ፕሬዝዳንት ነጋሶ መሪ ሆኑ – ከአበበ ገላው (ጋዜጠኛ)

ጋዜጠኛና አክቲቪስት አበበ ገላው ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ትናንት ለዘ-ሐበሻ ከሰጡት አጭር ቃለ ምልልስ በኋላ በፌስ ቡክ ገጹ ያሰፈራት አጭር ግን ብዙ የምትናገር መልዕክት፦
መሪ ማለት ሌሎችን አጋፍጦ ዘወር የሚል ሳይሆን ከፊት ቀድሞ የመጣውን ሁሉ የሚጋፈጥ ማለት ነው። በትናትናው እለት የአንድነት አባላት በሰላማዊ መንገድ ስራቸውን በመስራታቸው ሲታሰሩ አብሬ እታሰራለሁ በማለት መደ ቤት ሳይሆን ወደ እስር ቤት ገብተዋል። በዚህም የታሰሩትን አስፈትተው መሪ መሆናቸውን አስመስክረዋል። ከዚህ በሁዋላ መታሰር የሚገባን እኛ እንጂ አባላቶቻችን አይደሉም ማለታቸው ቁርጠኝነታቸውን ያሳያል። ነጋሶ ወያኔን በቃኝ ብለው ህዝቡን በመቀላቀል ክብራቸውን አስመልሰዋል።
በሌላ በኩል አንድነቶችና ሰማያዊዎች ከምርጫ ፱፯ በሁዋላ የነጻነት ጥሪ እንዲያስተጋባ ማድረጋቸው ታላቅ እመርታ ነው። ፍርሃት ሲሸነፍ የአንባገነኖች የምጽአት ቀን ይቃረባል። ሁለቱ ፓርቲዎች እየተደጋገፉ መታገል ይጠበቅባቸዋል። የአንድነቶች ቅስቀሳ ምርጥ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በዳይ እንደ ተበዳይ   !
Share