Hiber Radio: “የመጣሁት በእስር ቤት ያሉትን ጭምር እንዲፈቱ ለ እስራኤል መንግስት ጥሪ ለማቅረብ ነው” – ኦባንግ ሜቶ

June 24, 2013

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
Hiber Radio: "የመጣሁት በእስር ቤት ያሉትን ጭምር እንዲፈቱ ለ እስራኤል መንግስት ጥሪ ለማቅረብ ነው" - ኦባንግ ሜቶ 1
የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ሰኔ 16 ቀን 2005 ፕሮግራም

<<እስራኤል የመጣሁት በችግር ላይ ያሉ ወገኖቻችንን ጉዳይ በተመለከተ ከእነሱ ጋር ለመወያየት እና በእስር ቤት ያሉትን ጭምር እንዲፈቱ ለእስራኤል መንግስትና ለሚመለከታቸው ባለስልጣናት ጥሪ ለማቅረብ ነው…>>

አቶ ኦባንግ ሜቶ በእስራኤል ያደረጉትን ስብሰባ አስመልክቶ ከሰጡን ቃለ ምልልስ የተወሰደ

<<…በቬጋሱ ስፖርት ክለብ ጉዳይ ቦርዶ በአብላጫ (በሞሽን) ተጫዋቾቹ እንዲመጡ ወስኗል። ጉዳዩ ግን የመጨረሻ ውሳኔ አላገኘም።በቀጣዩ ቅዳሜ ስብሰባ ጉዳዩ የሚነሳ ይመስለኛል። ዛሬም የቬጋሱ ጉዳይ የፌዴሬሽኑ ትልቅ እንቅፋት ነው። ሰላማዊ በሆነ መንገድ ሁለቱንም ወገኖች የሚያስታርቅ ነገር ከየቦታው እየመጣ ነው።ትልቅ በዓል ለማክበር እየተዘጋጀን ነው ችግር ሆኖ የተገኘው ይሄ ነው ።የሁሉም ስጋት ነው።ጥፋት ተሰርቷል በሁሉም በኩል በእኛም ግን ጥፋትን በጥፋት ለመመለስ አለመሞከሩ ጥሩ ነበር።እስካሁን ድረስ ያ ነገር አልታየም።ቅዳሜ እለት ከፍተኛ እርብርብ ተደርጎ ሰላማዊ ነገር ይደረጋል ብዬ ሙሉ እምነት ይኖረኛል …>>

ተካበ ዘውዴ የቀድሞው የብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂና የፌዴሬሽኑ የውድድር ጉዳይ ሀላፊ

<<…አቶ ጌታቸው ኢትዮጵያውያንን እኩል በሚያየው ፌዴሬሽን እንዴት ተጫዋቾችን ባልመረጥነው ወኪል ካልመጣችሁ በሚል ቅዳሜ ሰርፕራይዝ ይኖራል ብለው ያስፈራሩናል?...>>

ከኢትዮ ስታር ክለብ አባላት አንዱ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት በአንድ ራዲዮ ላይ ለተወካዩ ወግነው የቡድኑን አባላት ያስፈራሩበትን ቃለ መጠይቅ የፈጠረበትን ቅሬታ ሲገልጽ

የብዙዎቻችንን ልብ ያንጠለጠለው የኢትዮጵያ ለብራዚሉ የአለም እግር ኳስ ውድድር የማለፍ ጉዞ እና አዲሱ እክል ሰሞነኛ ውሎ ሲቃኝ (ወቅታዊ ዘገባ)

የአባይ ፖለቲካ የሱዳን የኢትዮጵያን አቁዋም መደገፍ የሚያመጣው ፖለቲካዊ አንደምታና ግብጽ ወታደራዊ ፉከራዋን እውን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል አቅም አላት? (ወቅታዊ ትንታኔ አለን)

የኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስ ጋዜጠኛ በኡጋንዳ በወገኖቹ ጥቃት እንደተሰነዘረበት መግለጹ(ቃለ መጠይቅ)

<<…በአላሙዲ የሚደገፈውን የወያኔ የዲሲ ፌስቲቫል ኢትዮጵያውያን እንዳይገኙ እና በተቃውሞው ዕለት ከጎናችን እንዲሰለፉ እንጠይቃለን…>> አቶ መስፍን የተለጣፊውን ፌዴሬሽን ለመቃወም የተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ አስተባባሪ ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ቃለ ምልልስ የተወሰደ

ሌሎች ቃለ መጠይቆችም አሉን

ዜናዎቻችን
የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያውያን ስፖርት ፌዴሬሽን ቦርድ በአብላጫው የቬጋስ ተጫዋቾች በዘንድሮው ውድድር እንዲሳተፉ ወሰነ

የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈጻሚ የቦርዱን ውሳኔ በጽሑፍ አላሳወቀም

ፕሬዝዳንቱ ያልመረጡትን ወኪል ካልተቀበላችሁ ብለው ማስፈራራታቸውን ተጫዋቾቹ ገለጹ

የሱዳኑ ፕት አልባሽር በህዳሴው ግድብ ዙሪያ አቋማቸውን በይፋ ገለጹ; ኡጋንዳ አዲስ ግድብ ለመገንባት ከቻይና ጋር ተስማማች

ፕ/ት ኦባማ ደ/አፍሪካ ውስጥ” ታስረው ለፍርድ እንዲቀርቡ” ተጠየቀ

የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝ በአሜሪካን ባለስልጣናት ፊት ተብጠለጠለ ዶ/ር ብርሃኑ “መፍትሄ ካልተበጀ መጨርሻው አያምርም “ይላሉ

<<ትኩረት እንሻለን!>><<በደል በዛብን!>> በግብጽ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

Latest from Blog

ነገሩ እንዲህ ነው ባሳለፍነው ታህሳስ 15 በተካሄደው ብልጽግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ ላይ የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አረጋ ከበደ እጃቸውን አውጥተው ተናገሩ እኔ አቅቶኛል የአማራ ክልል ቀውስ ማስተዳደር አልቻልኩም ብለው ተናገሩ በዚህ ጊዜ

“አንተን ለማኝ አደርጋለሁ” አቢይ አሕመድ ለአማራ ክልል ፕረዚዳንት ለአረጋ ከበደ የሰጠው ማስጠንቀቂያ

January 31, 2025
ከቴዎድሮስ ሃይሌ የምናከብራቸው ጀነራል ተፈራ ማሞ ሰሞኑን አደባባይ ወጥተው አድምጠናል:: የጀነራሉ ጤንነትና ደህንነት ሲያሳስበን ለቆየነው ወገኖች ሁሉ በጥሩ ቁመና ላይ ሆነው በማግኘታችን የሕሊና እረፍት ሰጥቶናል:: አሁንም ባሉበት ሰላሞት እንዲበዛ ምኞታችን ዳር የለውም::

እስክንድር ነጋ እና ጀነራል ተፈራ ማሞ ከድል ለዲሞክራሲ እስከ ፉኖ ተሰማራ!

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) ዛሬም እንደ ትናንቱ አያሌ ምሁራንና ታዋቂ ነን ባይዎች ስለብሔራዊ ሽምግልና እርቅ ይደሰኩራሉ፡፡ ያለምንም ሐፍረት ቅዱሱን ሽምግልናን ከምእራብ ከተሸመተው ኤፍሬም ይሳቃዊ ድርድር ጋር እያምታቱ የአያት የቅድመ አያቶቻችንን የተባረክ የሽምግልና ሐብት ያበላሻሉ፡፡ ሽምግልና በመለኮት

ፍትህ የሌለው ሽምግልናና እርቅ ሥራ እንደሌለው እምነት የሞተ ነው!

Go toTop