January 9, 2017
3 mins read

በሶስት ጠርዝ ጥቃት ለመሰንዘር የወረደው የኮማንድ ፓስት ትእዛዝ ተሰረዘ

የልዑል ዓለሜ ዘገባ
በጎንደር በተለዩ አካባቢዋች በሚንቀሳቀሱ የነፃነት ፋና ወጊ ሐይሎች ላይ ጥቃት ለመፈጸም ትእዛዝ ወርዶለት ካስለፍነው ወራት ጀምሮ የተንቀሳቀሰው ከልዩ ሐይል. ከሰሜን እዝ እግርኛና ከአየር ሐይል እንዲሁም ከሁለር ብረት ለበስ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦሮች የተውጣጣው የህወሀት ቅጥረኛ ሰራዊት ባለበት እንዲቆምና አዲስ ትእዛዝ እንዲጠብቅ ተደረገ::
ቀድሞ የወረደው ትእዝዝ እንዲነሳ የተደርገበት ምክንይት ወታድራዊ መርጅዋች በነጻንት ሀይሎች እጅ በመግብታቸው መሆኑን የገልፁት ምንጫችን በኮማንድ ፓስቱ የበላይ ትእዛዝ የምንቀሳቀሱት የህወሀት ሐይልች ወደ ሚላኩበት የጦር ቀጠና ከመድረሳቸው በፊት በእንቅስቃሴ ላይ የድንገተኛ ሽምቅ ጥቃት ሰለባ በመሆናቸውና ጉዳዩ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ መሆኑን የገለጹ ሲሆን::
የህወህት ወታድራዊ ደህንነት በአስቸኩዋይ መልእክቱ ለኮማንድ ፓስቱ ከዚህ በታች የቀረቡትን ምክንያቶች አስተላልፏል..
. የነጻነት ሐይላት በገጠራማው የጦር ቀጠና እካባቢ በሚኖር ህዝብ በመደገፉቸው
. በወያኔ የመከላከያ አመራሮች ወይም በውስጥ አርበኞች በመረጃ በመደገፋቸው
. በተደራጁ የጀርባ ንቅናቄ ሐይላት ህክምና. ራሽን. አልቂ ትጥቆች እና የመሳሰሉት የሽፋን ድጋፎች ስለሚደረግላቸው ነው
ይህ ሪፓርት የቀረበለት ኮማንድ ፖስት ተብዬው በበክሉ
የጎደሉ አባላቱን ለመተካት…
መረጃ ያወጣሉ ተብለው የተጠረጠሩ እመራሮችን ለመገምገም…
የሀይል ፍተሻና ድክመቶችን ለመፈተሽ እንዲሁም…
አዲስ የጥቃት ስትራተጂ ስልቶችን ለማውጣት…
እንደተገደደ ታማኝ ምንጫችን ለማረጋገጥ ተችሏል::
የህወሀት ኮማንድ ፓስት በሶርቃ በዳንሻ በኡማህ ጅር በዳባትና በኡመራ ዙሪያ ተደጋጋሚ ጥቃት እንደተፈፀመበት የሚታወቅ ሲሆን ዛሬም የስርአቱ ፀረ ሽምቅ ሀይል በኡመራ አካባቢ በጀግኖቹ ክርን እየተደቆሰ እንደሚገኝ ምንጫችን አክለው በመጥቀስ የነጻንት ሀይላቱ ፈጽመው ባለመዘናጋት ተጋድሎአቸው ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ በጥብቅ አሳስበዋል::
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

2 Comments

  1. The news it is canceled may be a strategy to make the patriot off guard. So take care do not believe what is said.

Comments are closed.

bahr dar 10
Previous Story

ደም እና አጥንት የተከፈለውም ሆነ እየተከፈለ ያለው፥ በነፃነት ለሚቋጨው ኢትዮጵያዊነት ነው። የቀደመ፤ ቀላል ስሌት

አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ 2 2
Next Story

ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ርእሳነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ የ2009 ዓ.ም የገና በአል መልእክት

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop