የመድረክ ጥሪ ለኢሕአዴግና ለተቃዋሚዎች


የመድረክ ጥሪ ለኢሕአዴግና ለተቃዋሚዎች
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታዩ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሔ ሳያገኙ ከቀጠሉ የሃገሪቱ ኅልውና ለአደጋ የተጋለጠ እንደሚሆን የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥምረቱ መድረክ ገለፀ።
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታዩ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሔ ሳያገኙ ከቀጠሉ የሃገሪቱ ኅልውና ለአደጋ የተጋለጠ እንደሚሆን የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥምረቱ መድረክ ገለፀ።

መድረክ ይህን የገለፀው የትናንት በስተያው ዕሁድ (ሐምሌ 28/2005 ዓ.ም) አዲስ አበባ ላይ ባካሄደው ሕዝባዊ ስብስባ ላይ ሲሆን ገዥውን ፓርቲ ኢህአዴግን ለተቃዋሚዎች የፖለቲካ መድረክ በመንፈግ፣ በንግዱ ውስጥ ገብቶ የአገሪቱን ምጣኔ ኃብት በማዛባት፣ ሕዝብን በማፈናቀል፣ በሃይማኖት ጉዳይ በመግባትና በፀረ-ሽብር ሕጉ አሳብቦ በማሰር ኮንኗል።

ከሰላማዊ ትግል የተለየ አማራጭ የያዙ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶችም ሰላማዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አድርጓል።

ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ መድረክ የሚያነሳቸውን ክሦች አይቀበልም፡፡

ይልቁንስ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በማስፈን ለኢትዮጵያ ሕዝብ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዳስገኘ ነው የሚናገረው።

ዝርዝሩን መለስካቸው አምኃ ከላከው ዘገባ ያድምጡ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:  የእሪታ ቀን -- እሁድ ሚያዝያ 26 ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት መነሻ ቀበና መድኃኔዓለም ከሚገኘው የአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት
Share