July 2, 2013
4 mins read

አቶ ታምራት በንግድ ተሰማሩ፤ ቢተው ስልጣን ያዙ

tamerat layene
አቶ ታምራት ላይኔም ከብርሃኔ አበራ ቤተሰብ ጋር ይዛመዳሉ

አቶ ታምራት ላይኔም ከብርሃኔ አበራ ቤተሰብ ጋር ይዛመዳሉ
አቶ ታምራት በንግድ ተሰማሩ፤ ቢተው ስልጣን ያዙ 1
አቶ ታምራት በንግድ ተሰማሩ፤ ቢተው ስልጣን ያዙ
( ከኢየሩሳሌም አርአያ)
በአሜሪካ ዴንቨር ከተማ ከቤተሰባቸው ጋር የሚኖሩት አቶ ታምራት ላይኔ የጋዝ እስቴሽን በመክፈት በንግድ ስራ መሰማራታቸውን ምንጮች ገለፁ። በሙስና ወንጀል ተከሰው ለአስራ ሁለት አመት ታስረው የወጡት አቶ ታምራት ከተፈቱ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ፥ አማኝ ሆነው እንደሚቀጥሉና ነገር ግን በማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከማንም ፖለቲካ ድርጅት ጋር ሳይወግኑ ለአገር ይጠቅማል የሚሉትን ሃሳብ እንደሚያካፍሉ፣ መፅሃፍ እንደሚያዘጋጁ…ገልፀው እንደነበር ያስታወሱት እነዚህ ወገኖች፣ ታምራት ያንን ቢናገሩም በቃላቸው ግን እንዳልተገኙ አስረድተዋል። « የኢየሱስ አገልጋይ ሆኜ እኖራለሁ» ያሉት ታምራት አሁን ወደ ንግድ አለም መግባታቸው እንዳስገረማቸው ምንጮቹ ጠቁመዋል። ሌላው ቢቀር በስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ለሰሩት ጥፋት ህዝብን ይቅርታ ያለመጠየቃቸው አስገራሚ ነው ያሉት እነዚህ ወገኖች፣ በይፋ አደባባይ ወጥተው ህዝብን ይቅርታ የጠየቁት ዶ/ር ነጋሶና አቶ ገብሩ ብቻ እንደሆኑ አስታውቀዋል። አቶ ታምራትና አቶ ስዬ ግን ይህን ለማድረግ ጨርሶ እንደማይፈልጉ ከያዙት አቋም በቀላሉ መረዳት ይቻላል ብለዋል።
በሌላም በኩል የሕወሐት ማ/ኮሚቴ አባል የነበሩትና ደቡብን በበላይነት ሲያሽከረክሩ ቆይተው በ1993ዓ.ም በሙስና ወንጀል ተከሰው የታሰሩት አቶ ቢተው በላይ ለስድስት አመት ታስረው ከተፈቱ በኋላ በአቶ መለስ ዜናዊ የአፋር ክልል አማካሪ ተደርገው ተሹመው እንደነበረ ምንጮች አጋለጡ። ከአቶ አባተ ኪሾ ጋር ተከሰው የነበሩትና ከሕወሐት ተገንጥሎ ከወጣው <አንጃ> ቡድን አንዱ የነበሩት አቶ ቢተው ተመልሰው የመለስ አገልጋይ መሆናቸው ብዙዎችን ግራ ያጋባ መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል። በአፋር ክልል አማካሪ ሆነው ለሶስት አመት የሰሩት ቢተው በአሁኑ ወቅት በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኮሎጅ ተዛውረው በመስራት ላይ እንደሚገኙ ምንጮቹ አረጋግጠዋል። የአቶ ቢተው ወንድም ኮ/ል ሲሳይ (በቅፅል ስሙ ሃመዴ) ጀግና ኢትዮጲያዊና አገሩን የሚወድ ታታሪ እንደነበርና በአሰብ ውጊያ ከነሂሊኮፕተሩ ጋይቶ ማለፉን ምንጮቹ አመልክተዋል። አንድም ቀን ስሙ በነመለስ ተነስቶ የማያውቀውና የጡረታ መብቱ እንኳ ሊከበርለት ያለቻለው ሟቹ ኮ/ል ሃመዴ ልጆቹ ያለአሳዳጊ ተበትነው መቅረታቸውን ምንጮቹ ሳይገልፁ አላለፉም።

14 Comments

  1. To Mr. Tamrate…..Let me ask you a very simple question..Where did you get capital
    to starte a business in Denver ? We all know that the money u stole from Ethiopian people and was kept in Swise Bank. God will punish you because you robbed that money from Poor innocent People.

    • Any Christian (be it orthodox, protestant, ,,,,) can run a business with the objective of decent profit. But my question is where did he get the money?

  2. Medre leba weyane hulu eyezerefe eyemeta meragfiyawu USA honoal. magalet alebin yehem leba tamrat behayemanot shefan edmewun liyarazm asbo neber tegalete genzebu keyet meta meteyek albet.

  3. This is usual in all idiet politican of Ethiopia. We know Tamritrat he cheat many people by coverage of religion. God will punish him

    • @ BELACHEW ..you an idiot why u insult agew? Amhara and tigre has done nothing while Agew built Lalibela that all ethiopia are now feel proud of

  4. gobeze gobez belewat yebalewan mesehafe atebech alu…
    Tamerat, neged mejemeru chegeru menu laye newu.
    Eyerusalem Araya ..astesasebehen ena amegagebhen betasetekakel terunewu
    alebelezeya endekedewmohe diakon betehon yeshalal, derom anete tehonk,,,,,,

  5. SThis individual must be tried at the world court for the crime he committed against one ethnic group. the real person surfaced. He. Was not a true believer and not GOd fearing either if so he could have Confessed his sin and asked forgiveness from the victims. There is no room for proud heart in Gods house .

  6. Since he was released from the jail, I didn’t hesitate that this man is a charlatan. He just said that he received Jesus Christ as his savior and all protestant Christians were excited. He went to US and had interview with TBN and other medias. He is a wolf in a sheep skin. He didn’t regret and never repented for his crimes that he washed his hands with numerous innocent people’s blood. If he was really repented, he should have said sorry to the people of Ethiopia whom he tortured and killed.

  7. Zemedochay sedeb menyetkemal bayehone meteyake yalebetin hulu azegajeto be masegeja asdegefo tetyake maleton jemeru enji tera sededeb zembelo lemanem yemyaetekem dekamnew.

Comments are closed.

Previous Story

አንድነት አባሎቼን በማሰር የማደርገውን የሕዝብ ንቅናቄ ማደናቀፍ አይቻልም አለ

Next Story

አውራምባ ታይምስ እንደ ወንዳ ንብ አንዴ ተኩሶ ሞተ!

Latest from Blog

አስቸኳይ ህዝባዊ ጥሪ

July 24, 2024 ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት Global alliance for the Rights of Ethiopians (GARE) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት የብዙ ወገኖቻችንን ህይዎት ማለፉን
Go toTop