July 9, 2013
5 mins read

ለጠ/ሚ ኃይለማሪያም ደሳለኝ: በመላ ኢትዮጵያ በአባሎቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለውን ህገ ወጥ እስርና እንግልት በተመለከተ

UDJ Images
  አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)             
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
 
ቁጥር፡ አንድነት/694/2ዐዐ5
    ቀን፡ 01/11/2ዐዐ5 ዓም

ለጠ/ሚ ኃይለማሪያም ደሳለኝ

     አዲስ አበባ

ጉዳዩ፡- በመላ ኢትዮጵያ በአባሎቻችን ላይ እየተፈፀመ ያለውን ህገ ወጥ እስርና እንግልት በተመለከተ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩና የህግ የበላይነት እንዲጠበቅ ህገ መንግሥታዊ መብቱን በመጠቀም በሠላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ ፓርቲያችን የፖለቲካ ስርዓቱ አካል እንደመሆኑ በሀገራችን በሚደረገው የዴሞክራሲ ግንባታ ሂደት የበኩሉን አስተዋፅኦ በማድረግ ላይ ነው፡፡ በዚህም መሠረት የሦስት ወር ህዝባዊ ንቅናቄ እቅድ በማውጣት በመላ ኢትዮጵያ የሚካሄድ ፍፁም ሠላማዊ የሆነ የተቃውሞ እንቅስቃሴ መርሃ-ግብር ይፋ አድርጓል፡፡

ይህ ህዝባዊ ንቅናቄያችን የቅስቀሳ ወረቀት መበተን፣ ፔቲሽን በማስፈረም፣ ህዝባዊ ስብሰባ በማካሄድና ሠላማዊ ሠልፍ በማድረግ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ በዚህ ሠላማዊ እንቅስቃሴያችን ላይ ግን ፍፁም ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ አባሎቻችን በአዲስ አባና ከአዲስ አበባ ውጭ እየታሰሩ ይገኛሉ፡፡ የድርጅታቸውን ወረቀት ስላሰራጩ ብቻ የታሰሩ አባሎቻችንም በርካታ ናቸው፡፡ ለአብነት ያህል በሰሜን ጎንደር ዞን በምዕራብ አርማጭሆ አብርሃ ጅራ ከተማ የፓርቲያችን አባላት የሆኑት አቶ አለልኝ አባይ፣ አቶ እንግዳው ዋኘው፣ አቶ አብርሃም ልጃለምና አቶ አንጋው ተገኝ የፓርቲውን የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ለምን በተናችሁ ተብለው ከሰኔ 22 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ እንዲሁም በጎንደር ከተማ አቶ ማሩ አሻገረ ከሰኔ 26 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ፣ አቶ አምደማሪያም እዝራ እና አቶ ስማቸው ዝምቤ ከሰኔ 25 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ ናቸው፡፡ እንዲሁም በወገራ አቶ ጀጃው ቡላዴ ሰኔ 25 ቀን 2005 ዓ.ም ታስሮ ተለቋል፡፡ አቶ ጋሻው ዘውዱ ላይ ጥይት በመተኮስ የመግደል ሙከራ የተደረገ ሲሆን ሮጦ ለማምለጥ ችሏል፡፡ በአልፋ ጣቁሳ ወረዳ መምህር አዋጁ ስዩም ከሰኔ 26 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ ሲሆን ሁሉም የታሰሩት ለምን ቀሰቀሳችሁና ወረቀት አሰራጫችሁ በሚል ነው፡፡ በተመሳሳይም በአዲስ አበባ አቶ ሙሉጌታ ተፈራ ፔቲሽን በማስፈረም እንቅስቃሴ ላይ እያሉ ሰኔ 30 ቀን 2005 ዓ.ም በህገ-ወጥ መንገድ ታስረው ይገኛሉ፡፡

ስለዚህ ይሄ ህገ-ወጥ እስር በአስቸኳይ እንዲቆም እየጠየቅን የታሰሩትም በአስቸኳይ እንዲፈቱ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

ከሠላምታ ጋር

 

       ግልባጭ                                                                                   ነጋሶ ጊዳዳ (ዶ/ር)

ሊቀመንበር

  • ለኢፊድሪ ፕሬዘዳንት
  • ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት
  • ለፌዴሬሽን ም/ቤት
  • ለፌደራል ፖሊስ
  • ለአዲስ አበባ ፖሊስ
  • ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን
  • ለሰብዓዊ መብት ጉዳይ
  • ለእንባ ተባቂ ተቋም
  • ለአማራ ክልል መስተዳድር
  • ለሰሜን ጎንደር ዞን
  • በአዲስ አበባ ለሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ
  • ለመንግስትና የግል ሚዲያዎች

 

3 Comments

  1. Dr. Negasso, do you you think Hailemariam has the power and authority to release anyone from prison? Don’t you remember the power and authority yourself had when you were the Woyane president few years ago?

  2. በጣም የሚያሳዝን እና የሚያስቅ ማመልከቻ ነው። መቸ ነው ለወያኔ እንደዚህ አይነት ማመልከቻ ጽፋችሁ መልስ የተሰጣችሁ? እባካችሁ 23 ዓመት ሕዝብ አታታልሉ ይብቃቸው ድል ያለመሰዋትነት አይገኝም ጭራቁ መለስ ዚናዊ ደጋግሞ ደጋግሞ ቤተመንግስት ከፈለጋችሁ እኛ የከፈልነውን መሰዋትነት ከፍላችሁ መያዝ ትችላላችሁ ብሎ ነግሮችሆዋል ፈረሱም ይሄው ሚዳውም ይሄው ብሎል። አቅሙና ሞራሉ ካላችሁ መስዎትነት ከፍላችሁ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከቅኝ ግዛት አትርፉት ካልሆነ ግን ልፍለፋችሁ ሰልችቶናል በመግለጫ ብዛት ለውጥ አይመጣም (ለምን ከግብጽ፣ ከቱኒዚያ ፣ ከየመን ፤ ከሊቢያ ትምህርት አንማርም ) የጠቀስኮቸው ሃገሮች የኢኮኖሚ ችግር የለባቸውም ህዝባቸው በልቶ ጠጥቶ ይኖር ነበር የምግብ ዋስትና የተረጋግጠባቸው ናቸው ግን ህዝቡ ነጻነት እና ዲሞክራሲ አሁን ባለንበት ዘምን እንደማንኛውም ቤዚክ ኒድስ አድርጎ በመቁጠሩ ለዲሞክራሲ ሲል ከፍተኛ መሰዋትነት ከፍሎል እየከፈለም ነው። እና በርሃብ ለሚገረፍ ሕዝብ ሞት ምኑነው የኢትዮጵያ ሕዝብ በቁሙ የሞተ ህዝብ ነው (በእውነቱ በሃኛው ክፍለዘምን የመጭረሻ ድህነት እና ሆላ ቀርነት ያለባት ሃገር ኢትዮጵያ ናት ) ታዲያ ይህን ነገር ለማስወገድ መስዋትንት የግድ ነው። ምንም 30 ዶክተር ተስብስቦ ከበርሃ የሚጣን አውሬ በወሬና በመግለጫ ሊያሽንፍ አይችልም በሃይል ካልሆነ።

Comments are closed.

diriba kuma
Previous Story

አቶ ኩማ ደመቅሳ በአቶ ድሪባ ኩማ ተተኩ

Next Story

ይድረስ ለኔልሰን ራህላሂላ ማንዴላ!

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop