የአውራምባ ታይምሱ ዳዊት ከበደ በዋሽንግተን ዲሲ ከግርማ ብሩና ከሌሎች ባለስልጣናት ጋር ተወያየ

July 9, 2013

(ዘ-ሐበሻ)የአውራምባ ታይምሱ ዳዊት ከበደ ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከአቶ ግርማ ብሩና ከሌሎች የኤምባሲው ሃላፊዎች ጋር ረጅም ሰዓት የፈጀ ውይይት ማድረጉን ከኤምባሲ አከባቢ የተገኘ መረጃ አጋለጠ።

የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች እንዳጋለጡት ዛሬ ጁላይ 8 ከቀኑ 4pm ጀምሮ ዳዊት በኤምባሲው ቅጥር ግቢ ተገኝቶ ውይይት ያደረገው ስለምን እንደነበረ ባይታወቅም በድምጻዊ ሰለሞን ተካልኝ ምትክ ወያኔ ለመክፈት ላቀደው ሬዲዮ እንዲያዘጋጅ ሊሆን እንደሚችል የኤምባሲው ምንጭ ያለውን ግምት ገልጿል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይም የገዢውን ፓርቲ የሚያስደስቱ ቪድዮችን በመልቀቅ ከትግራይ ኦንላይን እና ከአይጋ ፎረም የማይተናነስ ገዢውን ፓርቲ የሚያስደስቱ ሥራዎችን እየሰራ ነው በሚል የሚተቸው ዳዊት ከበደ በኢትዮጵያ ኢምባሲ ከአቶ ግርማ ብሩ ጋር ከመገናኘቱ አስቀድሞ በቅርብ ወደ አሜሪካ ለአባይ ግድብ ጉዳይ መጥተው ያልተሳካ የገንዘብ ማሰባሰብ ካካሄዱት የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴዎሮስ አድሃኖም ጋርም በስልክ መገናኘቱን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል።

የአውራምባ ታይምሱ ዳዊት ከበደ በዲያስፖራው የሚገኙ የነፃው ፕሬስ ሚዲያዎችን በማጥቃት እየተወነጀለ እንደሚገኝ በተለያዩ የማህበራዊ ድረገጾች ከሚሰጡ አስተያየቶች መረዳት ተችሏል።

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop