October 7, 2016
25 mins read

በዳያስፖራ ከትግራይ ተወላጆች የተሰጠ (3ኛ) መግለጫ

ህውሓት/ኢህአዴግ ቢሾፍቱ ላይ ባደረሰው አሰቃቂ እልቂት በጣም አዝነናል
የሽግግር መንግስት በአፋጣኝ ይቋቋም!

በዳያስፖራ ከትግራይ ተወላጆች የተሰጠ (3ኛ) መግለጫ

ባሳለፈነው እሁድ (22.01.2009) ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተሰባሰቡ ዜጎች በተገኙበት በቢሾፍቱ ከተማ በደማቅ ሁኔታ በመከበር ላይ በነበረው የኢሬቻ በዓል ላይ፣ ዜጎች በአፋኙ “መንግስት” ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ባዶ እጃቸውን አጣምረው በሰላማዊ መንገድ በማሰማታቸው ምክንያት፣ ሰብአዊነት በጎደለውና ጭካኔ በተሞላበት የህውሓት/ኢህአዴግ አሰቃቂ እርምጃ የብዙኃን ህይወት ተቀጥፏል። የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ም/ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ በቪኦኤ ቀርበው እንደገለፁት፣ የህውሓት/ኢህአዴግ ታጣቂዎች በፈፀሙት በዚህ አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ምክንያት 678 ዜጎች መሞታቸው ተረጋግጧል። ከ400 በላይ ሰዎች በሞትና በህይወት መካከል ይገኙ የነበረ ሲሆን ትክክለኛ የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይም ሊያሻቅብ እንደሚችል ይገመታል።
እኛ ስማችን ከታች የተዘረዘረው የትግራይ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን፣ ጭካኔ በተሞላበት በዚህ አረመኔያዊ ድርጊት በከፍተኛ ሁኔታ ማዘናችንን ለመግለፅ እንወዳለን። የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን ለመግለፅ ቃላት ያጥሩናል። ህውሓት/ኢህአዴግ የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነቱን ለማስጠበቅ ሲል በዜጎች ላይ ያለውን አያያዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ በመሄድ፣ ዛሬ ህዝብን የሚያስተዳድር መንግስት ሳይሆን ህዝብን የሚያሸብር ወንበዴ መሆኑን በተግባር ያስመሰከረበት ዘግናኝ እልቂት ለማየት በቅተናል። በተለይ ደግሞ ይህን የሚያደርገው ህውሓት፣ የተለያዩ የብሔር ትንኮሳዎችን እያራገበና ከመቼውም በላይ በትግራይ ህዝብ ስም እየነገደና ጥላቻን እየበተነ ባለበት በዚህ ወቅት በመሆኑ ሀዘናችንን የከበደ አድርጎታል።
ቀደም ሲል ባወጣነው የጋራ መግለጫ እንደጠቀስነው፣ ህውሓት/ኢህአዴግ ከስልጣኑ ወርዶ የሽግግር መንግስት ባገሪቱ ካልተመሰረተ፣ ስልጣን ላይ በሚቆይበት እያንዳንዱ ተጨማሪ ቀን በዜጎች ላይ የባሰ እልቂትን እያስከተለና የአገሪቱን ህልውና ይበልጥ አደጋ ላይ እየጣለ መዝለቁ አይቀሬ ነው። ህውሓት/ኢህአዴግ ከህዝብ ራሱን ነጥሎ በትምክህትና በጉልበት ረግጦ ለመግዛት የሚሞክረው አካሄድ መቼም ቢሆን ሊሳካለት እንደማይችል ተረድቶ የሽግግር መንግስት ለማቋቋም ቢሰራ ለሁሉም የሚበጅ ነውና በድጋሚ ለመምከርና ለመዘከር እንወዳለን።
ህውሓት/ኢህአዴግና የኢትዮጵያ ህዝብ የገቡበት ቅራኔ ከዚህ ብኋላ በሌላ በማንኛውም መንገድ ሊታረቅ የሚችል ቅራኔ ባለመሆኑ መፍትሔው የሽግግር መንግስት በመመስረት ህዝብ በነፃና ገለልተኛ ምርጫ ይሆነኛል የሚለውን ስርዓት እንዲመርጥ መንገድ ማመቻቸት ብቻና ብቻ ነው የሚለው እምነታችን አሁንም ፅኑ ነው።
ይህ እንዳለ ሆነ፣ ካለፈው ባህሪው ተነስተን ህውሓት/ኢህአዴግ በጎ ፈቃደኝነት ይኖረዋል ብለን ለማመን ስለምንቸገር፣ ይህን የማሳከት ሃላፊነቱና የዜግነት ግዴታው የተጣለው በመላው አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ላይ መሆኑን በፅኑ እናምናለን። በመሆኑም በመላ አገሪቱ ለነፃነቱ በጋራ እየተነሳ እንዳለው ህዝባችን፣ በተለያዩ የተቃውሚ ጎራ፣ የሲቪክ ተቋማት፣ የእምነት ተቋማት፣ እና የሙያ ማህበራት ስር የምንገኝ ኢትዮጵያውያን (በተለይም በመሪነት ደረጃ የተቀመጥን ዜጎች) ጊዜያዊ ልዩነታችንን ወደጎን ብለንና የጋራ መድረክ በማዘጋጀት ሁሉንም ያቀፈና ያሳተፈ የሽግግር መንግስት የመፍጠር ሂደት ከወዲሁ እንድንጀምር በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን።
ከዚህ በተጓዳኝ ግልፅ ለማድረግ የምንፈልገው አንድ ነገር አለ። ይኸውም ህውሓት በትግራይ ህዝብ ስም የሚነግደውና በትግራይ ህዝብ ስም ጥላቻ የሚነዛው አልበቃ ብሎት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችን በማታለል ከቤት ንበረታቸው እያፈነቀለ ወደ ትግራይ ለማጓጓዝ እንቅስቃሴ መጀመሩን ከታማኝ ምንጮች ለመረዳት ችለናል። ይህንን ሴራውን ለማሳካት በትግራይ ተወላጆች ላይ ሃላፊነት የጎደለው እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል ሁሉ ጥቆማዎች ደርሰውናል። ይህን የአቋም መግለጫ በምናዘጋጅበት ሰዓት አንዳንድ የትግራይ ተወላጆች ከኦሮሚያ ክልል መውጣት መጀመራቸውን አረጋግጠናል።
የትግራይ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን በህውሓት ፕሮፓጋንዳና ሽንገላ ተታለው ለዓመታት ጎጆ ቀልሰው ከኖሩበትና ጥረው ግረው ካፈሩት ቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው፣ ከኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸው በመነጠል አፋኙና ነፍሰ በላው የህውሓት ቡድን ባዘጋጀላቸው ወጥመድ እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ እንወዳለን። ዛሬ ለትግራይ ህዝብ ከህውሓት በላይ ሌላ ጠላት እንደሌለው እያንዳንዱ የትግራይ ተወላጅ ሊያውቀው ይገባል። በህውሓት ስር ያሉ ወሮበላዎች ለትግራይ ህዝብ ቀርቶ አብረው ለታገሉ ጓዶቻቸውና ለቤተሰቦቻቸውም ምህረት የማያውቁ አረመኔዎች መሆናቸውን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊገነዘብ ይገባል።
በሁሉም የአገሪቱ ክፍል የምትኖሩ የትግራይ ተወላጅ ወገኖቻችን ህውሓት ባዘጋጀላችሁ ወጥመድ ሳትገቡና የህውሓትን ህልም አሳክታችሁ ራሳችሁን መቋጫ ለሌለው ሰቆቃ ሳትዳርጉ በፊት፣ በያላችሁበት ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገናችሁ ጋር በጋራ በመቆም ለነፃነታችሁ እንድትታገሉ በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ሁሉም ነፃ ካልወጣ ማንም ነፃ ሊወጣ እንደማይችል ተገንዝበን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ጎን በጋራ በመቆም ለነፃነት የሚደረገውን ትግል በያለንበት እንድንቀላቀል በድጋሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
በአገሪቱ በሁሉም አቅጣጫ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፣ ለዘመናት በመካከላችሁ አብረዋችሁ የኖሩ የትግራይ ተወላጅ ወገኖቻችሁ ከማንኛውም ኃይል ሊደርስባቸው ከሚችል ጥቃት የመጠበቅ አደራ ተጥሎባችኋል። አብዛኛው የትግራይ ተወላጅ ዜጋ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወገኑ በአፈናና በጭቆና ስር የሚኖር ወንድማችሁ በመሆኑ፣ በተለይ ህውሓት ህልሙን ለማሳካት ሊፈፅምባቸው ከሚችል ደባ ለመጠበቅና ለነፃነት ትግሉ ከጎናችሁ ለማሰለፍ የዜግነት ግዴታችሁን እንደትወጡ እንማፀናለን።
በማጠቃለል በቢሾፍቱ በደረሰ አሰቃቂ እልቂት ልባችን የደማ መሆኑን በድጋሚ እየገለፅን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና በአጠቃላይ ሀዘን ላይ ለተቀመጠው ኢትዮጵያዊ ወገናቸው እግዚአብሔር መፅናናቱን እንዲሰጥልን፣ የሙታንን ነፍስ በሰላም እንዲያሳርፍልን እንመኛለን። እግዚአብሔር በምህረቱ ይጎብኘን፤ አገራችንንም ይባርክልን። አሜን!
የስም ዝርዝር
1. ህይወት ተሰማ
2. ሓረገወይኒ:ገ/ኢየሱስ
3. ሕሉፍ በርሀ
4. ሜሮን አብርሃ
5. ሲራክ ኣማረ
6. ስልጣን ኣለነ
7. በላቸው ለማ
8. በየነ ገብራይ
9. ብሩክ እንግዳ
10. ተስፋዬ መሓሪ
11. ተስፋይ ኣፅብሃ
12. ታደሰ በርሀ
13. ታደሰ ገብረእዝጊ
14. ነጋሲ በየነ
15. ናትናኤል ኣስመላሽ
16. አሰር አሉላ
17. አባይ ኪሮስ
18. ዶክተር ኣረጋዊ በርሀ
19. ኣብራሃ በላይ
20. ኣብርሃም ኀይለ
21. ኤልያስ በየነ
22. ኪዳነ ኃይሌ
23. ኪዳነማርያም ፀጋይ
24. ካሕሳይ በርሀ
25. ዘልኣለም ንርአ
26. ዮሃንስ በርሀ
27. ዮሴፍ ብርሃነ
28. ዮናስ ሓጎስ
29. ዮናስ መብራህቱ
30. ደስታ ኣየነው
31. ገብረኪዳን ዳዊት
32. ዶክተር ግደይ ኣሰፋ
33. ጥላሁን አረፈ
34. የማነ ምትኩ
35. ሸዋዬ ሽፈራው
36. ደረጀ ገ/ሂወት
ማሳሰቢያ!
ከኢትዮጵያ ውስጥ ሆነው መረጃ በማቀበልና አንዳንድ እንቅስቃሴዎችን በማስተባበር እየተባበሩን ያሉ የትግራይ ተወላጆች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን፣ በርካቶች ስማቸው እዚህ እንዲካተት የፈቀዱ ቢሆንም ሊደርስባቸው ከሚችል አደጋ ለመጠንቀቅ ስንል በሚስጥር ለመጠበቅ ተገደናል።
አስተባባሪዎቹ
ህውሓት/ኢህአዴግ አብ ቢሾፍቱ ብዘብፅሖ ህልቂት ብጣዕሚ
ጊዜያዊ ናይ ሽግግር መንግስት ብቅልጡፍ ክጣየሽ አለዎ!
ተጋሩ አሕዋትና ህውሓት አብ ዘዳለዎ መፃወዲያ ከይንአቱ ንጠንቀቕ
ካብ ተወለድቲ ትግራይ ዝተፈነወ 3ይ መግለፂ
መስከረም 27 2009
አብ ዝሓለፈ ሰንበት (መስከረም 22 2009) ካብ ዝተፈላለዩ ክፍሊታት ሀገርና ዝተአኻኸቡ ዜጋታት አብ ቢሾፍቱ ከተማ ብድምቀት የኽብሩ አብ ዝነበሩሉ በዓል ኢሬቻ፣ ኢትዮጵያውያን ንአምባገነን “መንግስቲ” ኢትዮጵያ ዘለዎም ተቓውሞ ብሰላማዊ መንገዲ ኢዶም አጣሚሮም ብምግላፆም ምኽንያት፣ ሰብአዊነት ብዝጎዶሎን ጭካነ ብዝተሞለኦን ናይ ህውሓት/ኢህአዴግ ስጉምቲ ብዙሓት ኢትዮጵያውያን መተካእታ ዘይብላ ሓንቲ ህይወቶም ስኢኖም እዮም። ም/ሊቀመንበር ኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ አይተ ሙላቱ ገመቹ ንቪኦኤ-አምሓርኛ ቀሪቦም ዝሀብዎ መረዳእታ ከምዝሕብሮ፣ ወታደራት ህውሓት/ኢህአዴግ ብዝፈፀምዎ አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ምኽንያት 678 ሰባት ከምዝሞቱ ተረጋጊፁ እዩ። ልዕሊ 400 ሰባት ድማ አብ መንጎ ሞትን ሀለዋትን ከምዝርከቡ ዝገለፁ እንትኾን፣ ትኽክለኛ ቑፅሪ ዝሞቱ ሰባት ክውስኽ ከምዝኽእል ይግመት።
ንሕና ሽምና አብ ታሕቲ ዝተጠቐሰ ተወለድቲ ትግራይ ኢትዮጵያውያን፣ በዚ ጭካነ ዝተመልኦ አረመኔያዊ ስጉምቲ ህውሓት/ኢህአዴግ አዚና ዝሓዘንና ምዃንና ክንገልፅ ንፈቱ። ዝተሰመዐና መሪር ሓዘን ንምግላፅ ቃላት ይሓፁርና እዮም። ህውሓት/ኢህአዴግ ምእንታን ፖለቲካዊን ኢኮኖሚያዊን ዕብለላኡ ክሕልው ክብል አብ ዜጋታት ዘለዎ አተሓሕዛ ካብ ጊዜ ናብ ጊዜ እናከፈአ ክኸይድ ብምግባር፣ ሎሚ ህዝቢ ዘመሓድር መንግስት ከይኾነስ ንህዝቢ ዘሸብር ሽፍታ ከምዝኾኒ ብተግባር ዘመስከረሉ ህልቂት ንምርአይ በቒዕና አለና። ብፍላይ ድማ ንዚ ዝገብር ዘሎ ህውሓት፣ ዝተፈላለዩ ብሔር መሰረት ዝገበሩ ቅርሕንቲ አብ መንጎ ህዝቢታት ኢትዮጵያ እናፈጠረን ብሽም ተጋሩ እንዳነገደን አብ ዘርከበሉ አብዚ ሕዚ እዋን ምዃኑ ሓዘንና ዝኸበደ ገይርዎ አሎ።
ቅድም ክብል ብአምሓርኛ አብዝፈነናዬ ናይ ሓባር መግለፂ ከምዝጠቐስናዮ፣ ህውሓት/ኢህአዴግ ካብ ስልጣኑ ወሪዱ ጊዜያዊ ናይ ሽግግር መንግስቲ ክጣየሽ እንተዘይገይሩ፣ አብ ስልጣን አብ ዝፀንሐሉ ሕድ ሕድ ዕለት ካብ ዝሓለፈ ዝገደደ ህልቂት አብ ህዝቢ እንዳብፅሐን ህልውና እታ ሀገር ናብ ዝኸፈአ ሓደጋ እንዳእተወን ከምዝኸይድ ዘጠራጥር አይኮነን። ህውሓት/ኢህአዴግ ካብ ህዝቢ ንዓርሱ ነፂሉ፣ ብትምክሕቲን በጉልበትን ረጊፁ ንምግዛእ ዝፍትኖ ዘሎ አካይዳ አብ ዝኾነ ይኹን እዋን ክሰምረሉ ከምዘይኽእል ተረዲኡ ጊዜያዊ ናይ ሽግግር መንግስቲ ንኸጣይሽ ደጊምና ንላቦ።
ህውሓት/ኢህአዴግ ምስ ህዝቢ ኢትዮጵያ አቲዎ ዘሎ ቅርሕንቲ ድሕሪ ሕዚ ብኻሊእ ብማንኛውም መንገዲ ክሽምገል ዘይኽእል ብምኻኑ፣ ብሕታዊ መፍትሒ እቲ አቲዎ ዘሎ ቅልውላው ጊዜያዊ ናይ ሽግግር መንግስቲ ብምጥያሽ ህዝቢ ኢትዮጵያ ብነፃ ምርጫ ዝመሰሎ ስርዓት ንኽተክል ኹነታት ምምችቻው ጥራሕ እዩ ዝብል እምነትና ፅኑዕ እዩ።
እዚ ኸምዘሎ ኾይኑ፣ ካብ ሕሉፍ ባህሪያት ህውሓት/ኢህአዴግ ተበጊስና ንዚ ንምፍፃም ድልውነትን ውፉይነትን ይህልዎ እዩ ኢልና ንምእማን ስለ እንፅገም፣ ንዚ ናይ ምፍፃም ሓላፊነት አብ ኹሉ ፈተዊ ሀገርን ተገዳሲን ወገን ዝተደብረየ ሓላፍነት ምዃኑ ንአምን። ስለዝኾነ ድማ አሰር እቲ አብ መላእ ሀገር ንናፅነቱ ዝቃለስ ዘሎ ህዝብና ተኸቲልና፣ አብ ዝተፈላለዩ ናይ ተቓዋሚ ፓርቲታት፣ ሲቪክ ማሕበራትን ናይ እምነት ትካላትን ብአባልነት ንርከብ ዜጋታት (ብፍላይ ድማ አብ አመራርሓ ዘለና አካላት) ጊዜያዊ አፈላላይና ንጎኒ ብምባል ተቐራሪብና ናይ ሓባር መድረኽ ብምድላው፣ ንኹሉ ዘሳተፈን ዝሓቖፈን ናይ ሽግግር መንግስቲ ንምፍጣር ምንቅስቓስ ንኽንገብር ፃዊዕትና ነቕርብ።
ምስ እዚ ተተሓዙ ብፍላይ ንተጋሩ አሕዋትና መተሓሳሰቢ ክንህብ ንፈቱ። ህውሓት/ኢህአዴግ ብተጋሩ ሽም ዝንግዶን ዘሰራጭዎ ዘሎ ፅልኢታትን ከይአኸሎ፣ አብ ዝተፈላልዩ ክፍሊታት ሀገርና ንዝርከቡ ተጋሩ አሕዋትና አታሊሉ ካብ ገዝኦምን ንብረቶምን በምፍንቓል ናብ ትግራይ ከጓዓዕዝ ምንቅስቓስ ከምዝጀመረ ካብ እሙናት ሰባት ሓበሬታ ረኺብና አለና። እዚ መግለፂ አብ ነዳልወሉ እዋን ሓደ ሓደ ተጋሩ አሕዋትና ካብ ዝተፈላለዩ ኸባቢታት ኦሮሚያ ምውፃእ ከምዝጀመሩ አረጋጊፅና አለና።
ተጋሩ አሕዋትና ብናይ ህውሓት ፕሮፓጋንዳን ተንኮል ተዓሺኹም ንዓመታት ጎጆ አጣይሽኹም ካብ ትነብሩሉን ብርሃፅኩም ፅዒርኩም ካብ ዘጥረኽምዎን ንብረትኹምን ተፈናቒልኹም፣ ካብ ኢትዮጵያዊ ወገንኹም ብምንፃል ህውሓት ናብ ዘዳለወልኩም መፃወዲያ ከይትአትዉ አጥቢቕና ክነጠንቅቐኩም ንፈቱ። ሎሚ ንህዝቢ ትግራይ ከብ ህውሓት ንላዕሊ ፀላኢ ከምዘይብሉ ተረዲእኹም ንማዕርነትን ናፅነትን አብ ዝግበር ዘሎ ቓልሲ ምስቲ ኻሊእ ኢትዮጵያዊ ወገንኹም ብምትሕብባር በብዘለኽምዎ ክትቃለሱ ፃዊዕትና ነቕርብ። ህውሓት ንህዝቢ ትግራይ ይትረፍ፣ ንመቓልስቶምን ንቤተሰቦምን ምሕረት ዘይፈልጡ አረመኔታትን ፈተውቲ ኸርሶምን ዝኾኑ ገበነኛታት ዝተሰግሰጉሉ ናይ ሸፋቱ ድርጅት ምኻኑ ተረዲእና ከይተገራህና ዓጢቕና ክንቃለሶም ኸምዘለና ክነተሓሳስብ ንፈቱ። እዚ እንድሕር ደአ ዘይኾይኑ፣ ህውሓት አ ብዘዳለዉልና መፃወዲያ አቲና ንመሪር ጭቆና መግዛእቲን ዓርስና አሕሊፍና ንምሀብ ከምዝፈቐድናን ብፍላይ ድማ መሕብኢ ገበናቶም ንምዃን ክምዝተስማዕማዕናን ክንፈልጦ ይግባእ።
አብ መላእ ሀገርና ዝርከቡ ካልኦት ወገናትና እውን ንዓመታት ሀገርና ኢሎም አብ መንጎኹም ንዝነብሩ ዘለዉ ተጋሩ ወገናትኹም ካብ ዝኾነ ይኹን ሓይሊ ክበፅሖም ካብ ዝኽእል መጥቃዕቲ ናይ ምሕላው ሓደራ ተዋሂብኩም አሎ። መብዛሕትኡ ትግራዋይ ከምቲ ኻሊእ ኢትዮጵያዊ ወገኑን ብዓፈና፣ ጭቆናን ድኽነትን ዝነብር ሓውኹም ስለዝኾነ፣ ብፍላይ ድማ ህውሓት ንቲ እከይ ሕልሙ ንምሳኽዕ ክብል ክወስደሎም ካብ ዝኽእል አረመኔያዊ ስጉምቲ ናይ ምሕላው ሕድሪ ተዋሂብኩም አሎ። አብ ጎንኹም አሰሊፍኩም ንናፅነቶም ብሓባር ንኽተቃልሱን ናይ ዜግነት ግዴታኹም ንክትዋፅኡን ንሓትት። ኹልና ነፃ ተዘይወፂና ማንም ነፃ ክወፅእ ስለዘይኽእል፣ ብሓባር ምቅላስ አገዳሲ ከምዝኾነ ክነስምረሉ ንፈቱ።
በምጥቕላል አብ ቢሾፍቱ ብዝበፅሐ ዘስካሕክሕ ህልቂት ልብና ኸምዝደመየ ዳግም እንዳገለፅና፣ አብ ሓዘን ንዝተቐመጡ ቤተሰቦም፣ ወለዶም፣ አዝማዶምን መሓዙቶምን ከምኡ’ውን አብ ሓዘን ንዝርኸቡ ኹሎም ኢትዮጵያዊ ወገናትና እግዚአብሄር ፅንዓት ንኽህቦምን ንምነ። ንቶም ብግፍዒ ዝሞቱ ወገናትና ‘ውን መንግስተ ሰማያት የዋርሰልና። አምላኽ ብምሕረቱ ይጎብነየና፣ ሀገርና ይባርኸልና። አሜን!
ሽም ዝርዝር
1. ህይወት ተሰማ
2. ሓረገወይኒ:ገ/ኢየሱስ
3. ሕሉፍ በርሀ
4. ሜሮን አብርሃ
5. ሲራክ ኣማረ
6. ስልጣን ኣለነ
7. በላቸው ለማ
8. በየነ ገብራይ
9. ብሩክ እንግዳ
10. ተስፋዬ መሓሪ
11. ተስፋይ ኣፅብሃ
12. ታደሰ በርሀ
13. ታደሰ ገብረእዝጊ
14. ነጋሲ በየነ
15. ናትናኤል ኣስመላሽ
16. አሰር አሉላ
17. አባይ ኪሮስ
18. ዶክተር ኣረጋዊ በርሀ
19. ኣብራሃ በላይ
20. ኣብርሃም ኀይለ
21. ኤልያስ በየነ
22. ኪዳነ ኃይሌ
23. ኪዳነማርያም ፀጋይ
24. ካሕሳይ በርሀ
25. ዘልኣለም ንርአ
26. ዮሃንስ በርሀ
27. ዮሴፍ ብርሃነ
28. ዮናስ ሓጎስ
29. ዮናስ መብራህቱ
30. ደስታ ኣየነው
31. ገብረኪዳን ዳዊት
32. ዶክተር ግደይ ኣሰፋ
33. ጥላሁን አረፈ
34. የማነ ምትኩ
35. ሸዋዬ ሽፈራው
36. ደረጀ ገ/ሂወት

3 Comments

  1. በማጠቃለል በቢሾፍቱ በደረሰ አሰቃቂ እልቂት ልባችን የደማ መሆኑን በድጋሚ እየገለፅን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና በአጠቃላይ ሀዘን ላይ ለተቀመጠው ኢትዮጵያዊ ወገናቸው እግዚአብሔር መፅናናቱን እንዲሰጥልን፣ የሙታንን ነፍስ በሰላም እንዲያሳርፍልን እንመኛለን። እግዚአብሔር በምህረቱ ይጎብኘን፤ አገራችንንም ይባርክልን። አሜን! it was a coordinated massacre not በደረሰ አሰቃቂ እልቂት:: you should call it massacre not እልቂት for woyane it was ‘ተመጣጣኝ እርምጃ’

    ኢሬቻ በምስጋና መንፈስን አድሰው የሚመለሱበት እንጂ በአፋኝ ስርዓት ወጥመድ ውስጥ ወድቀው ህይወትን የሚያጡበት ቦታ አልነበረም። እንደ ወጡ የሚቀሩበት ቦታም አይደለም። ቄጠማ የታቀፈ ምእመን እንጂ ታንክ እና ሄሊኮፕተር የታጠቀ ወራሪ ጦር የሚታደምበት ቦታም አልበረም። ወያኔ ምን ያህል ደመኛ ጠላታችን እንደሆነ ሌላ ተጨማሪ አስረጂ የምንሻ አይመስለኝም።

  2. The Christmas Tree became a symbol of Christ’s Birth Day celebration but actually it was the German Barberians who used to honor it as “secred” ad the gifts were for the evergreen tree which remained green in winter. NOw the gifts are for the Christian friends and family and the tree for Birth Day of the Savior let us make “Erecha” a thanksgiving symbol. And always celebrate peaceful protest and love

Comments are closed.

jawar1
Previous Story

ዋዜማ ራዲዮ በቅርቡ ያደርኩትን ንግግር ከ Contex ውጪ ወስዶ አነጋጋሪ አድርጎታል። (ከጃዋር መሐመድ)

Next Story

የኦሮሚያ የሽግግር መንግስት ? የኦሮሚያ መከላከያ ስራዊት በርግጥ ታስቧልን ? አቶ ጀዋር ሙሃመድ እና ፕሮፌሰር ህዝቄል ጋቢሳ በጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ ይጠየቃሉ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop