ኢትዮጵያውያኑ በአላሙዲ የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ተቃውሟቸውን አሰሙ

(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያውያን የስፖርት እና የባህል ፌስቲቫል በሜሪላንድ ለ30ኛ ዓመት እያደረጉ ሲሆን በሌላ በኩል በአላሙዲ ስፖንሰር የተደረገው በRFK ስታዲየም ዲሲ በተመሳሳይ ቀን ተጀምሯል። በሜሪላንዱ የመክፈቻ ስነስርዓት ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የታደሙ ሲሆን አላሙዲ ስፖንሰር ባደረገው የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ደግሞ ጥቂት የወያኔ/ኢሕ አዴግን ሥርዓት የሚደግፉ ሰዎች ተገኝተዋል።
ይህን አላሙዲን ስፖንሰር ያደረገውን ዝግጅት በመቃወም በስታዲየሙ ደጃፍ የተቃውሞ ሰልፍ ሲያደርጉ የዋሉት ኢትዮጵያውያን “የአላሙዲ የደም ገንዘብ እይደልለንም” ሲሉ ተሰምተዋል።
አላሙዲ እጁን ከሰሜን አሜሪካው ስፖርት ፌስቲቫል ላይ እንዲያነሳ የጠየቁት ሰልፈኞቹ በተለይ አላሙዲ የስር ዓቱ ደጋፊ በመሆኑ እርሱን ብቻ የሚጠቅም የኢኮኖሚ ስርዓት በሃገሪቱ መዘርጋቱንም ሰልፈኞቹ በተቃውሟቸው አሰምተዋል።
ለ30 ዓመት የቆየውን ፌዴሬሽን ለመገንጠል አስበው ያልተሳካላቸውን አሁን በአላሙዲ ስፖንሰር የሚደረጉትን ግለሰቦች ሰልፈኞቹ “ተጠያቂ ናችሁ” ሲሉ የተሰማ ሲሆን፤ በተቃውሞ ሰልፉ ላይ በኢትዮጵያ እየደረገ ያለውን የሰብ አዊ መብት ጥሰት በማስታወስ ከወያኔ ጋር ተባብረዋል ያሏቸውን ሰዎች ስም በመጥራት አውግዘዋቸዋል። አላሙዲ በኢትዮጵያ የወሰደውን የመሬት ቅርሚትና በዚህም መሬት ላይ ያገኘውን ገንዘብ “የደም ገንዘብ” ሲሉ የገለጹት ሰልፈኞቹ በቀጣይም የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ታውቋል።
በዋሽንግተን በአላሙዲ ስፖንሰርነት የተዘጋጀው የስፖርት ፌስቲቫል በሰው እጥረት ድርቅ መመታቱን የታዘቡት አስተያየት ሰጪዎች “አላሙዲ ከፍሎ ከሌላ ስቴት ያመጣቸው ሰዎች ሳይቀሩ የርሱን ፌስቲቫል በመተው ወደ ኢትዮጵያውያኑ የሜሪላንድ ዝግጅት መምጣጣቸውን” ጠቁመዋል።
ከሲያትል በአላሙዲ ገንዘብ ሆቴልና የአየር ትኬት ተቆርጦልኝ ነው የመጣሁት ያለው አንድ አስተያየት ሰጪ “አላሙዲ ከኢትዮጵያ የወሰደውን ገንዘብ በዚህ በኩል ላካክሰው በሚል ነው በነፃ ሲቆርጡልኝ እሺ ብዬ እዚህ ከመጣሁ በኋላ በሜሪላንዱ የመክፈቻ ዝግጅት ላይ የተገኘሁት” ሲል ተናግሯል።

ተጨማሪ ያንብቡ:  በሰሜን አሜሪካ ከምንገኝ የቅማንት ተወላጆች የተሰጠ መግለጫ

9 Comments

  1. this is the best indication that ethiopians are highly rejecting weyane from everywhere and yet the end of weyane will come soon

  2. aye habesha..besewu hagerem mebochachek..
    le ethiopia selam ena democracy ke masebachu befit
    mejemeriya eres beresachu tesemamu .
    inorganic chicken and burger ,eyebelachu..astesasebachu
    ende doro kit tebabe newu..

  3. What is Up Mamo Kilo. Are you mad because ze-habesha reported your lord’s humiliation? There are certain things that money can’t buy. Certainly the billionare bought you, go ahead and bend down and leak his shoes. Money can’t by dignity, love, unity, and integrity. We might be poor, but we identfy with our people sufferings. Let us see where this aderbaynet will take you?

  4. Mamo you doma in stead of looking the bottom of the chicken why don’t you look at your self and watch your mouth. use your brain. innocent people are dieing in Ethiopia. your master woyane is looting our beloved country and a banda like you is advocating for them. please try to think twice.

  5. THE GENTLE MAN WHO TOOK ADVANTAGE OF HIS TRAVLING EXPENSE WITH ALAMUDI’S MONEY VERY CLEVER AND SMART TOO.

  6. Normally we humans should fight for the right of a single person against a government.Because whether we are Moslems or Christians we believe in god and thats our duty to protect and support each other and we know how many people are suffering in the hands of these ethnofasist(TPLF) in our mother land and now they are trying to buy some Hodams by the same money it was stolen from poor ethiopians.But in the case of ethiopia its almost 98% of our people left to live in agony and poverty.I am proud of you guys who are trying to be the voice of voiceless and show for this Billioner that he cant buy our dignity by stolen money from poor ethiopians.We have a promising movement now both inside and abroad therfore we have to support the struggle and make sure that TPLF will be history in short period of time.Go Semayawiw party,UDJ,Medrek,AEUM.(Go Ginbot7,EPPF,EPRP and all partys who are fighting for freedom.Go Obang the grate son of ethiopia and humanity before ethnicity. ESAT is giving the true Information to ethiopians and will continue to do so.But we have the responsibility to support them.God bless Ethiopia and death to TPLF and Hodams.Victory is on the way to ethiopian people.

  7. mamo: since you or weyanes appear on the stage of authority we ETHIOPIANS divided like pieces even though the division still exists all of us we hate weyanes

Comments are closed.

Share