የሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ተቃውሞ ቀጥሏል

June 26, 2013

· በአጣሪ ኮሚቴው የቀረቡት የመፍትሔ ሐሳቦች እንዲተገበሩ ጠይቀዋል
· የአቡነ ጢሞቴዎስን የሹመት ሐሳብ በማውገዝ ርምጃ ለመውሰድ ዝተዋል
· ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋራ ይወያያሉ

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት የተቃውሞ እንቅስቃሴያቸውን አጠናክረው ውለዋል፡፡ በዛሬው ዕለት ረፋድ ወደ መንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በከፍተኛ ቁጥር በማምራት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪክ አቡነ ማትያስን ለማነጋገር ያደረጉት ሙከራ ወደ ግቢው እንዳይገቡ በጥበቃ በመከልከላቸው ምክንያት አለመሳካቱ ተነግሯል፡፡

የፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት ሓላፊ አቶ ታምሩ አበራ ከጥቂት የደቀ መዛሙርቱ ተወካዮች ጋራ የተገናኙ ሲኾን፣ ደቀ መዛሙርቱ÷ ከአምስት ወራት በፊት ያቀረቧቸው ጥያቄዎች በአጣሪ ኮሚቴ ከታዩ በኋላ የተሰጡት የመፍትሔ ሐሳቦች በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲደረጉ፣ ከኮሌጁ እንዲባረር በአጣሪ ኮሚቴው የተጠቆመበትን የቀን መርሐ ግብር ሓላፊ ዘላለም ረድኤትን የኮሌጁ ሊቀ ጳጳስ በዋና ዲንነት ለማሾም ማሰባቸውን በመስማታቸው ይህን ከማስፈጸም እንዲታቀቡ ለልዩ ጽ/ቤት ሓላፊው ማሳሰባቸው ተዘግቧል፡፡

በልዩ ጸሐፊያቸው አማካይነት መልእክት ያስተላለፉት ፓትርያሪኩ፣ በነገው ዕለት ሁለት ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ኮሌጁ እንደሚልኩና በጉዳዩ ላይ ከእነርሱ ጋራ እንዲወያዩ እንደሚያደርጉ ለደቀ መዛሙርቱ ነግረዋቸዋል ተብሏል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ትላንት ሌሊት በኮሌጁ አዳራሽ ተሰብስበው ለጥያቄያቸው በአጭር ጊዜ ምላሽ እንደሚያገኙ በተሰጣቸው ተስፋና ውሎ አድሮ በታየው ኹኔታ ላይ በስፋት መወያየታቸው የተዘገበ ሲኾን ቀጣይ አካሄዳቸው የኮሌጁን መግቢያና መውጫ ከመቆጣጠር ጀምሮ በሓላፊዎች ላይ የሚወሰድን የኀይል ርምጃ ሊያካትት እንደሚችል ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ተመልክቷል፡፡

አጣሪ ኮሚቴው ሲያካሂድ በቆየው ማጣራት÷ ለኮሌጁ ሙሉ ሥልጣን ያለው ዋና ዲን እንዲሾምና ምክትል ዋና ዲን የሚለው ስማዊ ሥልጣን እንዲቀር፣ አካዳሚክ ምክትል ዲኑ ከሓላፊነታቸው ተነሥተው በማስተማር እንዲወሰኑና በምትካቸው አግባብነት ያለው ሰው እንዲተካ፣ የቀን መርሐ ግብር ሓላፊው ዘላለም ረድኤት ከኮሌጁ እንዲወገዱና ከነገረ ክርስቶስ እና ክብረ ቅዱሳን ጋራ በተያያዘ በቀረበባቸው የሃይማኖት ሕጸጽ እንዲጠየቁ በደረሰበት የመፍትሔ ሐሳብ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ ጋራ ውይይት ከተካሄደበት በኋላ እንዲፈጸም መወሰኑ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
(ምንጭ -ሐራ ተዋሕዶ)

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop