ለምን ተስፋየ ? አልኩ … ትንሿ እውነተኛ የመረጃ ፍንጭ ጠልቃ ብታደማኝ…

      ብዙም ሳልቆይ አንዳች ነገር ሰውነቴን ወረረው ! በግላጭ አግኝቸው በተጨባጭ ሳልይዘው ያለፍኩት መረጃ ትዝ አለኝና ከአልጋየ ተስፈንጥሬ በመነሳት ወደ ተስፋየ ገብረአብ መጽሃፍ አከፋፋይ ስልክ ደወልኩ … ስልኩ ተነሳ !

“ጤና ይስጥልኝ ? ”
“ጤና ይስጥልኝ ! ”
“እንደምን አደሩ !?” ቀጠልኩ
“አልሃምዲላህ ! ” መለሰ

   ከዚህ ቀደም ያገኘሁት ወንድም ነው። የማወራው ከምፈልገው ሰው ጋር መሆኑን ለማረጋገጥ መስመር ውስጥ ያገኘሁትን ወንድም “አቶ አማን  ነወት? “በማለት ጠየቅኩት ፣ አማን መሆኑን ካረጋገጠልኝ በኋላ ማንነቴን ሲጠየቀኝ ።… ከሁለት ቀን በፊት  የተስፋየ ገብረአብን መጽሃፍ አፈልጌ ደውየ እንደነበር ስገልጽለት አስታወሰኝ …በመቀጠልም . ..
” አዎ መጽሃፍ የሚሸጠውን ሰውየውን ፈልጌው ነበር አላገኘሁቱም ፣ የትኛውን መጽሃፍ ነው የምትፈልገው ? የ . … የፈልግከው ? “ሲል ጠየቀኝ ፣
አዲሱ መጽሃፍ ካለ መልካም ከሌለ ያለውን ባገኝ ቅር እንደማይልሰኝ ገለጽኩለት
” ያለው አይመስለኝም ድሮ ይህ ሰውየ ያመጣው የነበረው የጋዜጠኛው ማስታወሻ የሚል ነው ። ” ሲለኝ አስከተልኩና “እሱስ አለህ ? ” ስል ጠየቅኩት…
“እሱ ካለ እጠይቀዋለሁ ! ሰውየውን አላገኘሁትም ይሸጠው የነበረው . ..ስንት ነው የፈለግከው ? ” በማለት7በድጋሜ ሲጠይቀኝ መግዛት የምፈልገውን መጽሃፍ ብዛት ደርዘን አድርሸ መለስኩለት አቶ አማን መለሰ ” አገኘኋለሁ እና ቢጠፋ ቢጠፋ እሁድ አገኘዋለሁ ! እነግርሃለሁ ! ” አለኝ
አቶ አማንን በማስከተል የአዲሱን መጽሃፍ መምጣት መረጃ አና ስለ አከፋፋዩ ጠየቅኩት
” I don’t know ከእርሱ አዲስ ስለመኖሩ አላውቅም ፣ የበፊቱን ከእርሱ አግኝቸው ነበር ከዚህ በፊት . … አንተ እንግዳ ነህ ለጅዳ ?” በማለት አከታትሎ ጠያቂውን ያጠየቀ ጥያቄ ከወደ አቶ አማን ቀረበልኝ ፣  ለሃገሩ ባዳ ነኝ የሚል ነጭ ውሸት ዋሸሁት…
“የት ነው ያለህው ?”ከሚለው ጥያቄ ጀምሮ ” ማነው ይህን ስልክ የሰጠህ ? ” የሚለው ጥያቄ ከወደ አቶ አማን ተከታትሎ ቢቀርብልኝም ለስራ ጉዳይ ጅዳ ብመጣም የምኖረው ራቅ ወዳለች አንዲት የሳውዲ የጠረፍ ከተማ መሆኑን በማስረዳት እዚያ ላሉ ኢትዮጵያውያን መጽሃፉን ለማከፋፈል እንደምፈልግ ገለጽኩለት ፣በማከልም የእርሱን አድራሻ ያገኘሁት አውሮፓ ከሚኖር ወዳጀ መሆኑን አስረዳሁት ። ከዚያም አቶ አማን ጥያቄዎቹን በመግታት መጽሃፉን ከአከፋፋይ ካለው ሊጥይቅልኝ ቃል ገብቶልኝ ስልኩን ዘግተን ተለያየን …

ተጨማሪ ያንብቡ:  ስለ ኮሎኔል ታደሰ ጥቂት ልበል፡ ከፍል1 በይታያል የሩቅሰው

      አዎ ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋየ ገብረ አብ ተወልዶ ያደገባትን ፣ ለወግ ማዕረግ አብቅታ ያስተማረችውን ሃገር የኢትዮጵያን ህዝብ የሚጎዳ ስራ መስራቱን ለመቀበል ከባጀና ከከረመ አመታት ተቆጥረዋል። ተስፋየ እንደ ደራሲና ጋዜጠኛም ባይሆን እንደ ሰው ተፈጥሯዊ  ሃሳብ የመግለጽ የማይገሰስ መብቱ የተጠበቀ መሆኑን አምናለሁ። ዳሩ ግን ተስፋየ እንደተባለው እስከ ጥግ በሚጠቀመው መብቱ እንደ ዘርን ከዘር የሚያጋጭ መረጃን ማስተላለፉን አልቀበለውም። ተስፋየ ገብረአብ የኢህአዴግ ባለስልጣን እያለ ጀምሮ የጻፈውን ወደ ኋላ ዘወር ብሎ ላስተዋለው ያሳዝናል። ተስፋየ ገብረ አብ በኢህአዴግ መንግስት ታማኝ ሆኖ እና በወሳኝ የሃገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር ከፍተኛ ስልጣን ተቀምጦ የሚጎዳንን ፣ የሚለያየንን በቡርቃ ዝምታን መጽሃፉ ጀባ ብሎናል ። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ብዙዎችን በልዩነት በደጋፊና ተቃዋሞ ዙሪያ ያዘባራው ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋየ ገብረአብ በቡርቃ ዝምታ የተሰቀዘው የብዙዎች ልብ በቀጣይ ስራዎቹ ለማባበል አልገደደውም ።

      እርግጥ ነው ተስፋየ በልዩ የአጻጻፍ ክህሎቱና አልፎ አልፎ በሚያነሳቸው “ጮማ ” የፓለቲካ ወጎቹ እና በቀጣይ ባቀረባቸው ወጥ ልብ አንጠልጣይ የድርሰት ስራዎቹ  የተቃወሙ እና የሸሹት መልሶ ምርኮኛ ማድረግን የተካነ የጥበብ ሰው መሆኑን ላፍታ እንኳ መካድ አይቻልም። ዛሬ ሌላ ቀን ቢሆንም የተስፋየ የጥበብ ትጋት እና እየጣለ የሚያነሳን ያልረጋው የሃገራችን ፖለቲካ ውጥንቅጥ ውስብስብ ባህሪ ጋርዶብን የተስፋየ ገብረ አብ ድጋፍ ሰጭ የነበርን የተጎጅዋ ሃገር ዜጎች ቁጥር ቀላል አልነበረም !

    እርግጥ ነው ተስፋየ ገብረአብ ከተባለው ረቂቅ ሴራ በተጓዳኝ ጠቃሚ ጠቃሚ የሚባሉ መረጃዎችን ይፋ በማድረጉ ረገድ የሰራው መልካም ስራ የሚዘነጋ አይደለም። በስልጣን በቆየባት ሃገር ለተሰራው ሁሉ እሱም ከተጠያቂነት ባያመልጥም በስልጣን ዘመኑ በሃገሬ ምድር በአደባባይ እና በስውር ተሰርቶ ያየውን ባያጠግበንም ብዙ አካፍሎናል ። እማኝነቱን በሰጠባቸው የአንድ ቡድን የበላይነት የነገሰበት ሃገር ፣ የመብት ገፈፋና የሰብአዊ መብት ጥሰት ዙሪያ ያቀበልን መረጃዎች የስነጽሁፍ ጥበቡን ጨምሮ ብዙ ትምህርት ማግኘታችን የሚካድና የሚዘነጋ አይደለም ።በተስፋየ ዙሪያ ዛሬ ሌላ ቀን ያባተ ይመስላል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ሞሳድ የበላው ነጭ ድመት - ሱሌማን አብደላ

     ዛሬ ሌላ ቀን ሆነና በወጣቱ ሰብአዊ መብት ተቆርቋሪ በአለማየሁ ትጋት በመረጃ ተደግፎ የተጋለጠው የተስፋየ የከራረመ ሴራ በዳኛ ወልደ ሚካኤል መሸሻ ጥናታዊ ዘገባ በዝርዝር ይፋ ሆኗል። ይህንን መረጃ እያየሁም በተስፋየ ክህደት ዙሪያ እየተጠራጠርኩ ለማንበቤ ከተስፋየ አንደበት የሰማኋቸው የጸና ኢትዮጵያዊነት የአቋም መግለጫዎቹ እንደሆኑ ውስጤ አሁንም ያምናል ! አንዲህ ሆኖም የቀድሞ መከላከያ ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ስየ አብርሃን ጨምሮ በአካባቢያቸው ያሉትን ሃገር ወዳድ ተቃዋሚዎች እና አዛውንቱ የቀድሞው የሃገሪቱ ፕሬዚድንት ዶ/ዶር ነጋሶ ጊዳዳ ሳይቀሩ በተስፋየ ዘራፍ ብዕር ተወርፈዋል። ይህን ዘለፋውን ደጋግሜ ተምልክቸ ልቤ አልቀበል እያለው ብቸገርም ከተራ ጥላቻ የዘለለ የለመድነው የመቦጫጨቅ ፖለቲካ ነው በማለት ችላ እለው ነበር ። ዛሬ ግን ያ ሁሉ በትር ያዘነበባቸውን ወገኖች የማጥቃት አለማ አውጥቸ አውርጀ እመዝነው ዘንድ ግድ ይለኛል! ዛሬ የቀረበልን ጭብጥ ሰነድ ቢያንስ ተስፋየን እና ይጠላቸው የነበሩትን ሁሉ ሳይሆን ይወዳቸው የነበሩትንም ፖለቲከኞቻችን መላለሰሸ እገመግማቸው ዘንድ ተገድጃለሁ! ዛሬ ቢያንስ በግል በተስፋየ እጅ የተጻፉ ሰነዶች ጋር ለቀረበውን ቅንጣቢ መረጃ ማረጋገጫ ካጋገኘሁ ወዲህ ቢያንስ በተስፋየ ላይ ስለሚሰነዘረው ውንጀላ የጥርጣሬ ግርዶሹ ተገፎልኛል !

   የማለዳ ወጌን ለመደምደም ዳኛ ወልደ ሚካኤል መሸሻ በቀረበው 44 ገጽ ጥናታዊ ጽሁፍ በገጽ 31 ላይ እዚህ ጅዳ በአከፋፋይት የተጠቀሱትን ወንድም ካነጋገርኩ በኋላ በሰነዱ ጎን የሰፈረው መግለጫ አስታወስኩ … አንዲህ ይላል “…ከዚህ በላይ በሻጭነት የተመለከቱትን ምናልባትም በየአገራቱ ከምትገኙ ኢትዮጵያዊያን ቢያንስ አንዳችሁ አንዱን ታውቁ ይሆናል ብዬ እገምታለሁ። እናም፣ ከእንግዲህ ልብ ልንል ይገባል። ባለማወቃችን፣ ባለማስተዋላችን ተታልለናል። ካወቅን በኋላ ደግሞ እንነቃለን። በቃህ! ወደዚያ! እንላለን። ኢትዮጵያዊነት ኩራት መሆኑን እንነግራቸዋለን ማለት ነው!” ይላል!እርግጥ ነው ከተለቀቀው መረጃ ውስጥ የተጠቀሰውን አንድ መረጃ መረጋገጥ በመቻሌ እኔም በመልካም ጥበብ ተደቁሶ የተቀመመውን መርዝ ላለመጋት “በቃ!” ብያለሁ ! አዎ ! አትዮጵያዊነት ከጥበብ ሁሉ የላቀ ጥበብና ኩራት መሆኑን እነግራቸዋለሁ !

በቃ ይህን ነው የምለው . . . ኢትዮጵያ ለዘልአለም ትኑር !

 ነቢዩ ሲራክ

25 Comments

  1. Zba zinke new gizekn bekentu atefak everybody love Yeburka zimta and Tesfaye Gebreab who ever he is…..

    • Are you taking about yourself? I did not see the writer insulting anyone but you are and that shows a person with IQ 0.

  2. Hope most Ethiopians understand how Ethiopian/Eritrean politics is more complicated than we would like to imagine. What we wish to have and what we have on the ground are not the same.

    There r people thru out the world thru out history with double personality who don’t give value to their national identity and live dangerous life of spying hurting their own nation till the day comes they are exposed. Mr Tesfaye not surprisingly may be one of them; obviously he has Eritrean blood not Ethiopian.

    May be he was part of the “100 year home work” assignment given to innocent Ethiopians by….

    The good thing is this further opens eyes to imagine what might still be happening in the name of Ethiopia. How many cover agents are in woyane/TPLF government who sabotage the country but still want to be trusted by innocent citizen.

    For that matter, it was said in the pat by some that many innocent looking people from Tigrai even in the Derg hierarchy /military have played double face spying for TPLF/Woyane (perhaps one reason why paranoid Derg was killing civilians en-mass??)- some used to say the otherwise the feared military of the Derg system wouldn’t disintegrate that easy.

    The problem is it turns out Ethiopians probably have not established culture of trust among themselves.

    It looks for some their ethnicity outweighs their nationality. Unfortunately for some they want the larger Ethiopia as milk cow for resource than accepting, respecting and considering all what makes Ethiopia as their country.

    In conclusion, the current revelation is a lesson to those who are wasting their life striving to build a better Ethiopia where all Ethiopians will be equal irrespective of their color, stature, religion, Ethnic category. They should walk fine line being watchful in finding out who is who, who to trust who not to trust …

    So far it turns out, the generation of woyane/TPLF whether they defect from their parent party and say they came clean still ??hate to the greater democratic and prosperous Ethiopia most dream to build in the future.

  3. I have read the original paper by W/M Meshesha and it was an excellent pieces of work based on solid evidence. For their part I personally thank both the writer Mr Meshesha and the person who provide the solid and undisputed evidence. However, too much attention was given to the so called ato Siye Abraha in their work and in my view it overshadowed the quality of their finding because at one point I was fade up of the repetition and unnecessary infasis given to Siya Abraha. I don’t know the motive of woldemikial meshesha in giving such attention to Siye. Appart from that they really exposed that stupid chameleon. No more cheating Ethiopians

  4. You don’t need to write 41 page to prove the evil of Tesfaye. He is filled with hate for Ethiopia.

  5. Dump Mashash (why you call him judge?) brought this letter of at this time as ‘secret” because Tesfaye Gebreab is in Irrecha celebration in Holland this week.”The timing”
    Ye neftenya kids hate has no boundary. You hate Eritrea and Oromo but love Ethiopia (oh sorry neftenya code?
    Tefsaye told you that he is Ethiopia, rtrea and Ye Bishoftu boy. A person could have multiple identity. Why is this big article for this
    We know even when you fart.

  6. I have read the paper by W/M Meshesha and I could not get any substance from the whole 44 pages. It is illegal and unjust to steal once personal notes and copy and distribute them. Ok you have stolen it and what surprised me is that nothing you presented can not prove that Tesfaye is the Enemy of Ethiopia. Tesfaye wrote the truth about what he knows and what he has seen. What is being revealed in this trash paper is what we call ”Oromo Phobia”. All this effort is as the result of the fact that Tesfaye wrote truth about the Oromos and the unjust political system they are subjected to.

    Truth shall prevail

  7. Please, can you say it again? Ethiopiayawinet kurat new kalkew lela minim alsemahukim. Minew jal?

  8. This idiot fooled us. I read yeburka zimita yegazetagnaw and derasiw mastawesha. It never crossed my mind that he was planting his evil intention inside our nation. well yeburkaw zimata smells a little bit of conspiracy. before ten days I saw his interview with one addis based magazine and read it through. then I commented about him starting counter attack ( on Dr Negaso Gidada and Gebremedhin araya.) on those who said something about him and now I found out that he was afraid of them couse they know him well this looser. nway it Gives us a lesson to look at things carefully.

  9. One country spying the other is given. That isn’t the problem, Tesfaye’s work in books form of creating a serious problems between Amhars and Oromos is unforgivable. Thank you both Mr. Meshesha & Alemayehu. Ethiopians will live together and ever
    no one knows the fabric made of to keep us together.(except our creator)

  10. bikila አንተ ራስህ ተስፋዪ ገብረአብ ነህ አደል ቆርቆሮ ራስ ሻቢያ

  11. Hey Guys, there is simple solution for this. Do not buy Gebreab’s book. It is bull crap. Let some hard core OLF who are willing to be deceived buy it. Do not waste your time reading it. We have some work to do, like get rid of Woyanne. That is our priority. Some Eritreans are losers. Why, long before disintegration, they have a lot of businesses in Addis such as Hotels, Garages, Restaurants, Albergos, Pharmacies, etc. They helped Shabiya and destroyed everything, including their businesses. Tesfaye is one of those people who wants to bring chaos in east Africa. So, do not pay attention to him.

  12. @ Alex and Hagere

    When G7 gets fund from Erteria u never claimed that was evil but when Tesfaye wrote a book about oromo which is fact u guys started saying he Erterian,is this fair?
    we are the fab of Obbo Tesfaye , whether he is Ethiopian or Erterian i dont mind coz we he contrbuted to Oromo people is enough for us.
    Your comments shows not the hatred you have for Tesfay but the hatred for Oromo.
    so what ever you say , wish about oromo and those people who contributed something to oromo people,OROMUMMAA IS INREVOCABLE.
    WE NEVE GO BACK AS UR ANSESTERS KEEP US BACK.
    The time of i know for you has gone long time ago never to come back.
    OBBO TESFAYE IS HERO.

  13. Tesfaye is no different from any other Eritrean who hate Ethiopians and Ethiopia while Ethiopia gave them everything , Eritreans are worse than devil who have 9 different faces like TESFAYE who will not rest till they see the destruction of Ethiopia. Ethiopians are naive people who believe TESFAYE, TESFAYE has been especifically attacking good Ethiopians like NEGASO GIDADA and SEYE ABRAHA those people who were severely criticized by TESFAYE should be good for Ethiopia that is why he hates them and make fun of them in his book so we should go back and see who tesfaye hates and who he loves. Tesfaye I hope GOD will Judge you and evil Eritreans actually Eritreans are laboring the fruits of their hate towards Ethiopia we are seeing them die like animals in every corner of the world

  14. Everybody should read judge W/michael Meshesha’s article. Tesfaye is unbelievably decieving us. We should read his next book but only one copy for all of us. I recommend innocent Oromo brothers to read the article of judge W/MIchael and see the evidence there how arogant and Oromo-Amhara blood thursty this shabia spy is.

    I thank ‘tintagu’ Alemayehu for his patriotic work. Adios Tesfaye..enjoy your life in ‘father land’ Eriteria.

  15. I read all evil by TESFAYE. For all that evil he planted in Ethiopia, he was driven out of the country. And for sure he will die of his evil intention. Count my words!

  16. We are on standby to get the book, scan and pdf it, and distribute it to the few Jawars who want to spend their time on G/Ab’s vomit. By any means, G/Ab will get no penny from us, the majority of Ethiopians. Our neighbor Shemsu, and other shop owners are running out of paper for their sugar and salt sales. G/Ab can write and publish; the paper (hard copy) will end up at Shemsu Suk, while the diehard Oromos will ´be served with the soft copy (plus a certain amount of Mitmita). .

  17. pleas ///////////ERITRIANS LIVE AS alon its our problems we dont neds you gambelar comment time is over since tesfaye when he strat 1st < jornalist note no bady belivs him lot of ethiopian web sait many ethiopians comment or post about him so pls ..pls..pls.. stay out said you have owen problem solve that one can i asek do you thinks you put hugly names web sait names no body noes about ……… so PLS PLS

  18. ግሩም መነቃቃት ነው:: ስለዚህ ቆሻሻ ጥራጊ ዱሮዉንም ተናግረን ነበር ሰሚ ጠፋ እንጂ:: ዛሬ የዳኛ ወ /ሚን መጣጥፍ አንብቤ ሳበቃ አንዲት አጠር ያለች ፅሁፍ አዘጋጅቼ ነበር; ግን ኢንተርኔት ከተቁዋረጠ 5 ቀን እንደሆነው ሰማሁ:: እንደተለቀቀ እልከዋለሁና ጠብቁኝ:: ይሄን የውሻ ልጅ …

  19. summary of W/M Meshesha’s argument:

    Shabiya’s agent Tesfaye is our enemy
    the enemy of our enemy(shabiya) is our friend
    There fore:. Tesfaye is our friend. nonsence.

  20. tultula, you should be ashamed to say you would kill tesfaye, instead if you have the gut why dont kill at least one weyane who is killing and torturing our people now…sinte maferia hizib ale bakachihu….ethiopians are so stupid who cant fight the biggest enemey weyane while wasting our time in one person…shame on us

  21. @GUDU, @dagmawi and @ other amhara advocates who replied above….

    all of u suggested to read judge w/michael meshesha’s analysis. i read it. but before i get to that answer this question. Do you respect oromos? (dont kid urself, be honest). what are your ideologies for the oromo people?
    one couldnt know how the oromo people felt the suffer, opression, discrimination, hatred and racisim while growing up in this so called Ethiopian Community unless u are an oromo and been through that.
    to get back to the point; u dont have to go to so much trouble to proof what tesfaye wrote is true or not (detailed analysis of his life and picking up lines of his books and judging the out of context…) if wanted to know the truth just ask one oromo and ask him that this society never made him be ashamed of his culture and identity and all what tesfaye said. its is the message that counts not the messanger! and i know every single one of u who lived in ethiopia knew these (what tesfaye wrote) were true from the beginning. and if u choose to be oblivious to the facts thats ur choice

    and for those of u advocating this one ethiopia (ethiopian love) crap….ethiopia will be one country when every nationally and nation is respected and well known. with one nation higher and the other lower there is no country rather contemporary colonization.

    and at last. to the amara’s. no one judges u on what ur ancestor so horrifyingly, inhumanly, animanily and undescribably did to the oromo and other nations. but we will get past that when u accept what ur ancesstors did and fraud up on it and hate it as it was inhuman. then you will be respected and not judged (and not be called neftegna) for what happened in the past. and that is what u are very angry about tesfaye’s ye burqa zimita book. he only stated what happend at that time and to the oromo people not acknowledging what happened means depriving it from its identity.

    at last think of theses questions
    What is habesha to you?
    Do u consider a black ethiopian say gambela person habesha? (be honest)
    Do u think of some one from somali region as a habesha?
    Dont you think the so called Ethiopia is more than those what you call habesha? including people u have never seen and cultures not similar to urs?
    so please just because u consider ur self as habesha, amara, or tigre dont thnk u represent ethiopia. ethiopoa is much more than habesha tribes.

    JUST BECAUSE TESFAYE SHOWED THE CRUELTY OF AMHARA AND TIGRE PEOPLE TOWARDS OROMO. DOESNT MEAN HE WANTS ETHIOPIA TO FAIL AS A COUNTRY. AND THE CRUELITY STILL EXISTS CAUSE IT IS WHAT OROMOS FEEL DAY TO DAY. I KNOW I DO

Comments are closed.

Share