አያ ተክሌ ምነዉ አህያዉን ትተዉ ፈረሱን ቢጋልቡ

 በደርብ ከፈለኝ

አዋቂ መስሎኝ ሰምቼዉ
ትልቅ ሰዉ መስሎኝ ተጠግቼዉ
በቃኝ . . . በቃኝ  አወቅኩትና  ናቅኩት
ለካስ ወዳጄ ኖሯል ፈረስ እየናቀ አህያ የሚጋልብ
በሬ እያቀጨጨ ጅብና ድብ የሚያደልብ

ከላይ አያ ተክሌ ብዬ የጀመርኩህ ተሳስቼ ነዉ። ከአሁን በኋላ ግን አቦይ ተክሌ ብዬ ነዉ የምጠራህ። አይዞህ “አቦይ” ያልኩህ እንደ አቦይ ስብሐት አርጅተህብኝ አይደለም። አወቃለሁ አንድ ፍሬ ልጅ ነህ . . .  አዎ ልጅ ነህ . . .  አሁንም ልጅ!  “አቦይ” ብዬ ሹመት የሰጠሁህ  አነጋገርህ፤ አስተሳሰብህና እንዳዉ አኳኋንህ ሁሉ ከአቦይ ስብሐት ጋር ስለተመሳሰለብኝ ነዉ፤ ወይም እንደ አቦይ ስብሐት ቀላማጅ ነህ ትቀለማድለህ ማለቴ ነዉ። አቦይ ተክሌ ምንም ቢሆን የቅርብ ጓደኛዬ ነህና የጓደኝነቴን ምክር ቢጤ ልሰጥህ እስኪ ስማኝ። አቦይ ስብሐት ሃያ ሁለት አመት ሙሉ ቀላምደዋል፤ ከአሁን በኋላ ልቀላምድ ቢሉም አንድ ሐሙስ ነዉ የቀራቸዉ። አንተ ግን አንድ ፍሬ ልጅ ነህ፤ እንግዲህ ይታይህ 35 አመት፤ 40 አመት፤ 50 አመት፤ ስልሳ አመት እያልክ ወዳጅና ጠላት፤ዘመድና ባዳ ፤ ጎረቤትና የማዶ ሰዉ ሳትለይ ይህንን ሁሉ አመት እየቀላመድክ ልትኖር ነዉ . . .  ያዉም በዚህ እንደ አሞራ በሚበርረዉ የዳያስፖራ ኑሮ። ምነዉ ተክሌ ቢቀርብህ!  መዶሻ የያዘ ሰዉ ሁሌም የሚመለከተዉ ሚስማር ብቻ ነዉ ሲባል ሰማሁና መዶሻ የያዘ ሰዉም መሰልከኝ፤ አሁን ግን በደንብ አድርጌ ሳይህ መዶሻ የያዘ ሰዉ ሳይሆን ጭራሽ መዶሻዉን እራሱን መሰልከኝ።

 

“ዬት ይደርሳል የተባለ ጥጃ ሉካንዳ ታየ” . . .  አያ ተክሌ . . .  ይቅርታ አቦይ ተክሌ ማለቴ ነዉ . . . ይህ ስንኝ የተቋጠረዉ ለሌላ ለማንም ሳይሆን ላንተ ብቻ ይመስለኛል። እስኪ ንገረኝ ተክሌ ምነዉ የነካሄዉ ነገር ሁሉ አይበረክት ወይ አንተ አትበረክት። እስኪ መለስ ብለህ አስበዉ ECADF፤ EHSNA፤ ESAT TV ፤ ESAT Radio ሁሉንም ነካ ነካ ግን አንዱንም ሳታረካ አንተም ሳትረካ እንዳዉ ዉኃ ላይ እንደተንሳፈፈ ኩበት ባክነህ ቀረህ። ምነዉ ወንድሜ ተክሌ እንዲህ ነበር እንዴ እኔና አንተ የምንተዋቀዉ? ምን ላድርግ እንደዛ ማታ ማታ እንደምንጫወትበት ካርታ ተበዉዝክብኝኮ። ምነዉ ተክሌ የተደበቀዉ ጸባይህ እየወጣ ነዉ ወይስ ድሮ ሳዉቅህም እንዲህ ወናፍ ነበርክ? ተክሌ ከሁሉም ከሁሉም የምታናድደኝ ደርሶ አዋቂ ለመመሰል  ቱግ ቱግ ስትል ነዉ፡፡ ዉድ ጓደኛዬ ተክሌ እባክህ ተረዳኝ እኔ አዋቂ አትሁን ማለቴ አይደለም፤ ግን አዋቂ ለመሆን አዋቂ ሁን እንጂ አዋቂ አትምሰል። ደግሞም ቱግ ቱግ እንኳን ባንተ በእንደኔ አይነቱ አንድ ክንድ ከስንዝር በማትሞላዉ ባንተ በሸበላዎቹም አያምርም። ስለዚሀ ተክሌ እባክህ እንዳቅምህ . . .  አዎ እንዳቅምህ!

 

በያ ሰሞን በየድረ ገጹ እየገባሁ  ያገኘሁትን ሁሉ ሳነብ አንተም የሞነጫጨርከዉን አገኘሁና አንብቤዉ በጽሁፍህ ሳይሆን በጓደኝነትህ አፈርኩ። እስኪ ንገረኝ ተክሌ ምን ይሁን ብለህ ነዉ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዉን ፖለቲካ አትተንትን ያልከዉ፤ እናስ ምን ይተንትንልህ? እኮ ንገረኝ ተክሌ የፖለቲካ ፓርቲ መሪ ፖለቲካ ካልተነተነ ሌላ ምን ይተንትን?  ለመሆኑ ያልተተነተነ ፖለቲካ ምን አይነት እስትራቴጂ ነዉ የሚወጣለት? ምነዉ ተክሌ “አወቅሽ አወቅሽ ሲሏት” የምንላትን ሴትዮ ሆንክብኝ! የፖለቲካ ፓርቲ መሪ ሆኖ የአገሩን የፖለቲካ ሁኔታ የማይተነትንና መጻኢዉን እዉነት በስዕል ቀርጾ የማያሳየን ከሆነ ምኑን የፖለቲካ ፓርቲ መሪ ሆነ . . .  እንደሱ አይነት የፖለቲካ ፓርቲ መሪማ ካንተ ጋር የዋለ ሰዉ ማለት ነዉ። አይዞህ ተረት ጎበዝ ነህ ብዬ ነዉ (ከአህያ ጋር የዋለች . . . )  አቦይ ተክሌ ችኩልነትህን ድሮም አዉቀዋለሁ፤ ከተናገርክ በኋላ የምታስብ ሰዉ መሆንህም ለእኔ አዲስ አይደለም፤  ግን ምነዉ ተክሌ . . .  ያንተ እዉነት የሰዉ ሁሉ እዉነት ይመስልሃል እንዴ? እንደዚህማ ከሆነ እዉነት የሚባል ነገር ምድር ላይ የለም ማለት ነዉኮ!  ተክሌ እባክህ በዚህ “ካፍ ከወጣ አፋፍ” በሆነበት አለም ከመናገርህና ከመጻፍህ በፊት አስብ። ፈረንጆቹ (Think twice before you speak once) ይላሉ። ተክሌ አንተ ግን የሚጽፈዉ እጀህ ደራሽ የሚናገረዉ አፍህ ነካሽ ነዉና እባክህ እንዳዉ በዚያች በምታከብራት በወላዲት አምላክ ይዤሃለሁ ከመናገርህ  በፊት አምስቴ አስብ (Think five times before you speak once).

 

መቼም የኛ ነገር “አፍ ያለዉ ጤፍ ይቆላል” ነዉና አንድ ሰሞን ይችኑ የምትንጣጣዉን አፍህን አይተዉ  ኢሳቶች ወያኔ ላይ ብትንጣጣላቸዉ ብለዉ አስጠጉህ አንተ ግን ጠላትና ወዳጅ ሳትለይ ሁሉም ላይ የምትተኩስ ጉድ ነህና ኢሳቶች ላይ እሳት ሆንክባቸዉና እሳት አደጋ ጠርተዉ በግዜ ተገላገሉህ። ተክሌ ልክ እንደ ቁመትህ ምን ያህል ትንሽ ሰዉ እንደሆንክ ያየሁት በስራ አጋጣሚ የምታዉቀዉን ነገር ሁሉ ድረ ገጽ ላይ እንዳላዋቂ ሳሚ መለቅለቅህ ነዉ። አሁን ይህ ምን ይባላል? አዋቂነት ወይስ ጅልነት? መልሱ ቀላል ነዉ፤ ተክሌ አንተ አዋቂነት የሚባል ነገር በአጠገብህ ያለፈም አይመስለኝም። ጅልን ለማወቅ ደሞ ጅል መሆን የግድ ይላልና እስኪ እዚያ የሞነጫጨርከዉ መጣጥፍ ላይ የከተብከዉን ዝባዝንኬ እንዳለ ላሳይህ

ተጨማሪ ያንብቡ:  የኢትዮጵያ ማኅጸን ያፈራውን ዳግማዊ ካሊጉላ የምትከተሉ ወዮላችሁ! - ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

 

“ይሁን እንጂ፤ የኢሳት አስተዳዳር የሆነው ወዳጄ ነአምን ዘለቀ የዛሬ አመት አካባቢ እንዲህ ያለው ተመሳሳይ ስብሰባ ሲዘጋጅ፤እባክህን መሪዎቹ ንግግር ያሳጥሩና ለሰዉ እንዲተነፍስ ግዜ ይስጡት ብዬ አሳስቤው ነበር። ነአምን አንዳንዴ አይሰማም። ወይም ቢሰማም አያደምጥም” አቦይ ተክሌ

 

“ነአምን አንዳንዴ አይሰማም። ወይም ቢሰማም አያደምጥም” . . . ወይ ጉድ! አንተንስ ምን እንበል? . . .  ተክሌ የሚባል ስም ከተሸከምክ ጀምሮ ሰምተህም አዳምጠህም የማታዉቀዉን ጆሮም አፍም የሌለህ እንግዳ ፍጥረት! ለካስ አለምክንያት መዶሻ አልተባልክም!  ነአምንማ እንተም እንደመሰከርክለት አንዳንዴ ነዉ እንጂ አብዛኛዉን ግዜ ይሰማልኮ፤ እንደዚህ ብዙ ግዜ የሚሰሙ ኢትዮጵያዉያን ደግሞ ብርቅዬ ናቸዉ . . . የሉማ! እስኪ ንገረኝ ተክሌ ምንድነዉ እየነገርከን ያለኸዉ፤ አንተ ሁሉን ነገር  አዋቂዉ ተናግረህ ነአምን አላዋቂዉ አለመስማቱን ነዉ ወይስ ከዚህ ሌላ የምትለን ነገር አለ? ደሞኮ ከብዙ ጉድ ያዳነን የነአምን አንዳንዴ አለመስማት ነዉ እንጂ ሰምቶህማ ቢሆን ኖሮ የዛሬዉ ትግላችን ከወያኔ ጋር መሆኑ ቀርቶ አንተ የቀደድከዉን ቀዳዳ መቋጠር ላይ ይሆን ነበር። ችግሩ ዲሲ ላይ አትቅደድ ብለዉ ሲያባርሩህ ቶሮንቶ ሄደህ ደሞ እንደገና ትቀድዳለህ . . .እስኪ ንገረን የሚቀደድ የሌለበት ዬት አገር እንስደድህ?

 

አቦይ ተክሌ  . . . ዶ/ር ብርሐኑ በሐይማኖት ጉዳዮች ላይ የጻፉት ሰፋ ያለ ጽሁፍ አልገባህ እንደሆነ መጠየቅ አንድ ነገር ነዉ፤ አለዚያ ስምም፤ሀሳብም ጸባይም  እንደምትጋራቸዉ እንደ አቦይ ስብሐት ህዝብ አንዳለ ባኮረፈበት አገር “ያኮረፉ ሰዎች እንጂ ያኮረፈ ህዝብ የለም” ብትል አባባሉ ለግዜዉ ሊያምርልህ ይችል ይሆናል፤ እመነኝ የሚሰማህ ግን አታገኝም። የዶ/ር ብርሀኑ ጽሁፍ ላይ ገጽ 16 መጨረሻና ገጽ 17 መጀመሪያ ላይ የቀረበዉ ሃሳብ ጥልቅ ወይም ሐቀኛ አይደለም ብለሃል። እስኪ ንገረኝ ተክሌ ምንድነዉ መለኪያህ? ጥልቀቱን ባንተ ስንዝር ሐቀኝነቱን ባንተ ሚዛን ነዉ የለካኸዉ? ከሆነ… አብረን ስለኖርን ዝንዝርህንም ሐቅህንም በሚገባ አዉቃለሁና አልፈርድብህም። አቦይ ተክሌ እንዳዉ ያንተ ነገር “አህያ ማር አይጥማት” ሆኖብህ ነዉ እንጂ እስኪ አሁን ምኑ ላይ ነዉ ያ ጽሁፍ ጥልቀት ያጣዉ ምኑስ ላይ ነዉ ሀቅ የጎደለዉ? አንድን ሰዉ ደደብ ነዉ ብሎ አንድ ሙሉ መጽሐፍ መጻፍ ይቻላልኮ፤ ለዚህ ደግሞ የሚያስፈልገዉ ብዙ ጥረትም አይደለም አንድ ያንተ አይነት ጭንቅላት ይበቃል። ችግሩ የሚመጠዉ የሰዉየዉን ደደብነት ዋቢ ጠቅሶና መረጃ አስይዞ ማቅረቡ ላይ ነዉ፤ እንደዚህ አይነቱ መረጃ ደግሞ እንኳን አንተ አያገባዉ ይገባል ያልከዉ ሰዉ ላይ ቀርቶ የእርጎ ዝንብ የሆንከዉ አንተ ላይም ማቅረብ አስቸጋሪ ነዉ። አይህ ወንድሜ ተክሌ አንተም እንደዚሁ ነህ። ሰዉን “ደደብ” ለማለት አፍህ ይቀድማል መረጃ ተብለህ ስትጠየቅ የምታሳየን ግን ያንኑ የምናዉቀዉን ባዶነትህን ነዉ . . .እሱ ደግሞ ሰለቸን . . .  አዎ ሰለቸን! ሰማህ ተክሌ ሰለቸን።

 

