ስለ ኮሎኔል ታደሰ ጥቂት ልበል፡ ከፍል1 በይታያል የሩቅሰው

ከፍል1
ይታያል የሩቅሰው

መነሻዬ ሰመረ ዓለሙ የተባሉ ሰው፡ ካቀረቡት ጽሁፍ መካከል፡ አንዱን በማንበቤ ስለተጠቃሹ ከማውቀው እውነት ጥቂት ቆንጥሪ
በሚከተሉት አርእዕስቶች በመክፈል፡ የነጠረውን ሀቅ እያነሳሁ አንድ ሁለት ለማለት ነው።

ስለዚህ

1/ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ፡ ምን ሰርቶ ነበር?

2/የመሰወሩ ምክናያቶችስ ምንና እነማን ናቸው?

3/እኛስ ስለ እሱ ምን ብለናል?

4/ወደፊትስ ምን ማለት አለብን?

የሚሉ ሃሳብና ጥያቄዎችን እያነሳሁ ባጭሩ ለመዳስ ልሞክር።

 ለዛሪ

1.1.ኮሎኔል ታደሰ ምን ሰርቶ ነበር፡

Colonel Tadesse Muluneh

ገና በለጋ እድሜው ዝነኛውን፡ የኢትዮጵያ አየር ሃይል የተቀላቀለው፡ ታደሰ ሙሉነህ በኮሌጁ የሚሰጠውን ትምህርት አጠናቅቆ፡ በምክትል፡ መቶ አለቅነት ማህረግ እንደተመረቀ ነበር፡ በሲያድባሪ የሚመራው የሶማሌ ተስፋፊ ጦር ኢትዮጵያን የወረረው፡ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ እንደሚያስታውሰው፡ ወቅቱ የሃይለስላሴ መንግስት፡ ወድቆ ደርግ ስልጣን የያዘበት ስለነበር ሀገራችን ለመከላከል የምታደርገውን እንቅስቃሴ፡ የሚደግፍላት ባልነበረበት ሁኔታላይ ስትሆን፡ ባንጻሩ ሶማልያ የረጅም ጊዜ የወረራ ዝግጅት ከማድረጓም በላይ ሶቬት እስካፍንጫዋ ያስታጠቀቻት በመሆኑ፡ በሁሉም ዘርፍ የእኛና የጠላት ሐይል አሰላልፍ፡ የሰማይና የመሪት ያክል፡ የተራራቀ ነበር ማለት ያስደፈራል።

ደርግ በአንድ በኩል ከምዕራባውያን መንግስታት መሳሪያ ለማግኘት፡ በሌላበኩል ወታደር መልምሎ በማሰልጠን ለውጊ ዝግጁ ለማድረግ፡ በሚሯሯጥበት ወቅት፡ የሶማሌ ታንክና ልዩ ልዩ ከባድ መሳሪያዎችን፡ የጫኑ በሺ የሚቆጠሩ፡ተሽከርካሪዎች ባይድዋ መድረሳቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ ይደርሰዋል፡ ይህ ሃይል ወንዙን ከተሻገረ፡ ከአንድ ሳምንት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ አዲስ አበባ ከመግባት የሚያግደው፡ ነገር እንደማይኖር ሰለሚገመት፡ ምንም እነኳን በተጠናከረ የአየር መቃወሚያና፡ እጅግ ዘመናዊ ተዋጊ አውሮፕላኖች የሚጠበቅ ቢሆንም፡ የተከፈለው ዋጋ ተከፍሎ ያ እንደጉንዳን የሚርመሰመስ ታንክና ከባድ መሳሪያ የጫነ መኪና ሳይሻገር፡ ድልድዩ መፍረስና ተመልሶ እስኪሰራ፡ ጥቂትም ቢሆን የዝግጅት ጊዜ መገኘት እንዳለበት፡ በባለስልጣናቱ ስለታመነ ለአየር ሃይላችን የውጊያ ትህዛዝ በመሰጠቱ፡ ግዳጁ ለም/ መቶ አለቃ ታደሰ ሙሉነህና ለበዛብህ ጴጥሮስ፡ በመሰጠቱ ወደ ቦታው ይከንፋሉ፡ በተጠንቀቅ ይጠባበቅ የነበረው የሶማሌ ወራሪም ገና በርቀት አየር መቃዎሚያውን ቢያስወነጭፍም፡ 2ቱ ጀግኖችና እውነተኛ የ ኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች፡በድፍረት ገስግሰው ተፈላጊውን ኢላማ መትተው ድልደዩን በማፍረስ፡ ፊታቸውን ወደሃገራቸው ሲያዞሩ ታደሰ ያበረው የነበረው ተዋጊ አውሮፕላን፡ በሶማሌ አየር መቃወሚያ በመመታቱ መንደድ ሲጀምር ወጣቱ ፓይለት በፓራሱት በመውረድ፡ በጉዞ ላየም ብዙ አስደናቂ ታሪኮችን እያከናወነ በጣም አስቸጋሪ ጉዞ በማድረግ፡ ኦጋዴን የሚገኜውን የወገን ጦር በመቀላቀሉ፡ የኢትዮጵያ ጀግና መዳሊያ የተሸለመ ከመሆኑም በላይ፡ከም/ መቶ አለቅነት አንድ ደረጃ በመዝለል የሻበልነት ማህረግ የተሰጠው፡ ጀግና ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ:  “ያቆሰለን ሳይጠፋ አናቀላፋ ”!  - ማላጂ

ኮሌኔል ታደሰ ሙሉነህ፡ ከዚያም በሗላ  በርካታ ሃገራዊ ግዳጆችን የተወጣና ጠቃሚ ቁም ነገሮችን ያከናወነ፣ በትምህርት ዝግጅቱም የ2ኛ ዲግሪውን በማዕረግ ያጠናቀቀ፡ ፍጹም ሐገር ወዳድ፣ቅንና እሩህ ሩህ፣ አርቆ አስተዋይ፡ ባጠቃላይ እንከን የለሽ ስብናን የተጎናጸፈ፡ ሲሆን ወያኔ ኢትዮጵያን ሲቆጣጠር፡ የጠላትን ፊት ላለማየት፡ ከድሪድዋ አውሮፕላን አስነስተው፡ ኬንያ ከገቡት የአየር ሃይል አብራሪዎቻችን አንዱ ነበር።

ከዚያም የሀገሩ ውድቀት የእግር እሳት የሆነበት፡ ኮሎኔል ታደሰ ኬንያ እየኖረ የፖለቲካ እንቅስቃሴ፡ ለማካሄድ ሲጀምር ሁኔታዎች ለህይወቱ አድገኛ ሆነው ስላገኛቸው፡ የተሻለ ከለላ ለማግኘት ባደረገው ጥረት የዑጋንዳ ባለስልጣናትን አነጋግሮ ባገኜው ይሁንታ መሰረት ወደዚያው ሄዶ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ እንዳለ፡ የወያኔና የሻብያ ግንኙነት፡ በመበላሽት ላይ እንደሆነና፡ ሻብያ ወያኔን በጦር ሃይል ለማበርከክ፡ ሚስጥራዊ ዝግጅት እያደረገ እንደሆነ፡ በአንድ የድሮ የኢትዮጵያ አየር ሃይል ባልደረባና ኤርትራ ከተገነጠለች በሗላ የኤርትራ ባለስልጣን በሆነ ግለሰብ፡ ይነግረውና፡ ኢትዮጵያን ከወያኔ ነጻ የማውጣት እቅዱን በኤርትራ በኩል ቢያደርግ እንደሚሻል ያግባባዋል፡፡

ኮሎኔል ታደሰም፡ የጠላቴ ጠላት የእኔ ወዳጄ ነው ወይንም ጅብን ለመውጋት አህያን መጠጋት እንዲሉ፡ ከስልት አንጻር ከዚህ የተሻለ ቦታ የለም በማለት፡ ጥያቄውን ተቀብሎ ወደኤርትራ በማምራት የሃገሪቱን መሪ በአካል አግኝቶ ሲያነጋግር፡ ሁኔታወች እስኪመቻቹልህ ድረስ፡ የኤርትራ ተዋጊጀት አብራሪዎችን ሲያሰለጥን እንዲቆይ፡ ትብብር ስለተጠየቀ እሽ ብሎ እያሰለጠነ  ለሁለት አመት ያህል እንደቆዬ፡ ወያኔ ሳያስበው፣ ሻብያ ግን ከ3አመት ባለነሰ ዝግጅት ጦርነቱ በሻብያ ተንኳሽነት ይፈነዳል።

ይህነን ተከትሎ ደግሞ በኬንያም፣ በሱዳንም፣ በሃገር ቤትም፡ ይንቀሳቀሱ የነበሩ፡ የወያኔ ተቃዋሚዎች ኤርትራ ገብተው፡ ከእዚያ እየተንደረደሩ ወያኔን መውጋት ይችሉ ዘንድ፡ ለኤርትራ መንግስት ጠያቄ አቅርበው ስለተፈቀደላቸው፡ ጠቅልለው እንደገቡ   ከኦነግና ከኦቭነግ በቀር፡ ሌሎቹ ግንባር ፈጥረው በአንድ ድርጅት ጥላ ስር በመሰባሰብ ለውጊያ እንዲዘጋጁ፡ በሻብያ መመሪያ ስለተሰጣቸው፣

ተጨማሪ ያንብቡ:  ዳግማዊ አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም፣ የት ናቸሁ?

1ኛ/በአቶ ዮሴፍ ያዘው፡ ይመራ የነበረው፡ የኢትዮጵያ ህዝቦች ዲሞክራ ግንባር፡

2ኛ/በአቶ ተስፋዬ ጌታቸው ይመራ የነበረው፡ የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ንቅናቄ፡

3ኛ/በአቶ ቱሗት ፖል ይመራ የነበረው፡ የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባር፡

4ኛ/በአቶ ጁማ እሩፋኤል ይመራ የነበረው፡ የቤንሻንጉል ንቅናቄ፡ በጋራ ባደረጉት የውህደት ጉባኤ ላይ ኮሉኔል ታደሰ ሙሉነህም ተካፋይ እንዲሆን ትደርጎ ስለነበር፡ ተዋህደው አዲሱን ድርጅት የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር የሚል ስያሜ በመስጠት የመጀመሪያ ጉባያቸውን ሲያጠናቅቁ፡

1ኛ/ ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህን፡ የግንባሩ ሊቀመንበር፡

2ኛ/ አቶ ቱሗት ፖልን፡ የግንባሩ ም/ሊቀመንበረ፡

3ኛ/አቶ ጁማ እሩፋኤልን የግንባሩ ጽሃፊ፡

4ኛ/አቶ ዮሴፍ ያዘውን የግንባሩ ድርጅት ጉዳይ፡

5ኛ/አቶ ተሰፋዬ ጌታቸውን የግንባሩ የእርዕዮታለም ጉዳይና ሌሎች 2 ሰወችን በማከል፡ 7 ያመራር አካላትን መርጠው ነበር። ኮሎኔል ታደሰ ያካበተውን የጠለቀ እውቀትና ሰፊ የስራ ልም፡ ሳይሰስት ተግባር ላይ ስላዋለው፡ አርበኛ ግንባር ባጭር ጊዜ በብዛትም ሆነ በጥራት ጠላቱን ወያኔን ብቻ ሳይሆን፡ አስተናጋጇን  የኤርትራን መንግስትም፡ ከማስፈራት ደረጃ ላይ ከመድረሱም በላይ፡ በዲፕሎማሲውም ዘርፍ ኮሎነል ታደሰ ወደ አውሮፓና አሜሪካን በመጓዝ፡ ኢትዮጵያውያንንና የውጭ ሀገር መንግስታትን፡ አነጋግሮ በማሳመን ሰፊ ድጋፍን ያስገኘ ሰው ነው።

ኮሎኔል ታደሰ ወደ አሜሪካን ባቀናበት ወቅት፡ሻብያን በጥርጣሪ አይን የሚያዩ፡ ኢትዮጵያውያን፡ ተሰባስበው መኝታ ክፍሉ ድረስ በመሄድ፡ በሻብያ ድጋፍ ኢትዮጵያ ነጻ ትወጣለች ብለህ አትድከም ይልቅ፡ ሻብያ እንደበግ አስብቶ ሳያርድህ፡ አሁን እንደወጣህ በእዚሁ ቅርና ልጆችህን አሳድግ፣ ሚስትህም፡ ኢትዮጵያም ያንተ ብቻ አይደለችም፡ ወ.ዘ.ተ. በማለት ቢለምኑት፡ የሰጣቸው መልስ፡ ሁሉም ኢዮትጵያ ለእኔብቻ አይደለችም፡ እያለ ጥሏት ከሸሸ የጎርቤት ሀገር ዜጋ መጥቶ ሊታደጋት ነውን? ባለቤቴም ሆኑ ልጆቸ አሜሪካን ገብተዋል፡ የተሻለ ኑሮ እየኖሩ ነው ወደፊትም ቢሆን እኔ ኖረሁም አልኖርሁም ይኖራሉ፡ ሌላው ኢትዮጵያዊ ግን ይህንን እድል ማግኘት አይደለም በሀገሩ ላይ በሰላም የመኖር መብቱ ተገፍፎ 2ኛ ዜጋ ሆኖ በመማቀቅ ላይ ከመሆኑም በቀር፡ ወያኔ ውሎ ካደረ ኢትዮጵያ የምትባል ሃአገር አትኖርም፡ እናም ቢሆን ከጥፋት አድናታለሁ፡ ካልሆነም ጥፋቷን ሳላይ ማንም ያጥፋኝ ማን ስከላከልላት እኔ ቀድሜያት፡ እጠፋለሁ፡ ሞት እንደሁ ፈራንም ደፈርን የማይቀር የተፈጥሮ እዳችን ነው። የሚል እንደነበር ካነጋገሩት ሰዎች መካከል አንዱ ሰሞኑን በቁጭት አጫውተውኛል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  ስለሟቹ ሕገ መንግሥታችን (ከአሁንገና ዓለማየሁ)

ለዛሪ በዚህ ላብቃ ቀሪውን በክፍል ሁለት ሳምንት እመለስበታለሁ፡ የሳምንት ሰው ይበለን፡

ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይታደጋት አሜን!!!!

                                                          

 

8 Comments

  1. I cant wait reading the 2nd part and I would love to read about tesfaye getachew, a true Ethiopian and my good friend at AAU,how he perish in Eritrea.

  2. thank u very much for relentless effort to secure the release of this great patriot. I believe next time u will display ur email so that true citizens create contact and share ideas.

  3. አቶ ይታያል የሩቅሰው!
    ስለጀግናው ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ የሰሩትን የመጀመሪያውን ክፍል ጽሑፍዎን አንብቤ ደስ ብሎኛል፤ ሆኖም በጠላት አየር መቃወሚያ ተመቶ በዣንጥላ ከወረደ በኋላ በእግር ተጉዞ ከወገን ጦር ጋር የተቀላቀለ ሳይሆን፤ በወቅቱ ሻምበል ታደሰ መሬት ላይ እንዳረፈ በአካባቢው የነበረው የጠላት ጦር እሱን ለመያዝ በመሯሯጥ ላይ እንዳለ በአካባቢው የፈልጎ ማዳን ጦር ይዛ ትጠባበቅ የነበረችው የአየር ኃይል ሄሊኮፕተር ከጠላት መንጋጋ ውስጥ መንጥቃ አውጥታዋለች። ለዝርዝሩ የቀድሞው አየር ኃይል ማህበር 20ኛ ዓመቱን ሲያከብር ባሳተመው “የኢትዮጵያ አየር ኃይል ትላንት እና ዛሬ” መጽሔት ላይ ኮሎኔል ለማ በየነ “በቀኝ ያዋለ ዕለት” በሚል ርዕስ ያሰፈሩትን ያንቡ።

  4. ሰላም የተከበሩ ወንድሜ አቶ የጎራው ስለሰጡት አስተያይትና፡ እርማት እጅግ በጣም አመሰግናለሁ፡ እርማቱንም ተቀብየዋለሁ፡ በተረፈ እኔ የምኖረው አውሮፓ ስለሆነ የጠቀሱትን መጽሄት የማግኘት እድሉ የለኝምና እባክዎ ወድ ወንድሜ ስለ ኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ የሚያወራ ካለው እሱን ብቻ በኢሜል zeledaw@hoo.con ይልኩልኝ ዘንድ ወንድማዊ ተብብርዎን የመለምነው በታላቅ አክብሮት ነው።

  5. Thank you for sharing first hand information of our hero who dedicated his life to mother land Ethiopia over luxurious life in USA. Please try to point out his place of origin where he is born and brought up before joining ethiopian Air Force. Thank you

  6. I respect Col. Tadesse for his courage and Ethiopiawinet. However, Shaebia and Woyane are one and the same, they are anti-Ethiopia. I feel sorry for him and disappear this way. I have no idea about military, but our forefathers fought the Italians and others inside Ethiopia. Is it impossible to fight woyane inside Ethiopia?
    I don’t believe anything good is coming from Shaebia. Woyane helped by Shaebia and what did Shaebia got:
    1. Woyane signed Eritrean independence.
    2. For seven years Shaebia used Ethiopian resource to build its army to fight Ethiopia.
    3. They divided Ethiopia along Ethnic lines so that Ethiopia will disintegrate. WOYANE’s top leadership is controld by Shaebia. Thus, Shaebia and Woyane are one and the same.
    4. Shaebia deported more than 300,000 Ethiopians who used to live in Eritrea (in 1991).
    5. Egypt, Syria, Iraq, Sudan, all arab countries helped Shaebia to distablized Ethiopia, Shaebia helped Woyane to distabilized Ethiopia, TPLF fabricated ANDEM, OPDO, SNNP to control Ethiopia.

    Solution: first we should know who are our enemies, let us be inclusive (instead of divisive as our enemies want us), let us united under common issues that will save Ethiopia.

  7. አቶ የሩቅ ሰው፤
    የጠየቁትን ለመላክ ያሰፈሩት የኢሜይል አድራሻ የማይቀበል/የማይሄድ መሆኑን እንዲያውቁት።

  8. ሰላም ወንድሜ አቶ የጎራው የሰጠሁወት ኢሜል ስህተት ነበረው አሁን ላስተካክለውናZeledaw@yahoo.com ብለው ቢልኩልኝ ትብብረዎን በአክብሮት እጠይቃለሁ አመሰግናለሁ።

Comments are closed.

Share