የምስራች ለኢህአዴግ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤትነት ምልክቶች በአንድ ካድሬ ተገኘ

ከዳዊት ሰለሞን (ጋዜጠኛ)

ኢህአዴግ መለስን በተፈጥሮ ሞት እንደተነጠቀ የድርጅቱ አመራሮች የሙሉ ጊዜ አገልግሎቱን ለለቅሶው ባበረከተው ቴሌቪዥን በመቅረብ ሟቹ መለስ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት እንደነበሩ ይናገሩ ነበር፡፡የኢህአዴግን አቅጣጫ የሚቀይሱ፣የትግራይን ስትራቴጂክ እቅድ የሚነድፉ፣የድርጅቱን የንድፈ ሃሳብ መጽሄት በዋና አዘጋጅነት የሚያገለግሉ፣የአገሪቱን የጦር ሃይል በ1997 ጠቅልለው ወደ ራሳቸው ዕዝ ያስገቡ፣ዶክተሩን፣መምህሩን፣ተማሪውን፣አርቲስቱን፣ወጣቱን፣በንግራቸው የሚያማልሉ፣የአፍሪካ አዲስ ተስፋ ተሰኝተው በእነ ቶኒ ብሌር የተመረጡ፣የአገር ውስጡን ተቃዋሚ ጣት እቆርጣለሁ በማለት የሚያስፈራሩ፣እነዚህና ሌሎች ስንክሳሮች ተመዝዘው መለስ‹‹የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ናቸው ››ተባሉ፡፡ከመለስ በኋላ ይህን ጭንቅላት ስለ ማግኘቱ የተነገረለት ወይም አለኝ ያለ እስከ ዛሬ ማለዳ አላጋጠመኝም ነበር፡፡
በመለስ እግር የገቡት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የመለስ ጫማ እንዳልበቃቸው በመታመኑ በክላስተሮች የተከፋፈሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተመደቡላቸው ወይም ተመደቡባቸው፡፡(ሂደቱን አንዳንዶች በጠቅላይ ሚኒስትሮች ብዛት አገራችን እመርታ አስመዘገበች በማለት መቀለዳቸውን አስታውሳለሁ)ነገር ግን ለእኔ ሹመቱ የእመርታ ጉዳይ ሳይሆን ያን ምጡቅ ጭንቅላት በአንድ ሰው መተካት አለመቻሉን ኢህአዴግ ማመኗን የሚያሳብቅ ነው፡፡
(የፎቶ ምንጭ አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ)
ኢህአዴግ አንዱን መለስ በብዙ ለመተካት እየወሰደ ከሚገኘው እርምጃ በተቃርኖ ዳንኤል ብርሃነ የሚባል ግለሰብ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ነኝ››በማለት ራሱን አስተዋውቋል፡፡ይህ ምጡቅ ጭንቅላት በመፈለግ ከመለስ ሞት በኋላ በቀን ብርሃን ባትሪ እያበራ ሲፈልግ ለከረመው ኢህአዴግ ትልቅ የምስራች ነው፡፡
ወዳጄ እርስዎ ‹‹ምጡቅ ጭንቅላት››የሚል ቃል ሲያደምጡ ወደ አይነ ህሊናዎ የሚመጡት እነ አልበርት አነስታይን፣ሊዮ ቶሎስቶይ፣አጼ ምኒልክ፣ማዘር ቴሬዛ፣ኔልሰን ማንዴላና ሌሎች ይሆናሉ ፡፡በኢህአዴግ ማውጫ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤትነት ሁሉን በጠላትነት አይን ማየት፣ዘረኝነት፣ፍረጃ፣አማራጭ የሚባል ሃሳብ ጠረጴዛው ላይ እንዳይቀርብ የተለየ ሃሳብ አመንጪን መምታት ነው፡፡በዚህ ረገድ የፌስ ቡኩ ዳንኤል ብርሃነ ‹‹የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ስለ መሆኑ መከራከር ጉንጭን ማልፋት ነው፡፡የህግ ባለ ሞያና የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ነኝ የሚለን ግለሰቡ በቅርቡ ፖስት ያደረጋቸውን ወይም አስተያየት የሰጠባቸውን አንዳንድ ጹሁፎች በመመልከት ምጡቅ ጭንቅላት እኛ በምናውቀውና እነርሱ በሚሉት መካከል የሰማይና የምድር ያህል ልዮነት እንዳለው እንገነዘባለን፡፡
Wossi Zebdewos:- ”There was a defection news/ Rumor at the first place??”

ተጨማሪ ያንብቡ:  የታመመው መንግስት (ጥሩነህ)

Daniel Berhane:- ”Yes, there is such a news from the enemies of Tigrai.”
ዘብዴዎስ የተሰኙ የፌስ ቡክ ተጠቃሚ ለዳንኤል እነ አርከበን በተመለከተ የኩብለላ የጭምጭምታ ዜና ከመነሻው ስለ መኖሩ ይጠይቁታል፡፡ዳኒ በመልሱ ‹‹አዎን ከትግራይ ጠላቶች እንዲህ አይነት ወሬ ነበር››ብሎ ቁጭ፡፡በቃ በእርሱ ምጡቅ ጭንቅላት ውስጥ እነ አርከበ ኮበለሉ ማለት የትግራይ ጠላት መሆን ነው፡፡ የባለስልጣኑን ኩብለላ ከትግራይ ጠላትነት ጋር ሊያቆራኝ የሚችል የዳንኤል ምጡቅ ጭንቅላት ካልሆነ በቀር እንዲህ አይነት ጭንቅላት ማግኘት ያስቸግራል፡፡እንቀጥል
Daniel Berhane:- #Ethiopia: History repeats itself. Now Arena-Tigray is the enemy with-in.
አረና በቀድሞ የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች የተመሰረተ ፓርቲ ነው፡፡ዳንኤል ይህንን ፓርቲ እንዴት እንደሚመለከተው ሲጠቅስ በውስጥ ያለ ጠላት ብሎታል፡፡በቃ ለዚህ ምጡቅ ጭንቅላት ህወሃትን መቃወም ጠላትነት ነው፡፡አረና በትግራይ ምድር ሆኖ ህወሃትን መቃወሙን ደግሞ በውስጥ ያለ ጠላት በማለት እንዲፈርጅ አድርጎታል፡፡ምን ይደረግ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ነዋ፡፡አሁንም ከዳንኤል ይቅርታ ከምጡቅ ጭንቅላት ጋር ነን፡፡
Daniel Berhane:- በትግራዮች እና በኢሕአዴግ አባላት ላይ ማህበራዊ መገለልን ያወጃቹሁ ሰዎች(ጨዋው የኢትዮጲያ ሕዝብ አሳፈራችሁ እንጂ)፣ በተግባርም የትግራዮች ቤት ሲቃጠል እና ‹‹የሚቃጠል›› ተብሎ ሲፃፍበት ግድ ያልሰጣችሁ ሰዎች፣ የበድሩ አደምን ዘረኛ መፈክር ከማውገዝ ይልቅ የቃላት ጨዋታ የመረጣችሁ ሰዎች፣ በእናንተ አመራርና ቅስቀሳ ስለተደበደቡና ስለተገደሉ ትግራዮች ከመቆጨት ይልቅ መከራከር የመረጣችሁ ሰዎች፣ እንኳን በፈቃዳችሁ መራብ ቀርቶ ምግብ አጥታችሁ ብትራቡ ግድ የሚሰጠው የሚኖር ይመስላችላኋል
ደረጄ ሀብተወልድ የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን የርሃብ አድማ በማስመልከት የዳንኤል ወንድሞች የሰጡት ምላሽ አበሳጭቶት እነርሱ እኮ ለቅንጅት አመራሮች የርሃብ አድማ የሰጡት መልስ ተመሳሳይ ነበር እናም ርዕዮት የርሃብ አድማ በመጀመሯ ያዝናሉ ብለን መጠበቅ አይገባም፡፡ይላል ዳኒ ለደረጀ መልስ በመጻፍ‹‹እንኳን በፈቃዳችሁ መራብ ቀርቶ ምግብ አጥታችሁ ብትራቡ ግድ የሚሰጠው የሚኖር ይመስላችላኋል››ምጡቅነቱን አሳየን፡፡አዎን በዳንኤል ዙሪያ ግድ የሚለው ላይኖር ይችላል፡፡እናንተ ግድ እንዲላችሁ ነፍስ መበላለጥ አለበት፡፡ደግሞስ ይህን ዘረኛ ከፋፋይ የፖለቲካ እሳት እንዲዛመት ያደረጋችሁት እናንተው መሆናችሁን መዘንጋት አይኖርብህም፡፡በጣም ግራ ያጋባኝ ነገር ድሬዳዋ ያደገ ሰው በድሬ የተማረ ከየት ነው ይህንን ዘረኛ አመለካከት የያዘው?
Daniel Berhane:- It is boring to see such a long collection of stupid comments. If you don’t like the info, go hang yourselves.
ዳንኤል ለለጠፈው ጽሁፍ በዛ ያሉ ሰዎች ተቃራኒ አስተያየት መሰንዘር በመጀመራቸው ባለ ምጡቅ ጭንቅላቱ ‹‹እኔ የሰጠሁት መረጃ ያልተመቸው ራሱን ማጥፋት ይችላል ብሎ አረፈው፡፡ጠላትነት፣ራስን ማጥፋት፣ማንም ስለ እናንተ ግድ የለውም፣የትግራይ ጠላቶች ››የሚሉ ቃላትን በዳኒ እያንዳንዱ ጽሁፍ ውስጥ ተሰግስገው ያገኛሉ፡፡እነዚህን ቃላትም መለስ በህይወት ዘመናቸው የተካኑባቸው እንደነበሩ ካስታወሱ ቃላቶቹ ምጡቅ በመሆን የሚገኙ ወይም የምጡቅነት መለኪያ መሆናቸውን ይረዳሉ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግስት አንኳር ስህተቶች - አንድነት ይልቃል

Daniel Berhane:- ርዐዮት ሐኪም ተከለከለች በለኝ – ምንም ማድረግ ባልችል አብሬ እታመማለሁ፡፡
ፍቅረኛዋን በዚህ ቅዳሜና/እሁድ ሳታገኝ ቀረች በለች አዝናለሁ፡፡
ሌላው የሚዲያ ሰርከስ አይመለከተኝም፡፡
ወዳጄ ስላቁን ተመልከቱ፡፡የርእዮትን የርሃብ አድማ ፍቅረኛዋን ከማግኘት ጋር በማቆራኘት እቃቃ ሊያደርገው ይሞክራል፡፡አስረኛዋ በማንም የመጎብኘት ፍቅረኛዋን ጨምሮ መብት አላት፣ህክምና ማግኘትም የታሳሪ መብት ነው፡፡ወደ ጡት ካንሰርነት ሊያደግ የሚችል እጢ እንዳለባት የተነገራት ሴት የህመሙን እድገት ለመቀነስ የተመረጠ ምግብ መብላት፣ጭንቀት ከሚፈጥር ሁኔታ መራቅ ይገባታል፡፡የጀመረችው የርሃብ አድማ ደግሞ በተቃራኒው ለህመሙ መፋጠን የራሱን አስተዋእጾ ያበረክታል፡፡ምጡቅ ሆይ ሰብዓዊነት ግድ ሊለን አይገባም ይሉን ይሆን?አብረው የሚታመሙ ከሆነ ምነው አብረዋት ባይራቡ የመራቧን መንስኤ ባያወላግዱት?ረስቼው ምጡቅነት ለካ ለሰብዓዊነት ቦታ የለውም፡፡

10 Comments

  1. You don’t have even half Daniel’s caliber and brain. Face it Mr. Dawit!

    It is amazing, these day, any one who can write is being titled Gazetegna!

  2. Theft, robbery, photocopy, lying or fraud is not the standard for measuring IQ. May be gays don’t know what IQ is.

  3. ጎበዝ ጊዜያችሁን ለመልካም ነገር መጠቀም መቻል ብዙ ልንደርስባቸው ወደአሰብነው ግቦች ሊያደርሰን ይችላል ያ! ግብ ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? ኢትዮጵያን በጋርዮሽ የሚገዙዋትን የወረሯትን (ሻቢያና ህወሃት) ከኢትዮጵያ ምድረ-ገጽ ማስወገድ ነው። አሁን ተግባባን? እነማን ናቸው ኢትዮጵያን በጋርዮሽ የሚገዟት ሻቢያና ህወሃት? ቴዎድሮስ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ፤ደብረጽዮን፤በረከት፤ሳሞራ፤ስብሃት ነጋ ፋሲል ኖሆም…ወዘተ ኤርትራዊ ሲሆኑ ከትግራይ አባይ ጸሃየ አባይ ወልዱ ስዩም መስፍን ፤አዲሱ ለገሰ፤ተፈራ ዋልዋ እስረኛው ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን ከትግራይ ሲሆኑ እንደ ዳንኤል ብርሃኔ ያለው ደግሞ የተወለደው በወያኔ ጊዜ ያደገው በውያኔ ጊዜ የተማርረ ከሆነ ተምሮ የሚሆነው ጠባብነትን በሰው ሞት መደሰትን በወያኔ ጊዜ የተካነው ስለሆነ ገና ራሱን እስከሚያውቅና ራሱም ነፃ እስከሚወጣ ድረስ ክሚቃጅ ጋር መቃጀት ተገቢ አይሆንም።

  4. Because they do not fell secured, all the EPRDF’s cadre are now a days are becoming just like a stinging snake. They understand that Ato Melese was a bad leader who left them unsecured. Since all dictators are not act like a true leader who have confidence in their own people, that is why those cadres have a big mouth and tell unreasonable talks.

  5. Unsecured leader just like Melese Z. is very dangerous. He is dangerous for his followers, party members, and finally for the existence of his organization/s. Do all EPRDF’s member know this logic properly. That is why things becomes for them like a nightmare. Here and there just like a dog infected by rabies virus which is a killer disease and dangerous to human beings..

  6. There goes the debacle between ingenious and insanity. Tplfites change the definition of everything these days. We do not even know the definition of right and wrong anymore. Visionary Ethiopians languish in tplf prisons throughout Ethiopia for their ideas on bogus terrorism charges. For instance, Andualem is in prison for his brave political ideals. If this guy called Daniel think his ideals are superior than anyone, let him debate with Andualem ( He is not to be allowed to bring his AK-47; the debate will be civil ). And let us see who wins. Bring it on tplfites! I challenge you. Reyote alemu is in prison because of her superior visions, ideals and for standing up for the truth. The whole world think the braves should be rewarded, and she was rewarded for that. Tplf punishes rights and reward corruption, abuse, blind loyalty, and wrongs. As we all know, tplf has guns no ideas. The only idea that comes from tplf is building condominium. If you think the Egyptians built the pyramids 5000 years ago, this idea would be laughable. Beautiful and superior ideas are incarcerated in tplf prison. What does this tell us? You see my fellow Ethiopians, when you engage someone in argument, and that someone scream at you, beat you, put you in prison, and kill you, that simply means that someone lost the argument. Tplf and its supporters who argue on behalf of their bosses are insane or barely humans.

  7. አሁን ማን ይሙት ዳኒኤልን መከታተል ራስን ማዋረድ አይደለምን? just forget him. endiawum unlike bemadireg ena minim teketay endaynorew bemadireg zero masgebat new. coz commentu justified aydelem, genbim aydelem, so ignore him as one of the stupids of TPLF

  8. yezine dedebe amelekaket ante medgeme gematen eyazametke newe yemeselegnale tebabe sew hulem ene geniuse negne bilo newe yemiamenew weyanewoch erasachewn metuke weym geniuse argew yemiayute tegebinete alew yemnadergew neger aheyanetachenene selemiasay yemeslegnale mezengatachen, betenesh neger medesetachene shekem mechalachen enesune giniuse egnane aheya maderegu ayasgermeme ahune egna drama,quase,FM, radio madamete neberebene? tadia enhagose lemen geniusnen ayhunu sente sewe eserebet taguro,sentu tesedo,sentu moto ergefe argene restene eskesta kesereden bemn keaheya teleyene

Comments are closed.

Share