አቦይ ተክሌ ደሞ ብለህ ብለህ አንተም እንደ ወያኔ ምሁራን ተቃዋሚዉን ሁሉ “ሊብራል” ልትለዉ ነዉ እንዴ! መቼም አንዳንዴ ነካ ሲያደርግህ እንደ ዕብድም መሆንም ያምርሃል እንጂ በወያኔነት እንኳን በፍጹም የምትታማ ሰዉ አይደለህም፤  ግን . . . ግን ጠንቀቅ በል ልጄ ዉኃኮ ሲወስድ እያሳሳቀ ነዉ . ..  እንግዲህ ይታይህ ተክሌ ባንተ መንቀዥቀዥኮ መወሰድህ ነዉ!  ብሉይን በመቀበል ከዚያ ክርስትናን፤ ከዚያ እስልምናን፤ ከዚያ ካቶሊክን፤ ከዚያ ፕሮቴስታነንስዝምን፤ በመቀበልና በማቻቻል የኖረች አገር ናት ብለሀል አገራችን ኢትዮጵያን። እርግጥ ነዉ፤ ግን ለመሆኑ ብሉይ የሚባል ሐይማኖት አለ አንዴ ወይስ አንተዉ ወደኋላ ሄደህ ልትጀምር ነዉ? ደግሞስ ክርስትና፤ ካቶሊክና  ፕሮቴስታነንስዝም ስትል ካቶሊክና ፕሮቴስታንት ምን መሆናቸዉ ነዉ? ክርስትና አይደሉም እንዴ? ወይስ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከምንም ተቋም ጋር የማይገናኝ “ክርስትና” የሚባል ሐይማኖት አለ? አየህ ተክሌ ምን አይነት የተበላሸ ጭንቅላት እንዳለህ የሚያሳየዉ እንደዚህ አይነት ቆሻሻና ወደ አንድ ወገን ያጋደለ ትንተናህ ነዉ። ይልቅ ምነዉ እንዲህ አይነቱን ጭንቅላት የሚፈልገዉን ትንተና ለዚያ አትችልም ላልከዉ ሰዉ ብትተዉለት! ማቻቻል የሚል ቃልም ተናግረሃል፤ ምን ማለትህ ነዉ? ኢትዮጵያ ዉስጥኮ ማን ማንን ችሎ እንደኖረ ግልጽ ነዉ . . .  እና አሁንም በዚያዉ እንቀጥል ነዉ እንዴ የምትለን? ዶ/ር ብርሀኑኮ በዚያ ጸሁፉ ዉስጥ ያስነበበን የተለያየ ሐይማኖት ቢኖረንም እንዴት ሁላችንም ያሰኘንን ሐይማኖት ባሰኘን መንገድ እያመለክን (ይግባህ መቻቻል አይደለም) በእኩልነት ተከባብረን መኖር እንደምንችል ነዉ። ይህንን ደግሞ ሊብራል ዲሞክራሲ በሚገባ ተንትኖ አስቀምጦታል። አየህ ተክሌ  ፖለቲካ ተንትን ተብሎ ስራ ሲሰጥህ አንደጋይኮ ኮሜርሻል ነገር ትደባልቃለህ፤ አዋቂ ሲተነትን ደሞ አትተንትን ብለህ ትወርድበታለህ፤ ምነዉ ተክሌ . . .  “ያግቡብሽ እምቢ ያዉጡብሽ እምቢ” ሆንክሳ!

ተጨማሪ ያንብቡ:  ለዳቦ ጥያቆ አንድና አንድ መልሱ ዳቦ ነው። (ዳዊት ዳባ)

 

ኦባማ ሲመረጥ ምሁር ነበር ብለሃል. . . . አይደለም ብዬ ብከራከርህስ?  ምነዉ ተክሌ የማታዉቀዉ ዉስጥ ገብተህ ትፈተፍታለህ! አባማ ፕሬዚዳንት ሆኖ ሲመረጥ የፖለቲካ ሰዉ (ሴኔት) ነበር፤ ዛሬም የፖለቲካ ሰዉ ነዉ። በእርግጥ ኦባማ የምሁር ችሎታዉም ተሰጥኦዉም አለዉ፤ ግን በምሁርነት የሚበልጡት ሺዎች አሉ፤ ኦባማን አባማ ያሰኘዉ በምሁርነት ችሎታዉ ላይ አዳብሎ የያዘዉ ከፍተኛ የፖለቲካ ችሎታዉ ነዉ (ይህ ችሎታ የፖለቲካ ትንተናዉንም ያጠቃልላል)። አለዚያ ለምሁርነቱማ ሀርቨርድና ፕሪንስተን ዉስጥ አባማን የሚያስከነዱ ብዙ ምሁራን አሉኮ። ተክሌ አንተኮ አንዳንዴ የምትናገረዉንም የምታዉቅ አይመስለኝም፤ ለዚህ ይመስለኛል ‘ተክሌ’ ከተናገረ በኋላ ነዉ የሚያስበዉ እየተባልክ የምትታማዉ። ምሁር ምሁርነቱ ሲቀንስ ወደ “ቡሽነት” ይለወጣል ነዉኮ ያልከዉ? የፈጣሪ ያለህ!  . . .  ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም አሉ፤ ዕድሜ ላንተ ዘንድሮ ሊጣባ ነዉ። አየህ ተክሌ በዚህ አንተ ባልከዉ ስሌት ከሄድንኮ ኢሳት ዉስጥ ዜና ያነበበ ሰዉ ሁሉ ወናፍነቱ ሲጨምር ‘ተክሌ’ ይሆናል ማለት ነዉኮ . . .  እንዴ! እኛ አነተ አንዱም አላስቀምጥ ብለኸናል ደሞ ስንት ተክሌ ሊኖረን ነዉ?  ከዚህስ ቸሩ ፈጣሪ ይጠብቀን!!

 

“የፖለቲካ ተንታኝ የምለው፤ በፖለቲካ ውስጥ በቀጥታ በአድራጊ-ፈጣሪነት ሳይሳተፍ ወይም መሳተፍ ሳይጠበቅበት፤ የአንድን ፖለቲካዊ ስብስብ/ማህበረሰብ ፖለቲካዊ ሁኔታ እየቃኝ፤ ከአካባቢያዊና አለማቀፋዊ ሁነቶች ጋር እያጣቀሰ የሚናገር ነዉ” ብለሀል። ለመሆኑ ይህ የተናገርከዉ ነገር ያንተ ህግ ነዉ ወይስ የሁላችንም?  ያንተ ከሆነ ያንተ ነገር ሁሉም ግራ የተጋባ ነዉና አልፌሃለሁ። ግን ምነዉ ተክሌ ሰሜን አሜሪካ ዉስጥ እየኖርክ ፖለቲካ በምሁርና በፖለቲከኛዉ ሲተነተን ልዩነቱ አልገባህ አለ? እስኪ የሚገባህ ከሆነ ምሳሌ ልስጥህ . . .  ፕሮፌሰር ላሪ ሰባቶ (ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቨርጂኒያ) አንተ ያልከዉ አይነት የታወቀ ምሁርና ፖለቲካ ተንታኝ ነዉ፤ ግን ፖለቲካ አድራጊም፤ፈጣሪም አይደለም ። ተሳትፊ ግን ነዉ። አንተ ከዬት እንዳመጣኸዉ አላዉቅም አንጂ  ሰዉ ሆኖ ፖለቲካ  ላይ የማይሳተፍ የለም፡፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ  ፖለቲካ አድራጊም፤ፈጣሪም  ተሳታፊም ናቸዉ፤ ዋናዉ ስራቸዉ  ፖለቲካ መተንተን ላይሆን ይችላል፤ ግን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የአሜሪካንን ፖለቲካ ተንትነዉ ለህዝብ ማቅረብ ግዴታቸዉ ነዉ።  ህዝቡም ጆሮዉን በአብዛኛዉ የሚሰጠዉ ለፖለቲካ ኤክስፐርቱ ለላሪ ሰባቶ ሳይሆን ለፖለቲከኛዉ ለኦባማ ነዉ። አየህ ተክሌ ባንተ አባባል ፕሬዚዳንት ኦባማ ፖለቲካ ትንተናዉን ለላሪ ሰባቶ መተዉ አለባቸዉ ማለት ነዉ፤ ወይም የኦባማ ፖለቲካ ትንታኔ ያልጠራ የላሪ ሰባቶ ትንታኔ ግን የጠራ ነዉ ማለት ነዉ . . . እንዴት ሆኖ!  እርገጠኛ ነኝ ይህንን ጽሁፍ አንብበህ ስትጨርስ በራስህ ቅዠት ይምትስቅ ይመስለኛል። በነገራችን ላይ የኢትዮጵያም ፖለቲካ እንደዚሁ ነዉ፤ ጋዜጠኛዉም፤ የዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሩም፤ ሌላ ሌላዉም ሊተነትነዉ ይችላል፤ ግን ህብረተሰቡ (አንተን ላይጨምር ይችላል- አዋቂ ነሃ!) በብዛት ጆሮዉን የሚሰጠዉ ፖለቲካዉን የፖለቲካ መሪዎች ሲተነትኑት ነዉ። ደሞ ማነዉ ምሁር ሁሉ ፖለቲካ መተንተን ይችላል ብሎ የነገረህ?  አቦይ ተክሌ ሌላዉ ትልቁ ችግርህ ሰዉ ያለማክበር ነቀርሳ አለብህ፤ ለምሳሌ ዶ/ር ብርሀኑን አንዴ ዲባቶ ብርሀኑ ፤ አንዴ ብርሀኑ ነጋ፤ ሌላ ግዜ ደግሞ ልክ እንደ ቆሎ ጓደኛህ “ብሬ” ብለህ ጠርተዋኸል። ዶ/ር ብርሀኑ በዕድሜ ይበልጥሃል ደግሞም አስተማሪህ ነዉ፤ ስለዚህ አጠገቡ ስትሆን ዶ/ር ብርሀኑን እንዳሰኘህ መጥራት ትችላህ እሱ ያንተና የሱ ጉዳይ ነዉ፤ ለኛ ስትጽፍልን ግን ኢትዮጵያዊ ባህላችን ነዉና ማክበር ግዴታህ ነዉ። ይህንን ታላቆችህን የመዘርጠጥ ነቀርሳ በግዜ ካልታከምከዉ ብዙ ታዳጊ ልጆቻችንን ታበላሻለህና አንተዉ  ጽሁፍህ ላይ በጠቀስካት በእመ ብርሀን የዤሃለሁ እባከህ ታላቆችህን አክብር።

ተጨማሪ ያንብቡ:  አንዳርጋቸው ጽጌ! ከኢሳያስ ጉያ፤ ነጻነት? ወይስ ባርነት?

 

ኢትዮጵያ ዉስጥ ሙስሊም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ያነሱትን የመብትና የነፃነት ጥያቄ ሙሉ በሙሉ የምንደግፍ ኢትዮጵያዉያን፤ የምንደግፍ ግን ንቅናቀዉን በጥርጣሬ አይን የምንመለከት ኢትዮጵያዉያንና ጭራሽ ንቅንናቄዉን የምንቃወም ኢትዮጵያዉያን አለን። አቦይ ተክሌ አንተም የሙስሊሙን ህብረተሰብ እንቅስቃሴ መጠራጠር መብትህ ነዉ፤ ያ እዚያ ሙንጭርጭርህ ላይ የወረድክበት የፖለቲካ ተንታኝም አትጠራጠሩ አላለምኮ! መቼም ያንተ ዱላ ልክ እንደ ወያኔ ፌዴራል ፖሊስ ዱላ ያገኘዉ ሁሉ ላይ ይመዘዛል እንጂ ዶ/ር ብርሀኑማ እንድያዉም የሙስሊሙን እንቅስቃሴ የሚጠራጠሩ ሰዎችን በመንግስት ፕሮፓጋንዳ የተደለሉና የሐይማኖት አክራሪነትን የሚፈሩ ብሎ በሁለት ከፍሎ ነዉ ያስቀመጣቸዉኮ። አንተ ግን በዚያ በተከፈተ ቁጥር አንደ “ታድፋለች ቅጥ” በሚሰፋዉ አፍህ “ብሬ አድበሰበሰው” ብለህ አረፍከዉ። መቼም በባህላችንም ቢሆን ነዉር ነዉና አደባባይ ላይ “ባለጌ” ብዬስ አልሰድብህም!

 

ምንም ቢሆን ተሰድደህ ዳያስፖራዉን የተቀላቀልከዉ ለትግል ነዉና አስኪ አንድ ነገር ልጠይቅህ . . . . ክርስቲያኑ የሙስሊሙን የመብትና የነፃነት ጥያቄ በጥርጣሬ የጎሪጥ ከተመለከተዉ፤ ሙስሊሙ ደግሞ ይህንን እሱን በጥርጣሬ የሚለከተዉን ክርስቲያን በትግል አጋርነቱ ካላመነዉና ካልተቀበለዉ እንዴት ሆኖ ነዉ የኛ ትግል ግቡን መትቶ አገራችን የምንገባዉ? ይሄዉልህ ተክሌ በዚያ አስቀያሚ የፖሊስ ዱላህ ደጋግመህ የጨረገድከዉ ሰዉ እንዲህ አይነቱን አንተ አይቶ ለመረዳት አመትና ሁለት አመት የሚፈጅብህን ነገር እሱ በግዜ አይቶና ተንትኖ ለህዝብ ያቀረበ ሰዉ ነዉኮ! ምነዉ የልጅነት ገደኛዬ እንዲህ ገብስ ሆንክብኝ ከገብስም የነፈዘዉ! ለመሆኑ ጽሁፉን በደምብ አንብበኸዋል ወይስ ለትችት የሚመችህን ቦታ ብቻ ነዉ እየመረጥክ ያነበብከዉ፤ ለዚያዉምኮ አንተኑ ለትችት የሚያጋልጠዉን ቦታ ነዉ የመረጥከዉ። ለነገሩ አንተ መምረጥ መች ታዉቅበታለህ? ብታዉቅ ኖሮ አንዳቅምህ ትኖር ነበር። ዶ/ር ብርሀኑኮ እንደ ማንም ሰዉ የሚተች ሰዉ ነዉ፤ እንዳዉም እንደሱ ለትችት የተጋለጡ የፖለቲካ መሪዎች በጣት የተቆጠሩ ናቸዉ፤ በየቀኑ እንደሰሩ ነዋ! አንተ ግን ወይ አትሰራ፤ ወይ አታሰራ እንዳዉ “ዝናር በቅፌን” ይመስል መናኛ መናኛዉን ኮተት ተሸክመህ ከሚሰሩ ሰዎች ጋር ትቀላቀላለህ። አሁን እስኪ ተክሌ በሞቴ ንገረኝማ . . .  ተክሌ እንዴት ጎበዝ ነዉ፤ ዶ/ር ብርሀኑን እኮ አገኘዉ፤ ልክ ልኩን ነገረዉ ብለዉ ያንተ ብጤ ጥቅት ወናፎች ቢያናፍሱልህ እዝያ ቁመትህ ላይ ስንዝር ይሚጨምሩልህ ይመስልሃል? ቢጨምሩስ?

 

አየህ አቦይ ተክሌ ጽሁፍኮ ፊደልና ፊደል ማገናኘት ስለምንችል ብቻ የምንገባበት የጨረባ ተዝካር አይደለም። መጻፍ ማሰብ፤ ማሰላሰል፤ ማንበብና ነገሮችን የማመዛዘን ችሎታን የሚጠይቅ ትልቅ ስራ ነዉ፤ አንተ ደሞ ነገሮችን መቀላቀል ነዉ እንጂ ከእነዚህ እሴቶች ጋር በተለይ ከማሰብና ከማመዛዘን ጋር ጭራሽ የምትተዋወቅም አይመስለኝም። እዩኝ እዩኝ ትላለህ፤ አወቅኩ አወቅኩ ታበዛለህ። አንዳንዴማ ጭራሽ ካንተ በላይ የሚያዉቅ ሰዉ ያለም አይመስልህም። የሰዉ ልጅ የማዉቁ ትልቁ ምልክት አለማወቁን ማወቁ ነዉ። ኦይ ተክሌ ላንተ ግን ይህ የጠቢባን አባባል ተረት ነዉ የሚመስልህ። እባክህ የማታዉቀዉን ነገር አላዉቅም በል። በተለይ በተለይ የማተዉቀዉ ነገር ላይና በደምብ ያልገባህ ነገር ላይ አትጻፍ፤ አትተች አስተያየትም አትስጥ። ዉድ ጓደኛዬ ተክሌ አንግዲህ አንድም ገና የምታድግ ሰዉ ነህና ደሞም ሰዉ እፈር ተብሎ የሚነገረዉ ዉድቀቱን ሲረዳ ስለሆነ “እፈር “ ብዬህ አፌን አላበላሽም። እስከዛሬ እንዳየሁህ አንተም እንጣጥ እንጣጥ ማለት ነዉ እንጂ እፍረት የሚሰማህ ሰዉ አይደለህም። እንጣጥ የሚያበዛ ሰዉ ደግሞ ያመለጠዉ ለታ ዕድሜ ልኩን ያፍራል። እንግዲህ ይህ መጥፎ ቀን ሳይመጣብህ ከአቅምህ በላይ መዝለሉን አቁም። እርግጠኛ ነኝ ተክሌ ይህንን ጽሁፍ አንብበህ “ዲሞክራሲ” የማይገባቸዉ ሰዎች ሀሳቤን የመግለጽ መብቴን ሊቀሙኝ ነዉ እንደምትል፤ ሆኖም የዚህ ጽሁፍ ጥረት የዲሞክራሲ ጽንሰ ሀሳብ አንዲገባህና ከሰዎች ጋር በቡድን ስትሰራ ሌሎችን ሳትጋፋና ሳታስቀይም ሀላፊነት ተሰምቶህ ግዴታህን እንድትወጣ ነዉ እንጂ የሁላችንም ትግል ለመብት መከበር ነዉና መብትህን የነካም የደፈረም የለም። የፖለቲካ መሪዎቻችንን መተችትና ስህተት ሲሰሩ ተከታትሎ ማጋለጥ እጅግ በጣም አስፈላጊ ነገር ነዉ፤ ነገር ግን የሌለ ስህተት እየፈጠርክ፤ ያልተጻፈ  እያነበብክና ሰዎች ደፋር ተቺ ነዉ እንዲሉህ ብቻ የሚሰሩ ሰዎችን ባትቦጫጭቅ ጥሩ ይመስለኛል። አንድ ሰዉ ባጠፋዉ ጥፋት የሚያዝነዉ ለሌሎች ካለዉ ክብርና ፍቅር ነዉና . . .  ተክሌ እስኪ እባክህ ለህዝብ ክብር ስትል ጥፋትህን ተረዳና ከራስህም ከወገንም ጋር ታረቅ። የምትመኘዉን ትልቅ ሰዉ ለመሆን ከፈለግክ የትልቅነት መንገዱ ይህ ነዉ። እግዜር ይርዳህ!

19 Comments

  1. ኣለገባኝም ስድብ ነው ወይስ ኮመንት ሲጀመር ጀምሮ እስኪጨረስ ዽረስ ክስድብ ያለፍ አንዳች ፍሪ ሀሳብ አጣሁበት እንደኒ ሀሳብ ጋደኛክ ከሆነ በኤሜል ብትልክለት ጥሮ ይመስለኝ ነበር። እያስነበብከን ያለው የአንተን ከስነስራት የወጣ የግል ቄም ስድብ እንጄ ቢሳሳት እንካን እሶን ከስኸተቶ ልታርመው አልቻልክም። ደግሞም አንድ ስው ካልመስለው በስነስራቶ የመተቸት መብት እንጂ ወያኒነት አይመስለኝም አንተ እንደምትለው ከሁነማ ስው መሁናችን ቀርቶ የፍብሪካ ውጤት አስመስልከን። ሐሳብ በሐሳብ መፋጨቱ አትጥላው ፣ ስውንም ከማምለክ የፖለቲካ አስተሳስብ መውታት አለብን። ለአንተም እንዲሁም ለልጅ ተክሊ መልካም አዲስ አመት እንዲሁን መልካም ምኞቲን እመኛለሁኝ።

  2. I thank the writer for his brilliant and educative comment, which in my opinion would serve as a constructive advice to ego-centrists of the likes of Tekle.

    I recall Tekle once remarked that the impending release of Birtukan Midekesa from prison would be a setback for the struggle against TPLF/ERDF regime and drew a flurry of anger from her numerous supporters working hard for her freedom. Is this man crazy or cruel?

  3. Ye Current Affairs Discussion Froum Dedeboch
    Ye Dr Berhanu Ashkeroch & Isayas Afweorki Amlakiwoch
    Tekle eunetun new yetenagerew
    Tekle Ende Enante Dr Berhanu yalew Hulu Amen bell aykebelem

  4. What is all these?wow!!!!,you call your self a fraind of Tekle?what kind of fraind are you?I agree with you that Tekle is spontaneous most of the time,and I don’t agree on some his comment on that article,we should not forget also he has substance in the same article.we the right to mistrust people like Jawar and Haji Nejib,look what Haji Nejib’s wife said,she was talking about Islamization of Ethiopia.is it not true?it is available on YouTube.thanks for technology.Who made Jawar Mohamed to role all over ESAT?he was the darling of diaspora poletics.who put him and OLF on the high horse Ethiopian poletics?it is Dr Birhanu.it is a matter of time.he will bring Jawar back again to Ethiopian Arena.Ethiopian poletics is hijacked by narrow nationalists and extremists.look ESAT,who are they serving these days?Ethiopians are being pushed out,shabia and OLF are marching in.my fraind we are watching carefully.
    I found your article very elementary and irrational,how can you call your self better than Tekle?it is total insult,I wonder also how the web master allow you to post the kind of character asasnation on their web site. I gues they are fun club members of G7.Tekle has the right to his opinion.you should not insulted in that manor.it was gross to say the list.

  5. I agree 100% with Derbeb Kefelgne Tekele you need to stay away from mic and computer keyboard your friend give you his advice I hope you will read this article before you do any thing.

  6. Hey mr writer please make ur statement short and brief this is too much
    By the way instade of criticizing his idea u insulted lije tekle that is not fair. Totally ur comment is to protecting somebody, so ur bodyguard for somebody

  7. Mr web master..
    You sanctioned my comment because I criticized your boss Birhanu Nega,yegeremal,eziam afena,ezihem afena,aye egna

  8. Mr web master..
    You sanctioned my comment because I criticized your boss Birhanu Nega,yegeremal,eziam afena,ezihem afena,aye egna.i will never visit your web site again.berta eski,yemecheh

  9. It is a big shame to insult others, this is a very rude way of talking about others. You should have put it in a better way, you can’t teach any one by writing this. You have to learn for your self you are talking nonsense if he is your long time friend you should have talk to him in person, I don’t think you are friends. We really are tired of this kind of stuff. Please try to be nice to each other to over throw weyane.

  10. Nice, that should be how this big boy needs to be addressed. He doesn’t deserve respect. He should know his level and capacity.

  11. Kiros,Don’t act like woyane,or don’t be woyane i know you don’t like Dr,Berhanu Nega because he is real Ethiopian anti woyane/Tplf.

  12. Wow that is harshe, he just express his opinion he don’t deserve this , ya we don’t need political analyst we have enough of those.we need leaders who get us to victory and freedom.

  13. for Buta Madingo
    u don’t have any idea, but u follow people and be bodyguard
    here is my qoestion for u
    1- what does it mean berhanu is real ethiopian?
    2-how do we know birhanu is anti woyane/tplf?
    3-why u follow people like berhanu
    Thanks

  14. This message for Kiros and others who are genune anti weyane force. Those oppostion forces who are working hard to remove the dictator weyane should be respected and we we should support them.we also should work wth them or doing the work on ourselves.Among those who are fighting to dismantel the dictator weyane bitterly is Dr Berhanu .Because of this the weyane put him in prison many times . 1. he was in prison with professor mesfin . 2.he was in prison wih kinjet for two years. 3. even though he is outside ethipia he is sentenced to death wtih the General Asaminw and others and again he is senteced with Eskinder Nega other political prisoners. This is not only he is explaing his stand on weyane many time on all gethering and meetings with his g7 movements.The ONE very imortant part he never speak AGAINST the oppostion forces .He is encourging every anti weyane movements to do thier owen parts in dismantling the Weyane Guglae peacfully or by arms from where ever place appropriate to each forces . So If you support and work with Dr berhanu 0r if you work with other forces who are spending thier time, money, energy and knowledge how can you be a bodyguard?.especially for Tekle you can comment but your comment must be reasonable. Dr berhanu suggested on religion is very important and eductive .This also the stand of g7. I encourage those who did not read to read it. It shows what to be done now and what is to be done in the future in ethiopia on all religion not only on muslim religion. Thank you

  15. For Tokchaw
    First of all I’m not criticized u .you better than Buta Madingo, because u explain for us how Dr. Berhanu is working hard on the struggle of freedom, I’m very positive with this, but my problem is the word real Ethiopian, and then don’t criticized Dr. berhanu. I mean weyane supporters said that don’t criticized Meles and G7 supporters said don’t criticized Berhanu, what is the difference between this two party. For me some of both party members are don’t know what they need, the only thing they knew is loving their leader, and what ever the leader said, he is wright. So we have to tell them those people to be better supporter, instead of bodygurd, otherwise they r dangerouse for their party too, like Kinijet supporter,especially the diaspora

    Thanks

Comments are closed.

Share