መኢአድና አንድነትን ለማዋሐድ እየተሞከረ ነው

July 31, 2013

*ውህደቱ ከሰመረ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ
(መኢአፓ) የተባለ አዲስ ፓርቲ ሊፈጠር ይችላል

በዘሪሁን ሙሉጌታ

የመኢአድ ፕሬዚዳንትነቱን ለወጣት አስረክበው የወረዱት ኢንጂነር ኃይሉ ሻውል
መኢአድና አንድነትን ለማዋሐድ እየተሞከረ ነው 1
የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)ን ለማዋሐድ ተቋርጦ የነበረው ውይይት ለመጀመር እየተሞከረ ነው። የውህደቱን ሂደት የሚመሩ ከየፓርቲዎቹ ሦስት ሦስት አባላት ያሉበት የውህደት አመቻች ኮሚቴ እንዲቋቋም በመርህ ደረጃ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
ቀደም ሲል ሁለቱ ፓርቲዎች ለማዋሐድ አመራሮቹ የተለያዩ ጥረቶች ሲያደርጉ ቆይተዋል። ሌሎች ሀገር ወዳድ ምሁራን ጋር በመሆን በኢንጂነር ኃይሉ መኖሪያ ቤት ጨምሮ በተለያዩ ቦታዎች ምክክር ሲደረግ መቆየቱን አንድ የአንድነት ከፍተኛ አመራር በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል። ነገር ግን የሁለቱ ፓርቲዎች ድርድር አንድነት በመድረክ ውስጥ በመሳተፍና መኢአድ መድረክ በጎሳ የተደራጁ ፓርቲዎች ስብስብ በመሆኑ መኢአድ ከፓርቲዎቹ ጋር የፕሮግራም ልዩነት እንዳለው በመግለፁ ድርድሩ ሳይሳካ መቅረቱ ይታወቃል። በመቀጠልም ባለፉት ሁለት አመታት መኢአድ በውስጥ ችግር በመቆየቱ ሁለቱን ፓርቲዎች የመዋሐድ ሐሳቡ ሳይንቀሳቀስ ቆይቷል።
ሆኖም ሰሞኑን መኢአድ ጠቅላላ ጉባኤ በማካሄድ አዲስ ፕሬዝዳንት ከመረጠ በኋላ ተቋርጦ የነበረው ፓርቲዎቹን የማዋሐድ ኀሳብ እንደገና መንቀሳቀስ መጀመሩን ለሁለቱም ፓርቲዎች ቅርበት ያላቸው ምንጮች አረጋግጠዋል።
ቀደም ሲል ‘‘33ቱ ፓርቲዎች’’ ጋር አብሮ ለመስራት የነበረው ሂደትን ሰማያዊ ፓርቲ ለብቻው ሰላማዊ ሰልፍ በመጥራቱ በሌሎች ፓርቲዎች በኩል መጠነኛ ቅሬታ በመፍጠሩ አሁን ሁለቱን ፓርቲዎች በማዋሐድ ትግሉን ለማጠናከር ጥረት እየተደረገ መሆኑን ምንጫችን ጠቁሟል።
አንድ የመኢአድ ከፍተኛ አመራር ሁለቱ ፓርቲዎች በቅንነት ከተንቀሳቀሱ አዲስ ውህድ ፓርቲ መፍጠር እንደሚችሉና ከሁለት አመት በኋላ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ ጠንካራ ሆነው ሊወጡ እንደሚችሉ ገልፀዋል። ውህደቱ ከሰመረ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ (መኢአፓ) የተባለ አዲስና ጠንካራ፣ ፓርቲ መመስረት እንደሚቻልም ግምታቸውን ገልፀዋል።
አስራት ጣሴ
መኢአድና አንድነትን ለማዋሐድ እየተሞከረ ነው 2
የአንድነት ፓርቲ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስራት ጣሴ ጉዳዩን በተመለከተ ከሰንደቅ ጋዜጣ ጥያቄ ቀርቦላቸው ‘‘ጉዳዩን ማንም የነካካው የለም’’ ካሉ በኋላ በመርህ ደረጃ ፓርቲዎቹን ለመዋሐድ የተጀመረው ጥረት እንደሚቀጥል ግን ተስፋቸውን ገልፀዋል።
ይሁን እንጂ አቶ አስራት ‘‘ጉዳዩን የነካካው የለም’’ ቢሉም ሰሞኑን በመኢአድ ጽ/ቤት መገኘታቸውን በተመለከተ ተጠይቀው በቀጣይ 33ቱ ፓርቲዎች ስለሚያደርጉት እንቅስቃሴ ከመኢአድ አዲሱ አመራር ጋር ለመወያየትና አዲሱን የመኢአድ ፕሬዝዳንት እንኳን ደስ አለህ ከማለት ባለፈ በጉዳዩ ላይ በኮሚቴ ደረጃ ውይይት አለመጀመሩን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የመኢአድ አዲሱ ፕሬዝዳንት አቶ አበባው መሓሪ ከሰንደቅ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ አቶ አስራት ጣሴ በፓርቲው ጽ/ቤት ተገኝተው ሁለቱ ፓርቲዎች በሚዋሐዱበት ጉዳይ ጋር በተያያዘ ውይይት ማድረጋቸውን አረጋግጠዋል።n

ምንጭ፡ ሰንደቅ ጋዜጣ የረቡዕ ጁላይ 30 ቀን 2013

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop