July 19, 2013
10 mins read

አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በ3 መርከብ ስሚንቶ አስጭነው በማስገባት የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

(ከኢየሩሳሌም አርአያ)
ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በሶስት መርከብ ስሚንቶ አስጭነው አገር ውስጥ በማስገባት ከፍተኛ የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ። በተከለከለ ፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ አገር ቤት የገባው ስሚንቶ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አዜብና ግብረአበሮቻቸው እንደዛቁበት ያረጋገጡት ምንጮቹ፣ አያይዘውም ጉዳዩ በደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ እጅ እንደገባ አስታውቀዋል። በሕገወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ በመመደብና አስፈላጊውን ትእዛዝ በመስጠት እንዲሁም የጥቅም ተካፋይ በመሆን ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት አዜብ መስፍን ከዚህ ድርጊታቸው በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ ተመስርቶ የነበረውን ክስ እንዲቋረጥ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ይህና ሌሎች ተያያዥ የወንጀል ድርጊቶችን የሚያስረዱ ማስረጃዎች በአቶ ጌታቸው እጅ እንደገቡ አረጋግጠዋል። አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር በኮንትሮባንድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው ወደ አገር ውስጥ ያስገቧቸው የህክምና መሳሪያዎች ተይዘው ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ ክሱ እንዲቋረጥ ያደረጉት አዜብ መሆናቸውን የገለፁት ምንጮቹ፣ በተለያዩ ጊዜያት የገቡና የነጋ ገ/እግዚያብሄር ንብረት የሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ያለቀረጥ እንዲገቡ በማድረግ አዜብ መተባበራቸውን አያይዘው ገልፀዋል። ጉዳዩም «ክስ በማቋረጥ..» በሚል በሰነድ ተደግፎና ከሌሎች መሰል ድርጊቶች ጋር ተያይዞ በታሳሪዎች ላይ ክስ የቀረበ ቢሆንም፣ ዋናው ተዋናይ ግን አዜብ ሳይጠየቁ መቅረታቸው አነጋጋሪ መሆኑን ምንጮቹ አልሸሸጉም። ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ አስተያየት የጠየኳቸው ታዋቂ የሆኑ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ባለሙያ ፥ « መንግስት ስለ ፍራንኮ ቫሉታ ሕግ አውጥቷል፤ ይህን በመተላለፍ ሶስት መርከብ ስሚንቶን የሚያክል ነገር በታሳሪዎቹ ብቻ ሊፈፀም አይችልም፤ ከዚህ ሕገወጥ ድርጊት በስተጀርባ ትልቅና ቁልፍ ስልጣን ያለው ሰው እጁ እንዳለበት ግልፅ ነው።» ብለዋል።
በተያያዘም ስለ ነጋ ገ/እግዚያብሄርና ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ የጀርባ ታሪክ በተመለከተ ምንጮቹ ተከታዩን መረጃ አስቀምጠዋል፤ “ ሕወሐት/ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ የአቶ ነጋ ስራ የመኪና ድለላና ኮረዶችን ከባለስልጣናት ጋር የማገናኘት የድለላ ተግባር ላይ ተሰማርቶ እንደነበረ ይገልፃሉ። በተለይ ሴቶችን እየመረጠ ለበርካታ የገዢው ሹማምንት ለወሲብ ከማቅረብ ጎን ለጎን የሕወሐት ቁልፍ ባለስልጣናትን በእጁ የማስገባት አጋጣሚ ፈጥሮለታል ፥ ይላሉ ምንጮቹ። ከባዶ ተነስቶ ሚሊየነር የሆነበት ምስጢሩ አዜብ መስፍን መሆናቸውን ያሰምሩበታል። ለዚህም «ነፃ ትሬዲንግ፣ ባሰፋና…» ሌሎች ከፍተኛ የቢዝነስ ተቋማቱና በሕገወጥ የዘረፋ ተግባር በድፍረት ተሰማርቶ መቆየቱን ከሞላ ጎደል ይጠቅሳሉ። በባለስልጣናቱ ተረማምዶ ከአዜብ ጋር በፈጠረው <ልዩ ቁርኝት> የተገኘ ሃብት እንደሆነ ይገልፃሉ። ከአዜብ ጋር በማሌዢያና ለንደን የፈፀሟቸው አስነዋሪ ተግባራት የሚያሳዩ የምስል ማስረጃዎች በደህንነት ሃላፊው እጅ እንደገቡ የጠቆሙት ምንጮቹ፣ የሁለቱን ግንኙነት በተመለከተ አብዛኛው የሕወሐት አመራር ጠንቅቆ እንደሚያውቀው አስታውቀዋል። አቶ ነጋ በቁጥጥር ስር ሲውሉ ማመን ተስኗቸው ከማንገራገራቸው ባሻገር፥ «..ለአዜብ ስልክ እንድደውል ፍቀዱልኝ?» በማለት መማፀናቸውንና ደህንነቶቹ እንዳልተቀበሏቸው ምንጮቹ አመልክተዋል። በሌላም በኩል ከአዜብ ጋር ተመሳሳይ <ግንኙነት> ያላቸው ሌሎች ሁለት ባለሃብቶች፥ አንዱ 40 ሚሊዮን የፈጀ ባለስድስት ፎቅ የቢዝነስ ተቋም (ቦሌ ከሜጋ አጠገብ) አዜብ በለገሱት ገንዘብ እንዲገነባ ሲደረግ፣ ከዚህ ግለሰብ ጋር በተደጋጋሚ በዱባይ በውቂያኖስ ላይ በተገነባውና የቱጃሩ አልወሊድ ቢንጣለል ንብረት በሆነው “ኪንግደም” ባለ4 ኮከብ እጅግ ዘመናዊ ሆቴል እንደተገናኙ፣ እንዲሁም ሌላኛው የአንድ ቢሊየን ብር ባለሃብት ሆኖ ከፍተኛ ደረጃ እንዲደርስ አዜብ ማድረጋቸውን ምንጮቹ አጋልጠዋል።
የአቶ ገ/ዋህድ ማንነት በተመለከተ ምንጮቹ ይህን ይላሉ፤ « ገ/ዋህድ የኢሰፓ አባል ሆኖ በአስመራ እስከ 1982ዓ.ም ያገለግል ነበር። በዚሁ አመት መጨረሻ በራማ በኩል አድርጎ ሕወሐትን ተቀላቀለ። በወቅቱ በመቀሌ እንዲቋቋም በተደረገውና የቀድሞ የደርግ ከፍተኛ መኮንኖች (ምርኮኛ) የተካተቱበት <ኢዴመአን> የተባለ ድርጅት መስራች አባል ነበር – ገ/ዋህድ። በ1983 ዓ.ም የሁለት ሳምንት ወታደራዊ ስልጠና ወይም በድርጅቱ አጠራር “ተአለም” ከወሰደ በኋላ በአጋጣሚ ፓርቲው መላ አገሪቱን እንደተቆጣጠረ ምንጮቹ ያመለክታሉ። በሲቪል ሰርቪስ አልፎ ደቡብን ከጀርባ እንዲመሩ ከተመደቡት አቶ ቢተው በላይ ጋር በአዋሳ ተመደበ። በ1993ዓ.ም በተፈጠረው የፓርቲው መሰንጠቅ አመቺ አጋጣሚ የተፈጠረለት ገ/ዋህድ የክልሉን ፕ/ት አቶ አባተ ኪሾን፣ ቢተው በላይና ሌሎችም እንዲታሰሩ በማድረግ ከፍተኛ ሚና ተጫወተ። ለዚህ ታማኝነቱ የላቀ ቦታ በመለስ ማግኘት እንደቻለና ከዛ በኋላ በየቀኑ ከአዜብና መለስ ጋር በስልክ ይገናኝ እንደነበረ በፈለገው ጊዜ ቤተመንግስት ይገባና ይወጣ እንደነበረ ምንጮቹ አረጋግጠዋል። በአዜብ መልካም ፈቃድ በጉምሩክ ወሳኝ ስልጣን እንዲጨብጥ መደረጉንም አክለው ገልፀዋል። ከአዜብና ሸሪኮቻቸው ጋር በመነጋገርና በመመሳጠር ስሚንቶና ሌሎች ቁሳቁሶች በህገወጥ መንገድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው አገር ቤት እንዲገቡ በማድረግ ከፍተኛ ሚና የተጫወተው ገ/ዋህድ፣ በሚሊዮን የሚገመት ሃብት ከዘረፋው እንዳተረፈም ተመልክቷል። ባለቤቱ ኮ/ል ሃይማኖትም እንዲሁ አዜብ በሚመሩት የሴቶችና ፀረ-ኤድስ ተቋም በምክትል ሃላፊነት እንዲመደቡና በየአመቱ ከአሜሪካ ብቻ እስከ 240 ሚሊዮን ዶላር በእርዳታ መልክ የሚገኘውን ገንዘብ በግልፅ በመዝረፍ ተባባሪ ሆነው መቆየታቸውን ምንጮቹ አስታውቀዋል።

12 Comments

  1. This guy seems to have the master of few facts, but hell of hearsays. his articles are good for psycholgical satisfaction of the diaspora tigrai haters. Otherwise, I never saw him substanciating his reports other than saying everything is in the hands of the security chief.

    Poor man! That is you would survive.

  2. One time one of the then political cadre of the Melaw Ethiopia Socialist Movement party ( long time ago) in Harar town said ” Ajaebe new yeEthiopia Abyot.” Now, I am also saying Ajaibe new ye woyane abyot and neger. Really, amazing and heart breaking news of mama Ethiopia. OoooooH! Besemish sinte gifie, bedel, mizbera, injustice, and other bad evil acts have done by the monster WOYANE.

  3. What is new..? Azeb is not going to enjoy the money she stole from poor people.
    Look what has happened to her husband super thief Meles,. Who robbed so much money. Azeb or Negan and other dont have no peace in their heart.They don;t sleep peacefully at nite God will punish them dearly.

  4. Dear Mussey.G- It is rather clear that your main concern is the emotional pampering of Tigrai’s than the entire interest of Ethiopia. Time after time, the author with his unique eloquence has gallantly shattered the high crime of Woyane Thugs. Millions of Ethiopians consider him as our own and unparalleled hero who championed the national interest of our sacred land than a self-possessed ethnic Mafias whose days in the helm are now truly numbered.

  5. wushetam feri hula,..chaka ende AZERB gebana tagel ….enkuwan genzeb yenanetenem sega tebela …tule tula hula.

    • Hello Mr. / Madame BMW,

      She was not in the forest. That is false story. She was a KOMARITE ( Yebuna bete ashashch) If you are understanding this Amharic word properly.

  6. BMW what are you taking about? Doesn’t mean any thing going to Chaka. Chaka yegeba hulu ager yezref yalewu manewu tekem lemagnet kehone what are you waiting for they are your good friend you are right she is eating the people live like her devil husband soon she will follow him.

  7. Respected Bertu,
    That is not my interest. I am just asking him to have his evidence in his hand rather keeping it in the hands of the security chief. I have been folowing his articles since the last 10 or some years ago. He seems to have unique ability of approaching many people, but most of them, I think are ordinary x-fighters. He also has the ability of writing every gossip he heard but his problem is in filtering the grain from straw. He was telling as that TPLF was divided into 3 cracks and that it was in its free falling. Such stories might have temporarily satisified the ego of Tigrai haters such as you. I am asking the writer to have at least few scanned documents that support his articles. Once in every month he has been releasing his “neTela zema”. I wish I see better documents.Isn’t it boring to hear that all his evidences are in the hands of the security chief.

    • If you only knew, it will make you ponder if I could be a “Tigrai Hater”. To many of Ethiopians Woyane does not mean the people of Tigrai. Period.

      In the presupposition to determine who represents the immortal threat for the existential of Ethiopia, one will consistently and clearly arrives whom to object in the face of such mortal danger. Accepting the infinitely variable style of struggle against Ethiopia’s apartheid developed by the nation killers known as “TPLF”, one needs to prioritize and refrain from criticizing the broad style of contribution, unless it is deemed to be counter measure in its attempt to save the nation. We need to learn from the wisdom and tolerance of the Pan African struggle against South African Apartheid which involved many stripes of allegiances but who all singularly remained to be an eternal enemy of that evil system.

      Historically, many of the material evidence to prosecute war crimes against the Third Reich during the Nuremberg Trial indeed were forthcoming from the inner core members of the system itself. That is why the chronicle documentation of Eyerusalem Araya (although he has never been a member of Woyane) is an invaluable contribution to bring justice in the final chapter of this dark period for our nation. While Woyane’s Mafias are busy in their unrelenting destruction of the country, I question the validity of any criticism directed to anyone who clearly paid the price for standing for what is right. If you are among the overwhelming Ethiopians struggling for liberation (I hope you are), I suggest your criticism of the authors writing style should be subjected to a placid PH test clearly disavowing that you are in no way supporting Ethiopia’s Enemy at the same time.

      May God Save Ethiopia, Amen!
      Bertu

  8. Nega owned only 2 Fiat D urban taxis and he was the one who gives rides to Sibhat Nega(Aboy) whenever he secretly comes to Addis for espionage during the Derg regime.So it is for his favour that he was made to be a multi millionnaire from ashes.

  9. This is a woman that does not deserve one iota of respect!! She is a dead woman while she lives! She is under a total control of demonic forces! No person in his right man will do the crime she has committed! She is a bond slave of Satan himself fulfilling his will; adding to the misery of our people!
    Rest assured, that this cursed woman also has an appointed time, when the God of heaven will say ” ENOUGH IS ENOUGH!!”
    Listen to me: Every Weyane (the curses of the nation) has passed the point of no return and they are beyond the reach of pardon and forgiveness (earthly or heavenly).
    One by one they will join that beast Zenawi, in Hell where right at this moment he is crying for a drop of water to cool his tongue!!!
    Man, the Weyanes practiced deceit all their lives, resisted the truth, and in that way of life their hearts got darkened!! and deep down they know they have missed the truth, but they will never have the change of heart to repent and do right and that is the kind of curse they are in!!!
    Azeb!! It won’t pay to serve the devil; by now you know that very well !! But there is no room for repentance for you even if you try to seek it with tears from now on until you die!! I wouldn’t want to be in your shoe a fraction of second !!!

    The God of heaven shall remove (Weyane the curse of the nation) and shall heal the land in His time and shall wipe the tears from our eyes! But until then the struggle must continue in every way!!!!

Comments are closed.

Previous Story

ትኩረቱ ወደ ጀግናዉ አጼ ዮሐንስ ከተማ – መቀሌ !

Next Story

አሸባሪዉ ኢህአዴግና የፀረሽብር ህጉ መወገድ አለባቸዉ

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop