August 9, 2015
3 mins read

በባህር ዳር ቀበሌ 11 ወጣቶችና በፖሊሶች መካከል ግጭት ተፈጠረ * አባላቱ በገፍ እየከዱት በሚገኘው አየር ኀይል አለመተማመኑ ስር ሰዷል

Photo File
በባህር ዳር ቀበሌ 11 ወጣቶችና በፖሊሶች መካከል ግጭት ተፈጠረ * አባላቱ በገፍ እየከዱት በሚገኘው አየር ኀይል አለመተማመኑ ስር ሰዷል 1

አርበኞች ግንቦት 7 ድምጽ እንደዘገበው የባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 11 አባይ ማዶ ወጣቶች አንድ አካባቢ ላይ ተሰባስበው በመጫወት ላይ እያሉ ፖሊሶች ድንገት መጥተው “ለምን አንድ ላይ ተሰብስባችሁ ቆማችሁ?” በማለት አምባጓሮ በመፍጠራቸው ነበር ግጭቱ የተነሳው፡፡
ፖሊሶቹ ወጣቶችን ከቆሙበት በኃይል አባረው ወደየቤታቸው ለማስገባት ሲሞክሩ ወጣቶቹ በፖሊስ ላይ የአጸፋ እርምጃ በመውሰዳቸው አንድ ፖሊስ ለከፋ ጉዳት እንደተዳረገ ታውቋል፡፡
የህወሓት አገዛዝ ለስልጣኑ የሚያሰጋውን የህብረተሰብ ክፍል እየመረጠ ትጥቅ ማስፈታቱን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ አምባገነናዊ ስርአት የግብአተ መሬት ጊዜውን በጥቂቱም ቢሆን ያራዝምልኛል ብሎ ከነደፋቸው እቅዶች መካከል አንዱ የሆነውን ህዝቡን ትጥቅ የማስፈታት ተግባር በታች አርማጭሆ ገበሬዎች ላይ በተለየ ሁኔታ በግፍ የሚያስታጥቀው የህብረተሰብ ክፍል ያለው ዘረኛው የህወሓት ቡድን በአማርኛ ተናጋሪው ገበሬ ላይ አሁን እየፈፀመ የሚገኘው የትጥቅ ገፈፋ ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ ሲያደርገው የቆየው መሆኑ ይታወቃል፡፡
አባላቱ በገፍ እየከዱት በሚገኘው አየር ኀይል ውስጥ ተፈጥሮ የቆየው አለመተማመን ስር ሰዶ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ታወቀ፡፡
ለሰላም ማስከበር ተልኮ ወደ ደቡብ ሱዳን ሊሄዱ የተመለመሉት የአየር ሀይል አባላት የደቡብ ሱዳን ጉዞ ተሰርዞ ወደ ሱማሊያ እንደሚሄዱ ስለተነገራቸውና በግምገማ በመወጠራቸው ምክንያት በርካታ አብራሪዎች፣ ቴክኒሻኖች እና ሌሎች የተለያዩ ክፍሎች ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞች በመክዳት ላይ ናቸው፡፡
በመሆኑም በአየር ሀይል ውስጥ አለመተማመኑ ገደቡን አልፎ አብራሪዎች ለልምምድ በሚያበሩት አውሮፕላን ውስጥ የህወሓት አባላት ከጎን እንዲቀመጡ እየተደረገነው፡፡ በተጨማሪም አብራሪዎች ነዳጅ በሚሞሉበት ጊዜ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡

1 Comment

Comments are closed.

Previous Story

በሞስሊሙ ማኅበረሰብ መሪዎች ላይ የተወሰነውን እስራት ሸንጎ ያወግዛል።

Next Story

ለኢትዮጵያዊውስ ማን አለው?

Latest from Blog

“መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የሚለው የዲያስፖራ ከንቱ አታካራ! – ክፍል ሁለት

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com) በአንዳንድ ስብሰባዎችና የሕዝብ መገናኛ መድረኮች የሚታየው የአንዳንድ ዲያስፖራዎች  “መነሻችን እዚህ መዳረሻችን እዚያ” የበከተ ከንቱ አታካራ በልጅነታችን ወላጆቻችን ትምህርት እንዲሆነን ይተርኩልን የነበረውን ከጫጉላ ወጥተው ጎጆ ለመመስረት የታከቱ ሁለት ያልበሰሉ ባልና ሚስትን ታሪክ

መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ እና ወያኔያዊ መሠረቱ

የማይወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል። የዛሬን አያድርገውና የትግሬ ልሂቆች “ትግራይ የጦቢያ መሠረት ናት ።  ጦቢያ ያለ ትግራይ፣ ትግራይ ያለ ጦቢያ ሊታሰቡ አይችሉም” በማለት ጦቢያዊ ከኛ ወዲያ ላሳር እያሉ አለቅጥ ይመጻደቁ፣ ይኩራሩ፣ ይታበዩ ነበር። ወያኔ

አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው ወንጀሎች ጥፋተኛ ተባሉ

ለአመታት በእረስር ላይ የሚገኙት  አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱባቸው የጥላቻ ንግግር ማሰራጨት እና የዕርስ በዕርስ ግጭት መቀስቀስ ወንጀሎች ጥፋተኛ መባላቸው ታውቋል፡፡ አቶ ታዲዮስ ታንቱ በተከሰሱበት ክሶች በዛሬ ቀጠሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ

ከ”ችርቻሮ” ድል አልፎ ለመሄድ የአንድነት አስፈላጊነት – ግርማ ካሳ

በአሁኑ ጊዜ ሁለት የፋኖ አሰላለፎች አሉ:: መኖር ያልነበረበት:: አንከር ሜዲያ ከሁለቱም አሰላለፎች፣ ሁለት ፋኖ መሪዎች ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች፡፡ ሁለቱን አደመጥኩ፡፡ በሰማሁት ነገር ተደስቻለሁ:: ትልቅ ተስፋ እንድሰንቅም አድርጎኛል:: የአማራ ህዝባዊ ድርጅት የፖለቲካ
Go toTop