የመድረክ ጥሪ ለኢሕአዴግና ለተቃዋሚዎች

August 8, 2013


የመድረክ ጥሪ ለኢሕአዴግና ለተቃዋሚዎች
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታዩ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሔ ሳያገኙ ከቀጠሉ የሃገሪቱ ኅልውና ለአደጋ የተጋለጠ እንደሚሆን የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥምረቱ መድረክ ገለፀ።
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታዩ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ችግሮች መፍትሔ ሳያገኙ ከቀጠሉ የሃገሪቱ ኅልውና ለአደጋ የተጋለጠ እንደሚሆን የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥምረቱ መድረክ ገለፀ።

መድረክ ይህን የገለፀው የትናንት በስተያው ዕሁድ (ሐምሌ 28/2005 ዓ.ም) አዲስ አበባ ላይ ባካሄደው ሕዝባዊ ስብስባ ላይ ሲሆን ገዥውን ፓርቲ ኢህአዴግን ለተቃዋሚዎች የፖለቲካ መድረክ በመንፈግ፣ በንግዱ ውስጥ ገብቶ የአገሪቱን ምጣኔ ኃብት በማዛባት፣ ሕዝብን በማፈናቀል፣ በሃይማኖት ጉዳይ በመግባትና በፀረ-ሽብር ሕጉ አሳብቦ በማሰር ኮንኗል።

ከሰላማዊ ትግል የተለየ አማራጭ የያዙ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅቶችም ሰላማዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አድርጓል።

ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ መድረክ የሚያነሳቸውን ክሦች አይቀበልም፡፡

ይልቁንስ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በማስፈን ለኢትዮጵያ ሕዝብ የኢኮኖሚ ዕድገት እንዳስገኘ ነው የሚናገረው።

ዝርዝሩን መለስካቸው አምኃ ከላከው ዘገባ ያድምጡ፡፡

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop